Mensur Abdulaziz Profile Picture
UMMA TOKEN INVESTOR

Mensur Abdulaziz baham ko'rdi
Tarjima qilib boʻlmadi.

✍🏻 ስለ ሻዕባን ወር አጫጭር ጥቆማዎች

┄┄┉┉✽‌»‌🌼»‌✽‌┉┉┄┄

☞ በሸይኽ ሙሐመድ ሷሊህ አል ዑሰይሚን

«ሙስሊሞች ሆይ ያለነው በሻዕባን ወር ላይ ነውና በዚህ ወር ዙርያ አንድ ስድስት ነጥቦችን በማውሳት ልንከተለው ስለሚገባን ግዴታችን እናብራራለን።

💥የመጀመርያው ነጥብ

የሻዕባን ወር ከሌሎች ወራት በተለየ ሁኔታ በፆም ይለያልን? አዎን ይለያል ። ምክንያቱም ነቢዩ [ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም] «በዚህ ወር ፆም ያበዛሉ። ከወሩ ጥቂት ቀናት እስኪቀራቸው ወሩን ይፆሙት ነበርና።»

በዚህም ሱና መሰረት የአላህ መልእክተኛን [ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም] በመከተል በዚህ በሻዕባን ወር ፆም ማብዛት አለብን።

💥ሁለተኛው ነጥብ

የሻዕባን ወር አጋማሽ ቀን ፆምን የተመለከተው ነው። ይህንን ቀን ለይቶ መፆምን የሚመለከቱ ከነቢዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ያልተገኙና ትክክለኛ ያልሆኑ ደካማ ሀዲሶች ተነግረዋል። በነዚህ ተመርኩዞ ይህንን ዒባዳ መፈፀም ደግሞ አይቻልም። ከነቢዩ ለመተላለፉ ባልተረጋገጠ ማንኛውም ነገር አላህን ማምለክ አይፈቀድም። በመሆኑም የሻዕባን አስራ አምስተኛው ቀንን ለይቶ መፆም የሌለ ነገር ነው። ከመልእክተኛው ለመገኘቱ መረጃ ከሌለ ደግሞ ቢደዐ ነው።

💥ሶስተኛው ነጥብ፤ የሻዕባን ወር አስራ አምስተኛው ቀን ሌሊት ትሩፋትን ይመለከታል።

ልክ ቀኑን መፆም የተረጋገጠ መረጃ እንደሌለው ሁሉ ለሌሊቱም ከሌሎች ሌሊቶች በላጭ ነው ተብለው የተነገሩት ሀዲሶች ከነቢዩ [ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም] ለመነገራቸው ትክክለኛ መረጃ የሌላቸው ደካማዎች ናቸው።

ስለሆነም የሻእባን አጋማሽ ሌሊት ልክ እንደ ረቢዕ ወር ሌሊት፣ እንደ ረጀብ ወር ሌሊት እንጂ የተለየ ነገር የለውም። ተነገረ የተባለውም መረጃ ቀድሜ እንደገለፅኩት ደካማዎች ናቸው።

💥አራተኛው ነጥብ

ይህችን የአስራ አምስተኛዋን ሌሊት ለየት አድርጎ ዝግጅት ፈጥሮ ማሳለፍ ቢደዐ ነው። ነቢዩ [ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም] ለየት አድርገው ያሳዩን፣ ሌሊቱን የሚሰገድ አምልኮትም ዝግጅትም የለምና። ስለዚህ ምሽቷ ልክ እንደ ሌሎች ምሽት ናት። አንድ ሰው ከዚያች ሌሊት በፊትም የለይል ሰላት መስገድ ልምዱ ከነበረ በዚያች ሌሊትም ተነስቶ መስገዱ ልክ እንደበፊቱ ነውና ችግር የለውም። ካልሆነና በፊት የማይሰግድ ከነበረ ዛሬ በሻዕባን "ለይለቱ ኒስፍን" ለየት አድርጎ መስገድ የለበትም። ምክንያቱም ከአላህ መልዕክተኛ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ያልተገኘ ተግባር ነውና። ከዚህም የከፋው ደግሞ አንዳንዱ ሰው የሆነ ያህል ረከዓ በዚህ ምሽት ይሰገዳል በሚል ለየት ያደርገዋል። ይሁንና ከነቢዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ይህንን ምሽት ነጥሎ ለየት ማድረግ ስላልተገኘ ይህችን ምሽት በሰላት ልዩ አናደርግም።

💥አምስተኛው ነጥብ

የአላህ ሱብሃነሁ ለነገሮች የሚያደርገው ውሳኔ በሻዕባን አስራ አምስተኛዋ (አጋማሽ) ምሽት ነውን❓

ምላሹም አይደለም ሲሆን፤ ምሽቷም የመወሰኛይቱ ሌሊት [ለይለቱል ቀድር] አይደለችምና ነው። ምክንያቱም "ለይለቱል ቀድር" በረመዳን ውስጥ የምትገኝ ምሽት ናት። ሃያሉ አላህ እንዳለው፤

”إنا انزلناه“

"እኛ አወረድነው" ማለትም ቁርኣንን ለመጀመርያ ግዜ ያወረድነው ማለቱ ነው። ይህም ሙሉ ምዕራፉ ሲነበብ እንዲህ ይላል፤

إِنَّا أَنزَلْنَاهُ فِي لَيْلَةِ الْقَدْرِ ﴿١﴾ وَمَا أَدْرَاكَ مَا لَيْلَةُ الْقَدْرِ ﴿٢﴾ لَيْلَةُ الْقَدْرِ خَيْرٌ مِّنْ أَلْفِ شَهْرٍ ﴿٣﴾ تَنَزَّلُ الْمَلَائِكَةُ وَالرُّوحُ فِيهَا بِإِذْنِ رَبِّهِم مِّن كُلِّ أَمْرٍ ﴿٤﴾ سَلَامٌ هِيَ حَتَّىٰ مَطْلَعِ الْفَجْرِ ﴿٥﴾

Al-Qadr☞ القدر:- [1-5]

[እኛ (ቁርኣኑን) በመወሰኛይቱ ሌሊት አወረድነው፡፡ (1)መወሰኛይቱም ሌሊተ ምን እንደ ኾነች ምን አሳወቀህ? (2)መወሰኛይቱ ሌሊት ከሺሕ ወር በላጭ ናት፡፡ (3) በርሷ ውስጥ መላእክትና መንፈሱ በጌታቸው ፈቃድ በነገሩ ሁሉ ይወርዳሉ፡፡ (4) እርስዋ እስከ ጎህ መውጣት ድረስ ሰላም ብቻ ናት፡፡(5)]

ይህ ክስተትና ምሽቱም መቼ እንደሆነ ሲገልፅ እንዲህ ይላል፤

(شَهْرُ رَمَضَانَ الَّذِي أُنزِلَ فِيهِ الْقُرْآنُ هُدًى لِّلنَّاسِ وَبَيِّنَاتٍ مِّنَ الْهُدَىٰ وَالْفُرْقَانِ ۚ فَمَن شَهِدَ مِنكُمُ الشَّهْرَ فَلْيَصُمْهُ ۖوَمَن كَانَ مَرِيضًا أَوْ عَلَىٰ سَفَرٍ فَعِدَّةٌ مِّنْ أَيَّامٍ أُخَرَ ۗ يُرِيدُ اللَّـهُ بِكُمُ الْيُسْرَ وَلَا يُرِيدُ بِكُمُ الْعُسْرَ وَلِتُكْمِلُوا الْعِدَّةَ وَلِتُكَبِّرُوا اللَّـهَ عَلَىٰ مَا هَدَاكُمْ وَلَعَلَّكُمْ تَشْكُرُونَ) البقرة:- 185

[(እንድትጾሙ የተጻፈባችሁ) ያ በርሱ ውስጥ ለሰዎች መሪ ከቅን መንገድና (እውነትን ከውሸት) ከሚለዩም ገላጮች (አንቀጾች) ሲኾን ቁርኣን የተወረደበት የረመዳን ወር ነው፡፡ ከእናንተም ወሩን ያገኘ ሰው ይጹመው፡፡ በሽተኛ ወይም በጉዞ ላይ የኾነም ሰው ከሌሎች ቀኖች ቁጥሮችን (በልኩ) መጾም አለበት፡፡ አላህ በእናንተ ገሩን (ነገር) ይሻል፡፡ በእናንተም ችግሩን አይሻም፡፡ ቁጥሮችንም ልትሞሉ አላህንም ቅኑን መንገድ ስለመራችሁ ታከብሩትና ታመሰግኑት ዘንድ (ይህን ደነገግንላችሁ)፡፡ (185)]

በዚህም መረጃ መሰረት ለይለቱል ቀድር ማለትም ፈጣሪያችን አላህ ለማንኛውም ነገር ሁሉ አመታዊ ውሳኔ የሚሰጥበት ምሽት በረመዳን ወር ውስጥ የምትገኝ አንዲት ሌሊት መሆኗን እንረዳለን። ምክንያቱም ሌሊቷ ቁርኣን የወረደባት ሌሊት ነች ። ቁርኣን ደግሞ የወረደው በረመዳን ወር ነውና የመወሰኛይቱ ምሽትም የምትገኘው በረመዳን እንጂ በሌላ ወር አይደለም። ስለሆነም የሻዕባን አጋማሽ ሌሊት "ለይለቱል ቀድር" የመወሰኛይቱ ምሽት አይደለችም። በዚያች ሌሊትም ለአመቱ የሚሆን ምንም የሚወሰን ነገር የለም።

💥ስድስተኛው ነጥብ፦ የሻዕባን ወር አጋማሽ ቀን ላይ አንዳንዶች ምግብ አዘጋጅተው ለድሆች በሚል የሚያከፋፍሉትና የእናት እራት፣ የአባት እራት ወይም የወላጆች እራት የሚሉት [እንዲሁም ባገራችን የእህል ዘሮችን ባንድ ላይ ሰብስቦ በመቀቀልና ከዚያም መጀመርያ ግቢ ውስጥና ውጪም በመበተን አመቱ የጥጋብ የርጋታ ይሁንልን የሚሉት] ሁሉ ከነቢዩ ያልተላለፈልን ከሰሃቦችም ሪድዋኑላሂ አለይሂም ያልተገኘ መጤ የሆነ ቢድዐ ነው።

👆 እነዚህን ስድስት ነጥቦች ጠቅሼ ብቆጥራቸውም ሌሎች ላብራራቸው የሚገቡ ሆነው ያለፍኳቸው እንዳሉ ግልፅ ነው። አላህ እኛንም እናንተንም ሱናን የሚያሰራጩ፣ ቢድዐን የሚያስጠነቅቁና ተመርተው የሚመሩ (ቅን ሆነው የሚያቀኑ) ያድርገን። ነቢዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም በጁምዓ ኩጥባቸው ወቅት እንደገለፁት ከምሪቶች ሁሉ በላጩ የሳቸው ምሪት ነውና ቅኑን መንገድ የሚከተሉ፣ በሳቸው አመራርም የሚመሩ ያድርገን። «በማስከተል፤ ከንግግሮች ሁሉ በላጩ የአላህ ኪታብ ነው። ከአመራሮች ሁሉ በላጩም የሙሀመድ ምሪት ነው። መጥፎ ጉዳይ ማለት መጤዎቹ ናቸው። ሁሉም ፈጠራዎች ጥመት ናቸውና።»ብለዋል።

🍀〰〰〰〰〰〰🍀

በታላቁ ፈቂህ ሸይኽ ሙሐመድ ሷሊህ አል ዑሰይሚን [ረሂመሁላህ]

__

3 ሻዕባን 1437/ 11 ሜይ 2016

ትርጉም፦ አቡፈውዛን

t.me/ReshadMuzemil

Xabar sifatida yuborish
Sahifamda baham ko'rish
Guruhda ulashish
Mensur Abdulaziz baham ko'rdi
Tarjima qilib boʻlmadi.

✨የቅርብ ሰዎችን ታገስ✨

የቅርብህ ሰዎች ስህተታቸው የጎላ ነው፡፡ ይህ የሆነበት ምክንያት ከሩቆቹ ሰዎች ይልቅ አጠገብህ ያሉ ሰዎች ብዙ ስህተት ስላለባቸው ሳይሆን ስህተታቸውን በየጊዜው የማየት እድል ስላለህ ነው፡፡ በየቀኑ የሚወስኑትን ውሳኔ፣ የሚገልጡትን ስሜትና

የመሳሰሉት ስለምትመለከት በዚያው መጠን እነሱን ለመታገስ ካልወሰንክ የቅርቡን እየናቁ የሩቁን የማከበር ወጥመድ ውስጥ መግባትህ አይቀርም፡፡

ከዚህም በተጨማሪ፣ የቅርብ ወዳጆችህ ካላቸው ቅርበት የተነሳ ራሳቸውን ግልጽ አድርገው የመቅረባቸውም ሁኔታ የመናቅን ዝንባሌ ሊያሳድሩብህ ይችላል።

ሰዎችን ባወቁ መጠን ከመናቅ ይልቅ

መታገስና ማክበር የበሳሎች ምልክት ነው፡

t.me/hikem2

Xabar sifatida yuborish
Sahifamda baham ko'rish
Guruhda ulashish
Mensur Abdulaziz baham ko'rdi
Tarjima qilib boʻlmadi.

🔶የወሊድ መከላከያ(contraceptive) መጠቀም?🔶

👉ጠያቂው ይላል፦ባልና ሚስት የወሊድ መከላከያ(contraceptive)ለመጠቀም ቢስማሙ ይህም ሚስትየው ስለታመመች ሳይሆን አራት ልጆች ብቻ እንዲኖራቸው በመስማማታቸው ነው።ህልማቸውም ተሳክቶ ከዚያ በኋላ ሚስት ከባሏ በመስማማት መከላከያውን ተጠቀመች።የዚህ ነገር ፍርዱ ምንድነው?እናም ባል ሳይስማማ ብትጠቀመውስ ፍርዱ ምንድነው?በዚህ ላይ ወንጀል እና ሸሪዓን መፃረር አለበትን?

👉ሸይኽ ኢብኑ ዑثይሚን(رحمه الله) ሚስት ያለ ባሏ ፈቃድ የወሊድ መከላከያ መውሰዷ በሷ ላይ ሀራም ነው።ምክንያቱም ለባሏም በልጆቹ ጉዳይ ሐቅ አለውና።ከሰዎች ብዙዎቹ(በዋነኝነት)ሚዘወጁት ልጆችን ፍለጋ እንጂ ለሌላ አይደለም።መከላከያውን በባሏ ፈቃድ መውሰዷን በተመለከተ እዚያ ላይ ሀጃ ያለባት ከሆነ-እርግዝናው ከተከታተለ ይህችን ሴት ሚያደክማትና ሚከብዳት ከሆነ በተለይም ቶሎ ቶሎ ከሚያረግዙት ከሆነች የዛኔ በባሏ ፈቃድ መጠቀሟ ችግር የለበትም።ነገር ግን እዛላይ ሚጣራ ነገርና(እንድትጠቀም በቂ ምክንያት)እና ሀጃ ከሌለ ልትጠቀም አይገባም።ምክንያቱም ይህ ነገር ሸሪዓችን ልጆችን ከማብዛት አንፃር ተፈላጊ የሆነውን ነገር ስለሚጋፋ ነው።ልጆችን ማብዛት ተፈላጊ እና የተጠበቀ ጉዳይም ጭምር ነው-ከኡማው ልቅእና ነው።አላህ(سبحانه وتعالى)በርግጥም በኢስራኢል ልጆች ላይ እንዲህ በማለት ተመፃድቋል(በፀጋው አስታውሷቸዋል)"ከነገድም የበዛችሁ አደረግናችሁ"(አል-ዒስራእ:6)እንዲሁም ነብዪሏሂ ሹዐይብም(عليه السلام)ህዝቦቹን እንዲህ በማለት አስታውሷቸዋል"ጥቂጦችም በነበራችሁና በበዛችሁ ጊዜ አስታውሱ"(አል-አዕራፍ:86)ነብያችንም(عليه الصلاة والسلام)የቂያም እለት በኡማቸው ብዛት በነብያቶች ይፎክሩባቸዋል(ይፎካከሩባቸዋል)።

ይህ ሰው(ባል)እና ሚስት አራት ልጆች ብቻ እንጂ ከዚያ በላይ የማይፈልጉ ሆነው የመስማማታቸው ሁኔታ ከነሱ የሆነ ስህተት ነው።እነዚህ አራቶቹም ልጆች ወይም ከፊሎቹ ሊሞቱ ይችላሉ።ሲቀጥል ማነው የልጆች ብዛት አራት ነው ያለው?።በል እንደውም ልጆች በበዙ ቁጥር በላጭ እና ለሰው ልጅ ልቅእና ነው ሚሆነው።አላህ(سبحانه وتعالى)በነዚህ ልጆች(ስበብ) መልካም ነገርን:በረከትን:እውቀትን እና በአላህ መንገድ መታገልን ሊያደርግ ይከጀላልና ከነሱ(ባልና ሚስት)ይህን(የልጆች ቁጥርን መገደብ)መተግበር አስፈላጊ አይደለም።

📖(ኑሩን ዐላ ኧድ-ደርብ)

📗ማጠቃለያ

🔹ድህነትን ፈርቶ የወሊድ መከላከያን መጠቀም አይቻልም-ስለሁሉም ሪዝቅ አላህ ቃል ገብቷልና።

🔹ከእርግዝና ጋር በተያያዘ በመደራረቡ ጉዳት ሚያመጣ ከሆነ እና በልጆቹም እድገት እና እንክብካቤ በማድረጉ ሂደት ችግር(non economical)ሚገጥም ከሆነ ብትጠቀም ችግር የለውም

🔹ምትጠቀመው መከላከያ እስከመጨረሻው መውለድን ሚያግድ መሆን የለበትም።ይልቁንም በሀጃዋ ያህል መሆን አለበት።

🔹በሀጃዋ ያህል ከሆነ ክኒንም(oral contraceptive) ይሁን IUD ወይም ሌላ አይነት መጠቀም ትችላለች።( ጎንዮሽ ጉዳትን ከግምት ውስጥ ማስገባት እንደተጠበቀ ይሆናል።)

Xabar sifatida yuborish
Sahifamda baham ko'rish
Guruhda ulashish
Mensur Abdulaziz baham ko'rdi

حكى ابن كثير وابن رجب الحنبلي عن شيخ اسمه عفيف الدين يوسف بن البقال

(وكان رجلًا صالحًا ورعًا زاهدًا)

أنه قال : كنت بمصر فبلغني ما وقع من القتل الذريع ببغداد في فتنة التتار ،

فأنكرت في قلبي وقلت : يا رب ، كيف هذا وفيهم الأطفال ومن لا ذنب له ؟

فرأيت في المنام رجلًا وفي يده كتاب ، فأخذته فقرأته ،

فإذا فيه هذه الأبيات ، فيها الإنكار عليّ :

دع الاعتراض فما الأمر لك ... ولا الحكم في حركات الفَلَك ولا تسأل الله عن فعله ... فمن خاض لُجّة بحر هلك إليه تصير أمور العباد ... دع الاعتراض فما أجهلك.

البداية والنهاية ٤٨٠/١٧ ، وذيل طبقات الحنابلة ١٠٣/٤.

قال الله تعالى : {مَا أَصَابَ مِن مُّصِيبَةٍ فِي الْأَرْضِ وَلَا فِي أَنفُسِكُمْ إِلَّا فِي كِتَابٍ مِّن قَبْلِ أَن نَّبْرَأَهَا ۚ إِنَّ ذَٰلِكَ عَلَى اللَّهِ يَسِيرٌ * لِّكَيْلَا تَأْسَوْا عَلَىٰ مَا فَاتَكُمْ وَلَا تَفْرَحُوا بِمَا آتَاكُمْ ۗ وَاللَّهُ لَا يُحِبُّ كُلَّ مُخْتَالٍ فَخُورٍ}.

image
Xabar sifatida yuborish
Sahifamda baham ko'rish
Guruhda ulashish
Mensur Abdulaziz baham ko'rdi
Tarjima qilib boʻlmadi.

ፍልስጤሞችንና እስራኤላውያንን አስመልክቶ እውነታው ምንድን ነው?

በሸይኽ ኢልያስ አሕመድ

ከሁዳ መልቲሚዲያ

Umma Life // One Umma // One Network

https://ummalife.com/adnankemal

9 ko'rish
Xabar sifatida yuborish
Sahifamda baham ko'rish
Guruhda ulashish