UMMA TOKEN INVESTOR

About me

إذا لم تستحي فصنع ما شئت. فربك يحسبك ما يدعك

umet mehamed shared a
Translation is not possible.

«ሒጃባችሁን ካላወለቃችሁ ፈተና ላይ አትቀመጡም‼»

በዩኒቨርሲቲ ደረጃ የዚህ አይነት የወረደ አመለካከት የሚያራምዱ ጽንፈኛ መምህራን መኖራቸው ግልፅ ነው ግን እዚሁ በዋና ከተማችን አዲስ አበባ ውስጥ እህቶቸችን «ሒጃባችሁን ካላወለቃችሁ ፈተና ላይ አትቀመጡም‼» እየተባሉ ከሆነ ተማሪዎቹ ሳይሆኑ የሀገሪቱ ሙስሊም ማህበረሰብ ምላሽ የመስጠት ኃላፊነት አለበት ተጣርቶ እርምጃ መወሰድም አለበት።

አንዳንድ ታዋቂ ሰዎች ኒቃብ አስገዳጅ አይደለም እያሉ የተናገሩት የደካሞች ንግግር ጠንካራ እህቶችን ተጋላጭ እያደረገ ይገኛል ምክንያቱም አሁን ላይ ሂጃብ ራሱ መልበስ አትችሉም ወደማለት መጡ ስለዚህ ጠንካራ ምላሽ መስጠት ያስፈልጋል፡፡

«አትፈተኑም ብሏል የተባለው በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሰብዓዊ መብት ትምህርት መምህር ነው። 2ኛ አመት ተማሪዎችን final exam ለመፈተን በገባበበት ሰአት ሒጃቢስቶችን ወይ ሂጃባችሁን አውልቁ ወይ ደግሞ ክላሱን ለቃችሁ ውጡ በማለት በእብሪት ተናግሯል። የአንዲት እህትንም ሒጃብ ለማውለቅ ሙከራ አድርጓል። ልትወጣ ስትል ተመለሺ ብሎ ተመልሳ ብትፈተንም እሷ ላይና ሌሎች ሒጃቢስቶች ላይ በሙሉ ፈርሟል ተብሏል።

አንድ መምህር የአንዲት ሴትን ልብስ ለማውጣት መሞከር ራሱ እጅግ አስነዋሪ ድርጊት ነው በተማሪዎቹ ላይም ትልቅ የስነ ልቦና ጫና ይፈጥራል ምናልባት በጣም ጎበዝ ካልሆኑ ፈተናውን ራሱ ተረጋግተው አልሰሩም ማለት ነው፡፡

ይህ ድፍረት እና ሙስሊም ጠልነት በጊዜ ሊታረም ይገባል ሂጃቧን ለማውለቅ የሞከረባትን ተማሪንም ይቅርታ መጠየቅ አለበት ዩኒቨርሲቲውም 20ኛው ክፍለ ዘመን አስተሳሰብ ላይ የተቸነከሩ መምህራን ጋር ከመንቀራፈፍ ወጥቶ ተራማጅ መሆን አለበት፡፡

የጊቢው ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ጉዳዩን አጠንክሮ መያዝ አለበት!

በሙስሊሙ ዓለም የተፈጠሩ ሁሉንም አዳዲስ መረጃዎች በተለይም በወቅታዊ የፍልስጤም ጉዳይ እውነተኛ እና ሚዛናዊ መረጃ ለማግኘት የሙሐመድ ትውልድ ገፅን ፎሎው ያድርጉ

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
umet mehamed shared a
Translation is not possible.

ጉድህን ተመልከት‼

===============

(ገንዘብህ የት የት እንዳለ ና ላሳይህ!)

||

✍ ስለ ባንኮች ብዙ ያላስተዋልናቸው ሚስጥሮች አሉ። ባለፈ በፈረንጆቹ ጁን 2023 ላይ በወጣው መረጃ መሠረት በጣም በርካታ ቢሊዮን ብር ከሙስሊሙ የሰበሰቡ ባንኮች አብዛሃኛውን ገንዘብ መልሰው ፋይናንስ አላደረጉም (ለሙስሊሙ አላበደሩም)። በዚህ ረገድ ጀማሪ እንደመሆናቸው መጠን ዘምዘምና ሂጅራ የተሻለ ፋይናንስ አድርገዋል። ሌሎች አንዳንድ ያልጠበቅኳቸው ባንኮችም በአንፃሩ ጥሩ ፋይናንስ አድርገዋል። የኛዎቹ አቅማቸውን ሼር በመግዛት፣ አካውንት በመክፈትና መሰል እገዛዎች ብናጠባክራቸው ኖሮ የሰጠናቸውን መልሶ ለማበደር እንደማይሰስቱ ይህ ያሳያል።

ዋናዎቹ ግን የሙስሊሙን ብር አፍነው ይዘው ምን እየሠሩበት እንደሆነ አላህ ይወቅ። ምናልባትም በወለድ ለሌላ እያበደሩት ይሆናል።

ይሄው ያበደሩት ራሱ ለነማን እንደሆነ አላህ ይወቅ። አይደለም ሌሎቹ የኛዎቹ ራሱ ይሄንን ብድር ለማን፣ በምን መስፍርት፣ ምን አይነት በተጠናና አዋጭ መስክ ላይ፣ እንደት… እንዳበደሩት ለጊዜው እንለፈውና፤ ባንኮች ካጠራቀሙት ላይ እስከ 80% ድረስ መልሰው ፋይናንስ ማድረግ ሲገባቸው ብዙ ብር የሰበሰቡት ባንኮች ግን 10%, 23%, 24% ብቻ ነው ያበደሩት።

የሚሻለን ምን መሰላችሁ፦ ሁሉንም ከወለድ ነፃ – IFB የሚሠሩ ባንኮች፤ ወይ ራሳቸውን ችለው ባንክ ማስደረግና ሙስሊሙ እነዛ ላይ ጭምር ሼር እየገዛ እንዲሳተፍ ማድረግ፣ ወይንም አንድ ወጥ ተቆጣጣሪ ኮሚቴ ተዋቅሮ የሁሉንም ከወለድ ነፃነት መከታተል፣ ለማንና እንደት እንደሚሠሩና እንደሚያበድሩ መቆጣጠር፣ የኛዎቹ ባንኮች በውስጣቸው ያለውን አንዳንድ የብድር አሰጣጥ፣ የሠራተኛ ቅጥር፣ የውጭ ምንዛሬ አሰጣጥ፣ በአካባቢያዊነትና ትውውቅ የቆሸሸ አካሄድ አጸዳድቶ አቅማቸውን ማጠንከር፣ ሼር መግዛት፣ አካውንት መክፈት፣ አሠራራቸውን ማዘመን፣ ሙያን ለባለሙያ ሰጥቶ እድገታቸውን ማፋጠን፤ ለነገ ይደር የማይባል የሁላችንም የቤት ሥራ ነው። ባይሆን ከውጭ ውበት ይልቅ የውስጥ ጽዳት ይቀድማልና ከዚያ በመጀመር፤ ማንም ቅሬታ የሌለበት አካታችና ሁሉም የራሴ ብሎ የሚያያቸው፣ ለነገ ከፍታቸው ሲባል ዛሬ በሙያውም፣ በገንዘቡም መስዋዕትነት የሚከፍልላቸው ባንኮች እናደርጋቸዋለን ኢንሻ አላህ።

||

t.me/MuradTadesse

fb.com/MuraadTadesse

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
umet mehamed shared a
Translation is not possible.

⚫️👉*የጁመዓ መልእክት*

📩

*ነቢዩ ሙሀመድ ﷺ *የሚከተለውን ብለዋል፦*

_ፀሀይ ከወጣችበት በላጩ ቀን የጁሙአ ቀን ነው በዛች ቀን ነቢዩላህ አደም_ _ተፈጠረ፣ጀነትንም ገባ፣ከጀነትም ወጣ፣ የቂያማ ቀንም በጁሙአ ቀን እንጂ አትቆምም_

   *📚<ሙስሊም _ ዘግቦታል*

_በጊዜ ወደ መስጅድ መሄድ ነቢዩ ﷺ የሚከተለውን ብለዋል፦_

_የጁማዕ ቀን ላይ በእያንዳንዱ መስጅዶች በር ላይ መጀመሪያ የመጣውን መጀመሪያ ላይ ቀጣይ የመጣውን በተርታ የሚመዘግቡ መላኢካዎች አሉ ልክ ኢማሙ ሚንበር ላይ በተቀመጠ ጊዜ መዝገባቸውን ዘግተው ኹጥባ ለማዳመጥ ይመጣሉ። መጀመሪያ ሰአት ላይ የመጣ ሰው ምሳሌው ልክ ግመል ሰደቃ እንዳወጣ ነው፤ከዛ ከብት እንደሰደቀ ነው፤ከዛ ሙክት በግ እንደሰደቀ ነው፣ከዛ ዶሮ እንደሰደቀ ነው፣ ከዛ እንቁላል እንደሰደቀ ነው።_

*📚[ቡኻሪ ዘግቦታል]*

                                                  *አላህ የጁማአ ቀን  አስመልክቶ እንዲህ ይላል*

  فَإِذَا قُضِيَتِ الصَّلَاةُ فَانتَشِرُوا فِي الْأَرْضِ وَابْتَغُوا مِن فَضْلِ اللَّهِ وَاذْكُرُوا اللَّهَ كَثِيرًا لَّعَلَّكُمْ تُفْلِحُونَ

_ሶለቲቱም በተፈጸመች ጊዜ በምድር ላይ ተበተኑ፡፡ ከአላህም ችሮታ ፈልጉ፡፡ አላህንም በብዙ አውሱ፡፡ ልትድኑ ይከጀላልና፡፡_

وَإِذَا رَأَوْا تِجَارَةً أَوْ لَهْوًا انفَضُّوا إِلَيْهَا وَتَرَكُوكَ قَائِمًا ۚ قُلْ مَا عِندَ اللَّهِ خَيْرٌ مِّنَ اللَّهْوِ وَمِنَ التِّجَارَةِ ۚ وَاللَّهُ خَيْرُ الرَّازِقِينَ

*ንግድን ወይም ዛዛታን ባዩ ጊዜም ቆመህ የተዉህ ሲኾኑ ወደእርሷ ይበተናሉ፡፡ አላህ ዘንድ ያለው ዋጋ ከዛዛታም ከንግድም በላጭ ነው፡፡* «አላህም ከሰጪዎቹ ሁሉ ይበልጥ ሲሳይን ሰጭ ነው» በላቸው፡፡

_📚{ጁማዓህ-10-11}_

የጁማዕ ሶላት ሁለት ረካዐዎች ያሉት ፈርድ ሶላት ነው።

*አንድ ሰው" ዘግይቶ ቢመጣና ሁለተኛውን ረከዐ ከጀማዓጋር ከሰገደ ቀሪውን አንድ ረከዐ አሟልቶ መስገድ አለበት ። አንድ ሰው" በጣም ዘግይቶ በመድረሱ የጁማዓው ሶላት ሙሉ በሙሉ ያመለጠው እንደሆነ አራት ረከዐዎች ፈርድ የዙሁር ሶላት መስገድ ይኖርበታል። የጁማዓ ሶላት የዙሁር ሶላት ምትክ ናት።*

                                            *_ሶላት አለን-ነብይ የማውረድ ትሩፋት_*

قال صلى الله عليه وسلم « مَنْ صَلَّى عَلَيَّ صَلاَةً صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ بِهَا عَشْرًا »

_ረሱል ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም እንዳሉት‘መን ሶላ ዓለየ ሶላተን ሶለልሏሁ ዐለይሂ ቢሃ ዐሸራ’ ‹‹በኔ ላይ አንድ ጊዜ ሶላዋት ያወረደ አላህ በርሱ ላይ አስር ጊዜ ሶለዋት ያወርድለታል_

وقال صلى الله عليه وسلم : « لاَ تَجْعَلُوْا قَبْرِي عِيْدًا وَصَلُّوْا عَلَيَّ؛ فَإِنَّ صَلاَتَكَ تَبْلُغُنِي حَيْثُ كُنْتُمْ »

*ሱል ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም እንዳሉት:* _መቃብሬን የባዕል ማዕከል አታድርጉት ፡፡በኔ ላይም ሶለዋት አውርዱ፡፡ የትም ሆናቸሁ ሶለዋት ብታወርዱ ይደርሰኛል፡፡_

وقال صلى الله عليه وسلم : « الْبَخِيْلُ مَنْ ذُكِرْتُ عِنْدَهُ فَلَمْ يُصَلِّ عَلَيَّ »

*እንዲህ ሲሉም ተናግረዋል፡*_ስስታም ማለት ከርሱ ዘንድ እኔ እየተወሳሁ በኔ ላይ ሶለዋት ያላወረደ ነው፡፡_

وقال صلى الله عليه وسلم : « إِنَّ لِلَّهِ مَلاَئِكَةً سَيَّاحِيْنَ فِي اْلأَرْضِ يُبَلِّغُوْنِي مِنْ أُمَّتِي السَّلاَمَ »

*እንዲህ ሲሉም ተናግረዋል:* _ለአላህ ተጓዥ መላኢኮች አሉት፡፡ ምድር ላይ ከኡመቴ የሚላክልኝን ሰላምታ ለኔ ያደርሳሉ፡፡_

وقال صلى الله عليه وسلم : « مَا مِنْ أَحَدٍ يُسَلِّمُ عَلَيَّ إِلاَّ رَدَّ اللهُ عَلَيَّ رُوْحِيَ حَتَّى أَرُدَّ عَلَيْهِ السَّلاَمَ »

_ነብዩ(ሶ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል፡: “አንድ ሰው ሰላምታ ሲልክልኝ አላህ ነፍስ ይዝራብኝና ምላሽ_ እሰጠዋለሁ፡፡

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
umet mehamed shared a
Translation is not possible.

አንድ ቀን

"ቀብር ስንት ሰዓት⏳⏰ ነው"ተባብለው ይቀብሩሃል!

ተዘጋጅተሃል ወይ.....?!ለዚያ ቀን ያኪ?

ያረቢ መጨረሻችንን አሳምርልን ኢላሂ

ያረቢ አደራ 🤲🤲🤲

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
umet mehamed shared a
Translation is not possible.

መልዕክተኛው ከባልደረቦቻቸው መሀል ቁጭ ብለው ህግጋቶችን እያስተማሯቸው ነው።ባልደረቦቹም ከመሀከላቸው የተቀመጡትን ነቢይ በስስት እየተመለከቱ እያዳመጡ ነው።

ድንገት አንድ የአይሁድ ሊቅ ሲንደረደር ወደ ስብስቡ መሀል ገብቶ ትሁቱን መልዕክተኛ አነቃቸው። ኮሌታቸው ጨፍግጎ ከያዘም በኋላ፦‹‹ብድሬን መልስ! ድሮም በኑ ሀሺም ጎሳዎች ብድር ታዘገያላችሁ›› እያለ ያንገላታቸው ጀመር።

ይህ ሰው በርግጥ ለመልዕክተኛው ገንዘብ ያበደረ ቢሆንም የተዋዋሉበት የመክፈያ ግዜ ግን አልደረሰም ነበር።

ቀና ብሎ ለማየት የሚሳሳላቸው ዑመር ረዐ ይህንን እንግልት ሲመለከት ብድግ ብሎ ሰይፉን ከማንገቻው መዘዘ'ና፦‹‹እባክዎ አንቱ ነቢ ይፍቀዱልኝና ይህን ሰው አንገቱን ልቀንጥስ›› አላቸው።

አንገታቸው የታነቀው ነቢይ ወደ ዑመር ዙረው ፍፁም በተረጋጋ አንደበት፦‹‹ተው እንጂ ዑመር! እኔ ብድሬን እንድመልስ ምከረኝ፣ እሱም በስርዐት እንዲጠይቀኝ አድርግ እንጂ ሰይፍን ምን አመጣው?›› አሉት።

የአይሁዱ ሊቅ ተረጋግቶ ቆመ። እንዲህም አለ፦‹‹በዕውነት በላከህ ጌታ እምላለሁ፤ ብድር ልጠይቅህ ሳይሆን የመጣሁት ትዕግስትህን ልፈትን ነው። በርግጥ ብድር መመለሻ ግዜህ አልደረሰም ነበር። ግና መገለጫዎችህን ሁሉ እኛ ዘንድ ባለው የኦሪት መፅሀፍ ስለተመለከትኩ አንድ ባህሪህን ብቻ ለማረጋገጥ ነው ዛሬ የመጣሁት።

ኦሪት ላይ እንዲህ ይላል" ያ ነብይ በቁጣ ግዜ ታጋሽ ነው፣ የመሀይማንም ጉንተላ ትሁትነትን እንጂ ሌላን አይጨምርለትም" አንቱ ነቢይ ሆይ! ዛሬ ይህን አረጋገጥኩ። ከአላህ ሌላ ጌታ እንደ ሌለ እመሰክራለሁ፤ አንቱም የአላህ ነቢይ መሆንዎን እመሰክራለሁ።

አንቱ ነቢ! ያ ያበደርኮት ገንዘብ ለድኾች ምፅዋት እንዲሆን ለግሻለሁ›› ብሎ እስልምናን ተቀበለ።

Send as a message
Share on my page
Share in the group