umma1697982674 Profile Picture
UMMA TOKEN INVESTOR

About me

⭕️ إذا أردت أن تكون سلفيًا حقًا فعليك ... "إذا أردت أن تكون سلفيّاً حقًا، فعليك أن تدرس مذهب السلف بإتقان، وتعرفه ببصيرة، ثم تعمل به من غير غلو ومن غير تساهل. هذا هو منهج السلف الصحيح، أما مجرد الاد

Translation is not possible.
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.
ከአላህ ጋር ነግዶ ማን ከሰረ?!
(እውነተኛ ድንቅ ታሪክ)
💎💎💎💎💎💎💎💎💎
Mahi Mahisho
🔹🔹🔹🔹🔹
በሰባዎቹ መጀመሪያ በሀገረ ግብፅ ግዛት ተፈህና አል-አሽረፍ በምትሰኝ ትንሽዬ መንደር ውስጥ ምንም የሌለው ደሀ የግብርና መሃንዲስ ጣራዋ በተቀደደ፣ ግርግዳዋ በተፈረፈረ ደሳሳ የጭቃ ቤት ውስጥ ከወላጆቹ ጋር ጎጆውን ቀልሶ ይኖር ይዟል። ግርግዳው በጋዜጣ የተሸፈነ ቤት!! በወላጆቹ ልፋት ተምሮ ለወግ ማዕረግ በቅቶ ቢመረቅም ስራ ማግኘት ግን አልተቻለውም። ሰላህ አጢያ ይሰኛል። ያረጀ እንጂ አዲስ ልብስ ለብሶ አያውቅም። ትክክለኛው የጫማ ቁጥር 42 ቢሆንም ከቆሻሻ ገንዳ ያገኛትን 44 ቁጥር ጫማ እንዳታልቅበት በቀስታ እየረገጠ ይጓዝባታል።
 
በግብርና ፋኩሊቲ ተመርቀው በከፋ ድህነት የሚሰቃዩ፣ ስራ ለመጀመር የሚፈልጉ ዘጠኝ የመንደራቸውን ሰዎች ሰብስቦ አነስተኛ ፕሮጀክት ለመጀመር ወሰነ። አማከራቸው ተስማሙ። አስረኛ አጋር እየፈለጉ እያንዳንዳቸው 200 የግብፅ ፓውንድ አዘጋጅተው ጠበቁ።
 
ተሰብስበው ሻይ እየጠጡ ወደነበሩት አጋሮቹ ዘንድ አቀናና "አስረኛውን አጋር አግኝቻለሁ" አላቸው።
"ማን እነደሆነ ንገረን" ሲሉ ጠየቁ
"አላህ ነው" በማለት መለሰላቸው። "ገንዘባችንን ከአደጋ ለመጠበቅ፣ ኃብታችንን ለማፋፋት እርሱ አንደኛው አጋራችን ይሆናል" በማለት ንግግሩን አከለ። ሁሉም ተስማሙ።
 
በጋራ የተቋቋመው የህብረት ኩባኒያ ውሉ ፀድቆ "አስረኛው ባለድርሻ አላህ የትርፉን አንድ አስረኛ ይወስዳል" የሚለው ቃል ከውሉ ወረቀት ላይ ሰፍሮ ሁላቸውም ፊርማቸውን አኖሩ። እውነተኛ የህብረት ስራ፣ ግልፅ ስምምነት ተደረገ።
 
የፕሮጀክቱ የመጀመሪያ ዙር ውጤት ጥሩ ትርፍና የተለየ ምርት ማስተናገዱን ሲመለከቱ ለተገኘው ትርፍ ለአላህ ምስጋና ይሆን ዘንድ የምርት ዑደት ውጤቱን "የታላቁ አጋር ድርሻ" በሚል መጠኑን ለመጨመር የአላህን ድርሻ ወደ 20% ለማሳደግ ወሰኑ። በየአመቱ ከፍ እያለ የአላህ ድርሻ 50% ደረሰ። አርሰው ቡቃያውን ወቅተው ምርቱን ይሸጣሉ። ነግደው ካተረፉት የአላህን ድርሻ ሳያጓድሉ ሀቁን ጠብቀው ትክክለኛ ቦታ ላይ ያውላሉ።
 
መስጂዶች፣ የሴቶች ሒፍዝ ማዕከል የአይታሞች ማደርያ የአቅመ ደካሞች መመገብያ ተቋማትን በአላህ ድርሻ ገነቡ። ትርፉ እያደገ ሲመጣ ለመሳኪኖች የዕርዳታ ድርጅትን አቋቋሙ..
 
በግብፅ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በአንድ ትንሽዬ መንደር ውስጥ ደረጃቸውን የጠበቁ አራት ኮሌጆችን ገነቡ። እያንዳዳቸው ለ600 ተማሪዎች የሚሆን ማደርያ 1000 ተማሪዎችን የሚያስተናግዱ ኮሌጆች!
ማንኛውም የኮሌጁ ተማሪ ወደ ቀዬው ለመሄድ ሲፈልግ ነፃ ትኬት ማግኘት እንዲችል በይተል ማል የሚል ቢሮን አቋቋሙ።
 
በመንደሩ ደሃ እስኪጠፋ ተቋሙ ፋፋ። ኸይራቱ ወደ ጎረቤት መንደሮች ጭምር ዘለቀ። ስራ አጥ ወጣቶች ከድህነታቸው ተላቀው እንዲሰሩ ተመቻቸላቸው። ለጎረቤት ሀገራት አትክልቶችን ኤክስፖርት ማድረግ ጀመሩ። ምርት በሚሰበሰብበት ወቅት ለከተማዋ ነዋሪ ከትልቅ እስከ ትንሹ የአትክልት ከረጢት በስጦታ ይበረከትላቸው ገባ።
 
በረመዳን የመጀመሪያዎቹ ቀናት ኢፍጣር ተዘጋጅቶ ወንዶች በአደባባይ ሴቶች በየቤታቸው በፍቅር በአብሮነት ተሰብስበው ያፈጥራሉ። ወላጅ አልባ ሴቶች ለትዳር ሲደርሱ ወጪያቸው ተሸፍኖ ይዳራሉ።
 
ይህ ሁሉ በአላህ ድርሻ የሚሰራ መልካም ተግባር መሆኑ ያስገረማቸው መስራቾቹ የፕሮጀክቱ ባለቤትነት ወደ አላህ እንዲዞር ወሰኑ። እነርሱም የአላህ ሰራተኛ የረቢ አገልጋይ ሆኑ። ባለቤትነቱን ወደአላህ ሲያዞሩ "ትርፉ ሳይቋረጥ ድሆች ይጠቀሙ ዘንድ ጌታችን ሆይ አደራ!" የሚለውን ቃል ከውሉ ወረቀት ላይ አሰፈሩ።
 
አትራፊ ንግድ!!
መልካም ግብይይት!!
"አላህ ከምእምናን ነፍሶቻቸውንና ገንዘቦቻቸውን ጀነት ለእነሱ ብቻ ያላቸው በመኾን ገዛቸው" ይሉሀል ይህ ነው።
 
ኢንጂነር ሰላህ አጢያ በ70 አመታቸው በጉበት በሽታ ሲሰቃዩ ቆይተው እንደ አውሮጳውያን የዘመን ቀመር ጥር 11 ቀን 2016 ሩሐቸው ከጀሰዳቸው ተላቀቀች። ከግማሽ ሚሊዮን በላይ ህዝብ ጀናዛቸውን ሸኘ። እየተላቀሱ ጀሰዳቸውን ከለህዱ አሳረፉ። ልጅ አልነበራቸውም።
 
አላህ ከምህረቱ አጎናፅፎ ጀነተል ፊርደውሱን ይወፍቃቸው።
 
╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍
ምንጮቼ:-
- الشيخ خالد الجندي ينعي صلاح عطية نسخة محفوظة 25 فبراير 2020
- تفهنا الأشراف قرية بلا عاطل أو فقير نسخة محفوظة 17 مايو 2017
- صلاح عطية رجل أعمال تاجر مع الله نسخة محفوظة 12 مايو 2017 على موقع واي باك مشين
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.
ሰባቱ የ‹‹ላ ኢላሀ ኢለላህ›› መስፈርቶች (ሸርጦች)
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩኅ ናበጣም አዛኝ በኾነዉ፦
1.ዕውቀት፡- ይህም ማለት የዚህ ቃል መልዕክት እና ቃሉ ዉድቅ
የሚያደርጋቸዉንና እና የሚያፀድቃቸውን ነገሮች ጠንቅቆ ማወቅ ማለት ነው፡፡
ለዚህም ማስረጃው ቀጣዩ የአላህ ቃል ነው፡፡
ﻭَﻟَﺎ ﻳَﻤْﻠِﻚُ ﺍﻟَّﺬِﻳﻦَ ﻳَﺪْﻋُﻮﻥَ ﻣِﻦْ ﺩُﻭﻧِﻪِ ﺍﻟﺸَّﻔَﺎﻋَﺔَ ﺇِﻟَّﺎ ﻣَﻦْ ﺷَﻬِﺪَ ﺑِﺎﻟْﺤَﻖِّ ﻭَﻫُﻢْ ﻳَﻌْﻠَﻤُﻮﻥَ
ﺍﻟﺰﺧﺮﻑ : ٨٦
(እነዚያም ከአላህ ሌላ የሚያመልኳቸዉ እነሱ የሚያውቁ ሆነው በእውነት
ከመሰከሩት በስተቀር ምልጃን አይችሉም) አል-ዙኸሩፍ 86
2.እርግጠኛነት፡- በአላህ ብቸኛ አምላክነት ላይ ሙሉ በሙሉ እርግጠኛ መሆን
ነው፡፡አላህ (ሱ.ወ)እንዲህ ይላል፡-
ﺇِﻧَّﻤَﺎ ﺍﻟْﻤُﺆْﻣِﻨُﻮﻥَ ﺍﻟَّﺬِﻳﻦَ ﺁﻣَﻨُﻮﺍ ﺑِﺎﻟﻠَّﻪِ ﻭَﺭَﺳُﻮﻟِﻪِ ﺛُﻢَّ ﻟَﻢْ ﻳَﺮْﺗَﺎﺑُﻮﺍ ﻭَﺟَﺎﻫَﺪُﻭﺍ ﺑِﺄَﻣْﻮَﺍﻟِﻬِﻢْ ﻭَﺃَﻧْﻔُﺴِﻬِﻢْ
ﻓِﻲ ﺳَﺒِﻴﻞِ ﺍﻟﻠَّﻪِ ﺃُﻭﻟَﺌِﻚَ ﻫُﻢُ ﺍﻟﺼَّﺎﺩِﻗُﻮﻥَ
ﺍﻟﺤﺠﺮﺍﺕ: ١٥
({እዉነተኞቹ} ምእመናን እነዚያ በአላህና በመልእክተኛዉ ያመኑት ከዚያም
ያልተጠረጠሩት ናቸው) አል-ሑጁራት 15
የአላህ መልእክተኛም (ሰ.ዐ.ወ) ለአቡ ሑረይራ (ረዲየ አላሁ አንሁ) እንዲህ
ብለውታል፡- ‹‹ ከዚህ አጥር በስተጀርባ የአላህን ብቸኛ አምላክነት ከልቡ
በእርግጠኝነት የሚመሰክር ሰው ብታገኝ በጀነት አበስረው፡፡›› ሙስሊም
ዘግበዉታል
3.መቀበል፡- የላኢላሀ ኢለላህን መልእክት (አላህን በብቸኝነት ማምለክን)
ከልብ መቀበልና ለሌላ አካል የሚከናወኑ አምልኮቶችን መተው ነው፡፡ ይህንን
ያልተቀበለ ግን አላህ ኩራተኛነታቸውን እና አለመቀበላቸው እንዲህ በማለት
ከገለፃቸው ሙሽሪኮች መደዳ ይሰለፋል፡፡
ﺇِﻧَّﻬُﻢْ ﻛَﺎﻧُﻮﺍ ﺇِﺫَﺍ ﻗِﻴﻞَ ﻟَﻬُﻢْ ﻟَﺎ ﺇِﻟَﻪَ ﺇِﻟَّﺎ ﺍﻟﻠَّﻪُ ﻳَﺴْﺘَﻜْﺒِﺮُﻭﻥَ
ﺍﻟﺼﺎﻓﺎﺕ: ٣٥ – ٣٦
(እነርሱ፤ ‹ከአላህ ሌላ አምልኮት የሚገባው ሆኖ የሚመለክ አምላክ የለም›
በተባሉ ጊዜ ይኮሩ ነበር፡፡ እኛ ለእብድ ባለቅኔ ብለን አማልክቶቻችንን የምንተው
ነን ይሉም ነበር፡፡) አልሷፋት 35-36
4.መታዘዝ፡- ይህ ማለት ‹‹ላ ኢላሀ ኢለላህ›› የሚለው የምስክርነት ቃል
ለሚያመላክታቸው ትዕዛዛትና ክልከላዎች ሙሉ ታዛዥ ተከታይና ተናናሽ መሆን
ነው፡፡ አላህ (ሱ.ወ) እንዲህ ይላል፡-
ﻭَﻣَﻦْ ﻳُﺴْﻠِﻢْ ﻭَﺟْﻬَﻪُ ﺇِﻟَﻰ ﺍﻟﻠَّﻪِ ﻭَﻫُﻮَ ﻣُﺤْﺴِﻦٌ ﻓَﻘَﺪِ ﺍﺳْﺘَﻤْﺴَﻚَ ﺑِﺎﻟْﻌُﺮْﻭَﺓِ ﺍﻟْﻮُﺛْﻘَﻰ ﻭَﺇِﻟَﻰ ﺍﻟﻠَّﻪِ
ﻋَﺎﻗِﺒَﺔُ ﺍﻟْﺄُﻣُﻮﺭِ
ﻟﻘﻤﺎﻥ : ٢٢
(እርሱ መልካም ሰሪ ሆኖ ፊቱን (በመታዘዝና በመተናነስ) ወደ አላህ የሚሰጥ
ሰው ጠንካራን ገመድ በእርግጥ ጨበጠ…)
ሉቅማን 22
5. እውነተኝነት፡- የላኢላሀ ኢለላህን የምስክርነት ቃል በሚሰጥበት ጊዜ
እውነተኛ መሆን ማለት ነው፡፡ የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ይላሉ
‹‹ማንኛውም ከልቡ በእውነተኛነት በአላህ ብቸኛ አምላክነትና በሙሐመድ
(ሰ.ዐ.ወ) መልዕክተኝነት የሚመሰክር ሰው አላህ ከእሳት እርም ይለዋል ››
ቡኻሪ ዘግበዉታል
6. መውደድ፡- ይህ ማለት ላኢላሀ ኢለላህ የሚለውን የምስክርነት ቃል ፣ አላህን
እንዲሁም አላህን በብቸኝነት የሚያመልኩትን የተውሂድ ሰዎችን መውደድ ነው፡፡
አላህ (ሱ.ወ) እንዲህ ይላል ፡-
( ﻭَﻣِﻦَ ﺍﻟﻨَّﺎﺱِ ﻣَﻦْ ﻳَﺘَّﺨِﺬُ ﻣِﻦْ ﺩُﻭﻥِ ﺍﻟﻠَّﻪِ ﺃَﻧْﺪَﺍﺩًﺍ ﻳُﺤِﺒُّﻮﻧَﻬُﻢْ ﻛَﺤُﺐِّ ﺍﻟﻠَّﻪِ ﻭَﺍﻟَّﺬِﻳﻦَ ﺁﻣَﻨُﻮﺍ ﺃَﺷَﺪُّ
ﺣُﺒًّﺎ ﻟِﻠَّﻪِ
ﺍﻟﺒﻘﺮﺓ: ١٦٥
(ከሰዎችም አላህን እንደሚወዱ የሚወዷቸው ኾነው ከአላህ ሌላ ባለንጣዎችን
(ጣዖታትን) የሚይዙ አሉ፡፡ እነዚያ ያመኑትም አላህን በመውደድ (ከነርሱ)
ይበልጥ የበረቱ ናቸው) አል በቀራህ 165
7. ማጥራት፡- ይህም ማለት የላኢላሀ ኢለላህን የምስክርነት ቃል የሰጠ ሰው
ስራውን ከሽርክ ማጥራት አለበት፡፡ እንዲሁም በዚህ የምስክርነት ቃል የዱንያ
ጥቅማጥቅሞችን ከመከጀል፣ ከይዩልኝ እና ይስሙልኝ መጥራት አለበት፡፡
የአላህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል ‹‹የቂያማ ዕለት የኔን ምልጃ
በማግኘት ዕድለኛ የሚሆነው ላ ኢላሀ ኢለላህን ከልቡ ያለ ሰው ነው፡፡›› ቡኻሪ
ዘግበዉታል
 
ከዚህዉ የተኮረጀ ነዉ
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.
🔶የወሊድ መከላከያ(contraceptive) መጠቀም?🔶
 
👉ጠያቂው ይላል፦ባልና ሚስት የወሊድ መከላከያ(contraceptive)ለመጠቀም ቢስማሙ ይህም ሚስትየው ስለታመመች ሳይሆን አራት ልጆች ብቻ እንዲኖራቸው በመስማማታቸው ነው።ህልማቸውም ተሳክቶ ከዚያ በኋላ ሚስት ከባሏ በመስማማት መከላከያውን ተጠቀመች።የዚህ ነገር ፍርዱ ምንድነው?እናም ባል ሳይስማማ ብትጠቀመውስ ፍርዱ ምንድነው?በዚህ ላይ ወንጀል እና ሸሪዓን መፃረር አለበትን?
 
👉ሸይኽ ኢብኑ ዑثይሚን(رحمه الله) ሚስት ያለ ባሏ ፈቃድ የወሊድ መከላከያ መውሰዷ በሷ ላይ ሀራም ነው።ምክንያቱም ለባሏም በልጆቹ ጉዳይ ሐቅ አለውና።ከሰዎች ብዙዎቹ(በዋነኝነት)ሚዘወጁት ልጆችን ፍለጋ እንጂ ለሌላ አይደለም።መከላከያውን በባሏ ፈቃድ መውሰዷን በተመለከተ እዚያ ላይ ሀጃ ያለባት ከሆነ-እርግዝናው ከተከታተለ ይህችን ሴት ሚያደክማትና ሚከብዳት ከሆነ በተለይም ቶሎ ቶሎ ከሚያረግዙት ከሆነች የዛኔ በባሏ ፈቃድ መጠቀሟ ችግር የለበትም።ነገር ግን እዛላይ ሚጣራ ነገርና(እንድትጠቀም በቂ ምክንያት)እና ሀጃ ከሌለ ልትጠቀም አይገባም።ምክንያቱም ይህ ነገር ሸሪዓችን ልጆችን ከማብዛት አንፃር ተፈላጊ የሆነውን ነገር ስለሚጋፋ ነው።ልጆችን ማብዛት ተፈላጊ እና የተጠበቀ ጉዳይም ጭምር ነው-ከኡማው ልቅእና ነው።አላህ(سبحانه وتعالى)በርግጥም በኢስራኢል ልጆች ላይ እንዲህ በማለት ተመፃድቋል(በፀጋው አስታውሷቸዋል)"ከነገድም የበዛችሁ አደረግናችሁ"(አል-ዒስራእ:6)እንዲሁም ነብዪሏሂ ሹዐይብም(عليه السلام)ህዝቦቹን እንዲህ በማለት አስታውሷቸዋል"ጥቂጦችም በነበራችሁና በበዛችሁ ጊዜ አስታውሱ"(አል-አዕራፍ:86)ነብያችንም(عليه الصلاة والسلام)የቂያም እለት በኡማቸው ብዛት በነብያቶች ይፎክሩባቸዋል(ይፎካከሩባቸዋል)።
 
ይህ ሰው(ባል)እና ሚስት አራት ልጆች ብቻ እንጂ ከዚያ በላይ የማይፈልጉ ሆነው የመስማማታቸው ሁኔታ ከነሱ የሆነ ስህተት ነው።እነዚህ አራቶቹም ልጆች ወይም ከፊሎቹ ሊሞቱ ይችላሉ።ሲቀጥል ማነው የልጆች ብዛት አራት ነው ያለው?።በል እንደውም ልጆች በበዙ ቁጥር በላጭ እና ለሰው ልጅ ልቅእና ነው ሚሆነው።አላህ(سبحانه وتعالى)በነዚህ ልጆች(ስበብ) መልካም ነገርን:በረከትን:እውቀትን እና በአላህ መንገድ መታገልን ሊያደርግ ይከጀላልና ከነሱ(ባልና ሚስት)ይህን(የልጆች ቁጥርን መገደብ)መተግበር አስፈላጊ አይደለም።
 
📖(ኑሩን ዐላ ኧድ-ደርብ)
 
📗ማጠቃለያ
🔹ድህነትን ፈርቶ የወሊድ መከላከያን መጠቀም አይቻልም-ስለሁሉም ሪዝቅ አላህ ቃል ገብቷልና።
🔹ከእርግዝና ጋር በተያያዘ በመደራረቡ ጉዳት ሚያመጣ ከሆነ እና በልጆቹም እድገት እና እንክብካቤ በማድረጉ ሂደት ችግር(non economical)ሚገጥም ከሆነ ብትጠቀም ችግር የለውም
🔹ምትጠቀመው መከላከያ እስከመጨረሻው መውለድን ሚያግድ መሆን የለበትም።ይልቁንም በሀጃዋ ያህል መሆን አለበት።
🔹በሀጃዋ ያህል ከሆነ ክኒንም(oral contraceptive) ይሁን IUD ወይም ሌላ አይነት መጠቀም ትችላለች።( ጎንዮሽ ጉዳትን ከግምት ውስጥ ማስገባት እንደተጠበቀ ይሆናል።)
Send as a message
Share on my page
Share in the group