umma1697982674 Profile Picture
UMMA TOKEN INVESTOR

About me

⭕️ إذا أردت أن تكون سلفيًا حقًا فعليك ... "إذا أردت أن تكون سلفيّاً حقًا، فعليك أن تدرس مذهب السلف بإتقان، وتعرفه ببصيرة، ثم تعمل به من غير غلو ومن غير تساهل. هذا هو منهج السلف الصحيح، أما مجرد الاد

Translation is not possible.

እስቲ በቅንነት አንብቡት

የባጃጅ ሾፌር ነኝ በየቀኑ ብዙ ዓይነት ሰዎችን አመላልሳለሁ ዛሬ በባጃጄ የጫንኩት ሰው ግን ለየት ያለ ነው በጣም ይንቀዠቀዣል ይወራጫል ያለ መቋረጥ ወደ ግራና ወደ ቀኝ ይመለከታል

በጣም ግራ ገባኝ ጥሩ የለበሰ፣ ጥሩ ቁመና ያለው ሰው ነው

አእምሮውን የሚያመውም ይመስላል "ወንጀለኛ ይሆንን? " ስልም

አሰብኩ ምን እንደሆነ እንዳልጠይቀውም ሆነ ውረድ እንዳልለው

ፈራሁት እኔ ለራሴ ያልተማርኩ ምስኪን ድሃ ነኝ፣ሌላ ነገር

ቢያመጣብኝስ ብዬ ዝም ብዬ መንዳት ቀጠልኩ

ረጅም መንገድ እንደተጓዝን ተሳፋሪዬ ከሆነ ሰው ጋር በስልክ ሲያወራ ጆሮዬን ሰጥቼ አዳመጥኩት ሚስቱ ሆስፒታል ውስጥ ናት በሞትና በህይወት መካከል ናት

ዶክተሮቹ ደም የሚለግስ ሰው እንዲያመጣ እንደነገሩት

በአስቸኳይ የደም ዓይነት " ኤ" ካላገኘች በጥቂት ሰዓታት ውስጥ

ልትሞት እንደምትችልና ተመሳሳይ ደም ማግኘት እንዳልቻለ፣

ነበር በጭንቀት የሚያወራው

አውርቶ እንደጨረሰ ፣እንባው በአይኑ ግጥም እንዳለ በመስታዎት

አየሁት አሳዘነኝ ስፈራ ስቸር

"ይቅርታ ጌታዬ፣ በአጋጣሚ ከወር በፊት የደም አይነቴን ተመርምሬ

ነበር የደሜ አይነት አንተ የምትፈልገው "ኤ" ነው ቅር የማይልህ

ከሆነ ለባለቤትህ ደም ለመለገስ ፈቃደኛ ነኝ…" አልኩት

ዝም አለኝ ዝም ብሎ ፍጥጥ ብሎ ተመለከተኝ ደነገጥኩ እንደ

መርበትበት አልኩና… "ደሜ ንፁህ ነው፣ ምንም አይነት ሱስ

የለብኝም ከድህነቴ በስተቀር ምንም አይነት ወንጀልም

የለብኝም…"በማለት ቀባጠርኩ

ዝም ያለው በመገረም ነበረ አመስግኖኝ ወደ ሆስፒታል በፍጥነት

ተጓዝን

ደሜን ሰጠሁ አጠቃላይ ስራው 2 ሰዓት ፈጀ

በህይወቴ ለመጀመሪያ ጊዜ ከፍተኛ ደስታ ተሰማኝ ድሃ

ብሆንም ጠቃሚ ሰው እንደሆንኩ አሰብኩ የኔ ደም ልክ

እንደማንኛውም ሰው ደም እንደሆነ ተረዳሁ የኔ የድሃው ደም

የሃብታምን ህይወት ከሞት መታደግ እንደሚችል ተገለጠልኝ

በጣምምምም ደስስስ አለኝ

ሰውዬው ደሜን የሸጥኩ አይነት ስሜት እንዳይሰማኝ ብሎ ነው

መሰል "ገንዘብ ልስጥህ" አላለኝም እኔም ገንዘብ ሊሰጠኝ

ባለመሞከሩ በልቤ አመሰገንኩት

ደጋግሞ አመሰገነኝ አድራሻ ተለዋውጠን ተለያየን።

ደስ እያለኝ ድሃ ብሆንም ጠቃሚ ሰው መሆኔን እያሰብኩ ወደ

ስራዬ አመራሁ

ይህ አጋጣሚ ለእኔ ቢጤ ደሀዎች ራሳቸውን ዝቅ አድርገው

ለሚያዩት ትልቅ ምሳሌ ነው…

ጠቃሚ ናችሁ ! ቀና ብላችሁ ተራመዱ ! በርትታችሁ ስሩ! ደማችን

ከሃብታሞቹ ደም ጋር አንድ ነው የድሀ ደም የሃብታምን ህይወት

ከሞት ሊታደግ ይችላል።

#ሼርርርር

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

ከአላህ ጋር ነግዶ ማን ከሰረ?!

(እውነተኛ ድንቅ ታሪክ)

💎💎💎💎💎💎💎💎💎

Mahi Mahisho

🔹🔹🔹🔹🔹

በሰባዎቹ መጀመሪያ በሀገረ ግብፅ ግዛት ተፈህና አል-አሽረፍ በምትሰኝ ትንሽዬ መንደር ውስጥ ምንም የሌለው ደሀ የግብርና መሃንዲስ ጣራዋ በተቀደደ፣ ግርግዳዋ በተፈረፈረ ደሳሳ የጭቃ ቤት ውስጥ ከወላጆቹ ጋር ጎጆውን ቀልሶ ይኖር ይዟል። ግርግዳው በጋዜጣ የተሸፈነ ቤት!! በወላጆቹ ልፋት ተምሮ ለወግ ማዕረግ በቅቶ ቢመረቅም ስራ ማግኘት ግን አልተቻለውም። ሰላህ አጢያ ይሰኛል። ያረጀ እንጂ አዲስ ልብስ ለብሶ አያውቅም። ትክክለኛው የጫማ ቁጥር 42 ቢሆንም ከቆሻሻ ገንዳ ያገኛትን 44 ቁጥር ጫማ እንዳታልቅበት በቀስታ እየረገጠ ይጓዝባታል።

በግብርና ፋኩሊቲ ተመርቀው በከፋ ድህነት የሚሰቃዩ፣ ስራ ለመጀመር የሚፈልጉ ዘጠኝ የመንደራቸውን ሰዎች ሰብስቦ አነስተኛ ፕሮጀክት ለመጀመር ወሰነ። አማከራቸው ተስማሙ። አስረኛ አጋር እየፈለጉ እያንዳንዳቸው 200 የግብፅ ፓውንድ አዘጋጅተው ጠበቁ።

ተሰብስበው ሻይ እየጠጡ ወደነበሩት አጋሮቹ ዘንድ አቀናና "አስረኛውን አጋር አግኝቻለሁ" አላቸው።

"ማን እነደሆነ ንገረን" ሲሉ ጠየቁ

"አላህ ነው" በማለት መለሰላቸው። "ገንዘባችንን ከአደጋ ለመጠበቅ፣ ኃብታችንን ለማፋፋት እርሱ አንደኛው አጋራችን ይሆናል" በማለት ንግግሩን አከለ። ሁሉም ተስማሙ።

በጋራ የተቋቋመው የህብረት ኩባኒያ ውሉ ፀድቆ "አስረኛው ባለድርሻ አላህ የትርፉን አንድ አስረኛ ይወስዳል" የሚለው ቃል ከውሉ ወረቀት ላይ ሰፍሮ ሁላቸውም ፊርማቸውን አኖሩ። እውነተኛ የህብረት ስራ፣ ግልፅ ስምምነት ተደረገ።

የፕሮጀክቱ የመጀመሪያ ዙር ውጤት ጥሩ ትርፍና የተለየ ምርት ማስተናገዱን ሲመለከቱ ለተገኘው ትርፍ ለአላህ ምስጋና ይሆን ዘንድ የምርት ዑደት ውጤቱን "የታላቁ አጋር ድርሻ" በሚል መጠኑን ለመጨመር የአላህን ድርሻ ወደ 20% ለማሳደግ ወሰኑ። በየአመቱ ከፍ እያለ የአላህ ድርሻ 50% ደረሰ። አርሰው ቡቃያውን ወቅተው ምርቱን ይሸጣሉ። ነግደው ካተረፉት የአላህን ድርሻ ሳያጓድሉ ሀቁን ጠብቀው ትክክለኛ ቦታ ላይ ያውላሉ።

መስጂዶች፣ የሴቶች ሒፍዝ ማዕከል የአይታሞች ማደርያ የአቅመ ደካሞች መመገብያ ተቋማትን በአላህ ድርሻ ገነቡ። ትርፉ እያደገ ሲመጣ ለመሳኪኖች የዕርዳታ ድርጅትን አቋቋሙ..

በግብፅ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በአንድ ትንሽዬ መንደር ውስጥ ደረጃቸውን የጠበቁ አራት ኮሌጆችን ገነቡ። እያንዳዳቸው ለ600 ተማሪዎች የሚሆን ማደርያ 1000 ተማሪዎችን የሚያስተናግዱ ኮሌጆች!

ማንኛውም የኮሌጁ ተማሪ ወደ ቀዬው ለመሄድ ሲፈልግ ነፃ ትኬት ማግኘት እንዲችል በይተል ማል የሚል ቢሮን አቋቋሙ።

በመንደሩ ደሃ እስኪጠፋ ተቋሙ ፋፋ። ኸይራቱ ወደ ጎረቤት መንደሮች ጭምር ዘለቀ። ስራ አጥ ወጣቶች ከድህነታቸው ተላቀው እንዲሰሩ ተመቻቸላቸው። ለጎረቤት ሀገራት አትክልቶችን ኤክስፖርት ማድረግ ጀመሩ። ምርት በሚሰበሰብበት ወቅት ለከተማዋ ነዋሪ ከትልቅ እስከ ትንሹ የአትክልት ከረጢት በስጦታ ይበረከትላቸው ገባ።

በረመዳን የመጀመሪያዎቹ ቀናት ኢፍጣር ተዘጋጅቶ ወንዶች በአደባባይ ሴቶች በየቤታቸው በፍቅር በአብሮነት ተሰብስበው ያፈጥራሉ። ወላጅ አልባ ሴቶች ለትዳር ሲደርሱ ወጪያቸው ተሸፍኖ ይዳራሉ።

ይህ ሁሉ በአላህ ድርሻ የሚሰራ መልካም ተግባር መሆኑ ያስገረማቸው መስራቾቹ የፕሮጀክቱ ባለቤትነት ወደ አላህ እንዲዞር ወሰኑ። እነርሱም የአላህ ሰራተኛ የረቢ አገልጋይ ሆኑ። ባለቤትነቱን ወደአላህ ሲያዞሩ "ትርፉ ሳይቋረጥ ድሆች ይጠቀሙ ዘንድ ጌታችን ሆይ አደራ!" የሚለውን ቃል ከውሉ ወረቀት ላይ አሰፈሩ።

አትራፊ ንግድ!!

መልካም ግብይይት!!

"አላህ ከምእምናን ነፍሶቻቸውንና ገንዘቦቻቸውን ጀነት ለእነሱ ብቻ ያላቸው በመኾን ገዛቸው" ይሉሀል ይህ ነው።

ኢንጂነር ሰላህ አጢያ በ70 አመታቸው በጉበት በሽታ ሲሰቃዩ ቆይተው እንደ አውሮጳውያን የዘመን ቀመር ጥር 11 ቀን 2016 ሩሐቸው ከጀሰዳቸው ተላቀቀች። ከግማሽ ሚሊዮን በላይ ህዝብ ጀናዛቸውን ሸኘ። እየተላቀሱ ጀሰዳቸውን ከለህዱ አሳረፉ። ልጅ አልነበራቸውም።

አላህ ከምህረቱ አጎናፅፎ ጀነተል ፊርደውሱን ይወፍቃቸው።

╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍

ምንጮቼ:-

- الشيخ خالد الجندي ينعي صلاح عطية نسخة محفوظة 25 فبراير 2020

- تفهنا الأشراف قرية بلا عاطل أو فقير نسخة محفوظة 17 مايو 2017

- صلاح عطية رجل أعمال تاجر مع الله نسخة محفوظة 12 مايو 2017 على موقع واي باك مشين

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

ሰባቱ የ‹‹ላ ኢላሀ ኢለላህ›› መስፈርቶች (ሸርጦች)

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩኅ ናበጣም አዛኝ በኾነዉ፦

1.ዕውቀት፡- ይህም ማለት የዚህ ቃል መልዕክት እና ቃሉ ዉድቅ

የሚያደርጋቸዉንና እና የሚያፀድቃቸውን ነገሮች ጠንቅቆ ማወቅ ማለት ነው፡፡

ለዚህም ማስረጃው ቀጣዩ የአላህ ቃል ነው፡፡

ﻭَﻟَﺎ ﻳَﻤْﻠِﻚُ ﺍﻟَّﺬِﻳﻦَ ﻳَﺪْﻋُﻮﻥَ ﻣِﻦْ ﺩُﻭﻧِﻪِ ﺍﻟﺸَّﻔَﺎﻋَﺔَ ﺇِﻟَّﺎ ﻣَﻦْ ﺷَﻬِﺪَ ﺑِﺎﻟْﺤَﻖِّ ﻭَﻫُﻢْ ﻳَﻌْﻠَﻤُﻮﻥَ

ﺍﻟﺰﺧﺮﻑ : ٨٦

(እነዚያም ከአላህ ሌላ የሚያመልኳቸዉ እነሱ የሚያውቁ ሆነው በእውነት

ከመሰከሩት በስተቀር ምልጃን አይችሉም) አል-ዙኸሩፍ 86

2.እርግጠኛነት፡- በአላህ ብቸኛ አምላክነት ላይ ሙሉ በሙሉ እርግጠኛ መሆን

ነው፡፡አላህ (ሱ.ወ)እንዲህ ይላል፡-

ﺇِﻧَّﻤَﺎ ﺍﻟْﻤُﺆْﻣِﻨُﻮﻥَ ﺍﻟَّﺬِﻳﻦَ ﺁﻣَﻨُﻮﺍ ﺑِﺎﻟﻠَّﻪِ ﻭَﺭَﺳُﻮﻟِﻪِ ﺛُﻢَّ ﻟَﻢْ ﻳَﺮْﺗَﺎﺑُﻮﺍ ﻭَﺟَﺎﻫَﺪُﻭﺍ ﺑِﺄَﻣْﻮَﺍﻟِﻬِﻢْ ﻭَﺃَﻧْﻔُﺴِﻬِﻢْ

ﻓِﻲ ﺳَﺒِﻴﻞِ ﺍﻟﻠَّﻪِ ﺃُﻭﻟَﺌِﻚَ ﻫُﻢُ ﺍﻟﺼَّﺎﺩِﻗُﻮﻥَ

ﺍﻟﺤﺠﺮﺍﺕ: ١٥

({እዉነተኞቹ} ምእመናን እነዚያ በአላህና በመልእክተኛዉ ያመኑት ከዚያም

ያልተጠረጠሩት ናቸው) አል-ሑጁራት 15

የአላህ መልእክተኛም (ሰ.ዐ.ወ) ለአቡ ሑረይራ (ረዲየ አላሁ አንሁ) እንዲህ

ብለውታል፡- ‹‹ ከዚህ አጥር በስተጀርባ የአላህን ብቸኛ አምላክነት ከልቡ

በእርግጠኝነት የሚመሰክር ሰው ብታገኝ በጀነት አበስረው፡፡›› ሙስሊም

ዘግበዉታል

3.መቀበል፡- የላኢላሀ ኢለላህን መልእክት (አላህን በብቸኝነት ማምለክን)

ከልብ መቀበልና ለሌላ አካል የሚከናወኑ አምልኮቶችን መተው ነው፡፡ ይህንን

ያልተቀበለ ግን አላህ ኩራተኛነታቸውን እና አለመቀበላቸው እንዲህ በማለት

ከገለፃቸው ሙሽሪኮች መደዳ ይሰለፋል፡፡

ﺇِﻧَّﻬُﻢْ ﻛَﺎﻧُﻮﺍ ﺇِﺫَﺍ ﻗِﻴﻞَ ﻟَﻬُﻢْ ﻟَﺎ ﺇِﻟَﻪَ ﺇِﻟَّﺎ ﺍﻟﻠَّﻪُ ﻳَﺴْﺘَﻜْﺒِﺮُﻭﻥَ

ﺍﻟﺼﺎﻓﺎﺕ: ٣٥ – ٣٦

(እነርሱ፤ ‹ከአላህ ሌላ አምልኮት የሚገባው ሆኖ የሚመለክ አምላክ የለም›

በተባሉ ጊዜ ይኮሩ ነበር፡፡ እኛ ለእብድ ባለቅኔ ብለን አማልክቶቻችንን የምንተው

ነን ይሉም ነበር፡፡) አልሷፋት 35-36

4.መታዘዝ፡- ይህ ማለት ‹‹ላ ኢላሀ ኢለላህ›› የሚለው የምስክርነት ቃል

ለሚያመላክታቸው ትዕዛዛትና ክልከላዎች ሙሉ ታዛዥ ተከታይና ተናናሽ መሆን

ነው፡፡ አላህ (ሱ.ወ) እንዲህ ይላል፡-

ﻭَﻣَﻦْ ﻳُﺴْﻠِﻢْ ﻭَﺟْﻬَﻪُ ﺇِﻟَﻰ ﺍﻟﻠَّﻪِ ﻭَﻫُﻮَ ﻣُﺤْﺴِﻦٌ ﻓَﻘَﺪِ ﺍﺳْﺘَﻤْﺴَﻚَ ﺑِﺎﻟْﻌُﺮْﻭَﺓِ ﺍﻟْﻮُﺛْﻘَﻰ ﻭَﺇِﻟَﻰ ﺍﻟﻠَّﻪِ

ﻋَﺎﻗِﺒَﺔُ ﺍﻟْﺄُﻣُﻮﺭِ

ﻟﻘﻤﺎﻥ : ٢٢

(እርሱ መልካም ሰሪ ሆኖ ፊቱን (በመታዘዝና በመተናነስ) ወደ አላህ የሚሰጥ

ሰው ጠንካራን ገመድ በእርግጥ ጨበጠ…)

ሉቅማን 22

5. እውነተኝነት፡- የላኢላሀ ኢለላህን የምስክርነት ቃል በሚሰጥበት ጊዜ

እውነተኛ መሆን ማለት ነው፡፡ የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ይላሉ

‹‹ማንኛውም ከልቡ በእውነተኛነት በአላህ ብቸኛ አምላክነትና በሙሐመድ

(ሰ.ዐ.ወ) መልዕክተኝነት የሚመሰክር ሰው አላህ ከእሳት እርም ይለዋል ››

ቡኻሪ ዘግበዉታል

6. መውደድ፡- ይህ ማለት ላኢላሀ ኢለላህ የሚለውን የምስክርነት ቃል ፣ አላህን

እንዲሁም አላህን በብቸኝነት የሚያመልኩትን የተውሂድ ሰዎችን መውደድ ነው፡፡

አላህ (ሱ.ወ) እንዲህ ይላል ፡-

( ﻭَﻣِﻦَ ﺍﻟﻨَّﺎﺱِ ﻣَﻦْ ﻳَﺘَّﺨِﺬُ ﻣِﻦْ ﺩُﻭﻥِ ﺍﻟﻠَّﻪِ ﺃَﻧْﺪَﺍﺩًﺍ ﻳُﺤِﺒُّﻮﻧَﻬُﻢْ ﻛَﺤُﺐِّ ﺍﻟﻠَّﻪِ ﻭَﺍﻟَّﺬِﻳﻦَ ﺁﻣَﻨُﻮﺍ ﺃَﺷَﺪُّ

ﺣُﺒًّﺎ ﻟِﻠَّﻪِ

ﺍﻟﺒﻘﺮﺓ: ١٦٥

(ከሰዎችም አላህን እንደሚወዱ የሚወዷቸው ኾነው ከአላህ ሌላ ባለንጣዎችን

(ጣዖታትን) የሚይዙ አሉ፡፡ እነዚያ ያመኑትም አላህን በመውደድ (ከነርሱ)

ይበልጥ የበረቱ ናቸው) አል በቀራህ 165

7. ማጥራት፡- ይህም ማለት የላኢላሀ ኢለላህን የምስክርነት ቃል የሰጠ ሰው

ስራውን ከሽርክ ማጥራት አለበት፡፡ እንዲሁም በዚህ የምስክርነት ቃል የዱንያ

ጥቅማጥቅሞችን ከመከጀል፣ ከይዩልኝ እና ይስሙልኝ መጥራት አለበት፡፡

የአላህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል ‹‹የቂያማ ዕለት የኔን ምልጃ

በማግኘት ዕድለኛ የሚሆነው ላ ኢላሀ ኢለላህን ከልቡ ያለ ሰው ነው፡፡›› ቡኻሪ

ዘግበዉታል

ከዚህዉ የተኮረጀ ነዉ

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

" ከምድርም ውስጥ ከምድርም በላይ በፍርስራሾችም ሆነን ሴንቲሜትር በሴንቲሜትር እየተፋለምን ነው "

ይላል የአሁኑ የሀማስ ቃል አቀባይ የአቡ ኡበይዳ መግለጫ !

ይህ የሙጃሂዶቹ ወግ ነው ። እነርሱ ሲያወጉ ወጋቸው ከምድር ይከብዳል ልባቸው እንደዚያ ነውና ! በእሳት ውስጥ ሆነው እሳት የማይፈሩ ፤ የመሳሪያ ዝናብ እየዘነበባቸው በዝናቡ ውስጥ ጠላትን እያሳደዱ የሚያጋዩት እነርሱ ፍረሀት የት እንዳለ እንኳ አያውቁም !

በዚህች 48 ሰአት ውስጥ 160 የእስራኤል ታንኮችንና ወታደራዊ ተሽከርካሪዎችን ሙሉ በሙሉና በከፊል ማውደም የቻሉት እነርሱ ትንግርት ናቸው ! ተነግረው የማያልቁ ትንግርተኞች ! ቃላት ሰነጣጥቀህ ብትገጣጥም የማትገልፃቸው ጀብደኞች !

በ 160 ታንክና ተሽከርካሪ ውስጥ ስንት አረመኔ ደም ጠጭ የወራሪዋ ሀገር ወታደር አብሮ ሊደመሰስ እንደሚችል አስቡት !

እስራኤል ሰቅጣጭ የአየር ድብደባ ባደረገች ቁጥር ከፍተኛ ምት እየተመታች እንደሆነ እወቁት ። የእስራኤል ታንኮች ተቸግረዋል ። ከመሬት ውስጥ ሆነው የሚጠብቋቸው የሙጃሂዶች በትር እያረፈባቸው እየተበታተኑ ነውና ። ስለዚህ ያው እስራኤል ዋነኛ መምቻዋ የአሜሪካ ጦርጄቶች ናቸው ።

ትንቅንቁ ቀጥሏል !

በሀቅና በባጢል መካከል የሚደረገው ጦርነት ተፋፍሞ ቀጥሏል !

የዳውድና የጃሉት ጦርነት !

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

🔶የወሊድ መከላከያ(contraceptive) መጠቀም?🔶

👉ጠያቂው ይላል፦ባልና ሚስት የወሊድ መከላከያ(contraceptive)ለመጠቀም ቢስማሙ ይህም ሚስትየው ስለታመመች ሳይሆን አራት ልጆች ብቻ እንዲኖራቸው በመስማማታቸው ነው።ህልማቸውም ተሳክቶ ከዚያ በኋላ ሚስት ከባሏ በመስማማት መከላከያውን ተጠቀመች።የዚህ ነገር ፍርዱ ምንድነው?እናም ባል ሳይስማማ ብትጠቀመውስ ፍርዱ ምንድነው?በዚህ ላይ ወንጀል እና ሸሪዓን መፃረር አለበትን?

👉ሸይኽ ኢብኑ ዑثይሚን(رحمه الله) ሚስት ያለ ባሏ ፈቃድ የወሊድ መከላከያ መውሰዷ በሷ ላይ ሀራም ነው።ምክንያቱም ለባሏም በልጆቹ ጉዳይ ሐቅ አለውና።ከሰዎች ብዙዎቹ(በዋነኝነት)ሚዘወጁት ልጆችን ፍለጋ እንጂ ለሌላ አይደለም።መከላከያውን በባሏ ፈቃድ መውሰዷን በተመለከተ እዚያ ላይ ሀጃ ያለባት ከሆነ-እርግዝናው ከተከታተለ ይህችን ሴት ሚያደክማትና ሚከብዳት ከሆነ በተለይም ቶሎ ቶሎ ከሚያረግዙት ከሆነች የዛኔ በባሏ ፈቃድ መጠቀሟ ችግር የለበትም።ነገር ግን እዛላይ ሚጣራ ነገርና(እንድትጠቀም በቂ ምክንያት)እና ሀጃ ከሌለ ልትጠቀም አይገባም።ምክንያቱም ይህ ነገር ሸሪዓችን ልጆችን ከማብዛት አንፃር ተፈላጊ የሆነውን ነገር ስለሚጋፋ ነው።ልጆችን ማብዛት ተፈላጊ እና የተጠበቀ ጉዳይም ጭምር ነው-ከኡማው ልቅእና ነው።አላህ(سبحانه وتعالى)በርግጥም በኢስራኢል ልጆች ላይ እንዲህ በማለት ተመፃድቋል(በፀጋው አስታውሷቸዋል)"ከነገድም የበዛችሁ አደረግናችሁ"(አል-ዒስራእ:6)እንዲሁም ነብዪሏሂ ሹዐይብም(عليه السلام)ህዝቦቹን እንዲህ በማለት አስታውሷቸዋል"ጥቂጦችም በነበራችሁና በበዛችሁ ጊዜ አስታውሱ"(አል-አዕራፍ:86)ነብያችንም(عليه الصلاة والسلام)የቂያም እለት በኡማቸው ብዛት በነብያቶች ይፎክሩባቸዋል(ይፎካከሩባቸዋል)።

ይህ ሰው(ባል)እና ሚስት አራት ልጆች ብቻ እንጂ ከዚያ በላይ የማይፈልጉ ሆነው የመስማማታቸው ሁኔታ ከነሱ የሆነ ስህተት ነው።እነዚህ አራቶቹም ልጆች ወይም ከፊሎቹ ሊሞቱ ይችላሉ።ሲቀጥል ማነው የልጆች ብዛት አራት ነው ያለው?።በል እንደውም ልጆች በበዙ ቁጥር በላጭ እና ለሰው ልጅ ልቅእና ነው ሚሆነው።አላህ(سبحانه وتعالى)በነዚህ ልጆች(ስበብ) መልካም ነገርን:በረከትን:እውቀትን እና በአላህ መንገድ መታገልን ሊያደርግ ይከጀላልና ከነሱ(ባልና ሚስት)ይህን(የልጆች ቁጥርን መገደብ)መተግበር አስፈላጊ አይደለም።

📖(ኑሩን ዐላ ኧድ-ደርብ)

📗ማጠቃለያ

🔹ድህነትን ፈርቶ የወሊድ መከላከያን መጠቀም አይቻልም-ስለሁሉም ሪዝቅ አላህ ቃል ገብቷልና።

🔹ከእርግዝና ጋር በተያያዘ በመደራረቡ ጉዳት ሚያመጣ ከሆነ እና በልጆቹም እድገት እና እንክብካቤ በማድረጉ ሂደት ችግር(non economical)ሚገጥም ከሆነ ብትጠቀም ችግር የለውም

🔹ምትጠቀመው መከላከያ እስከመጨረሻው መውለድን ሚያግድ መሆን የለበትም።ይልቁንም በሀጃዋ ያህል መሆን አለበት።

🔹በሀጃዋ ያህል ከሆነ ክኒንም(oral contraceptive) ይሁን IUD ወይም ሌላ አይነት መጠቀም ትችላለች።( ጎንዮሽ ጉዳትን ከግምት ውስጥ ማስገባት እንደተጠበቀ ይሆናል።)

Send as a message
Share on my page
Share in the group