UMMA TOKEN INVESTOR

About me

كن التغير الذي تريد أن تراه في العالم 🕌🕌🕌 🔹በመላው ዓለም የሙሐመድ ትውልድ እግሩ በረገጠበት ሁሉ ሙስሊሙን የሚመለከቱ ክስተቶችን ለማድረስ እና ዓለም አቀፉን የሀይል አሰላለፍ ከሙስሊሙ ዓለም ነባራዊ ዱኒያዊ እውነታ አንፃር ለመዳሰስ ያለመ የሁሉም የሙሐመድ ትውልድ ገፅ ነው፡፡

Followings
0
No followings
Translation is not possible.

♻️ 🔻🇵🇸⚡️🇮🇱 የእስራኤል ወራሪ ጦር ትናንት በጋዛ ሰርጥ ሰሜን እና ደቡብ በደረሱ ሁለት የተለያዩ ጥቃቶች 11 አሸባሪ ወታደሮቹ መገደላቸውን እንዲሁም ዛሬ ሌላ 1 ተጨማሪ ወታደሩ መሞቱን አስታውቋል።

ቴሌግራም https://t.me/Alif_Online_Official

ኡማላይፍ የሙሐመድ ትውልድ ገፆችን ፎሎው ያድርጉ

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

🔻 ♻️ 🔻 🇾🇪🇮🇶🏴‍☠️⚡️ #ሰበር

የየመን ጦር ኃይል ከኢራቅ እስላማዊ ተቃውሞ ጋር በመተባበር ሁለት የጋራ ወታደራዊ ዘመቻዎችን መተግበሩን አስታወቀ።

🔴 የመጀመሪያው ኦፕሬሽን በአሽዶድ ከተማ ወሳኝ የጠላት ይዞታዎችን ኢላማ ያደረገበት ሲሆን ሌላኛው ደግሞ በሃይፋ ከተማ በተመሳሳይ ወሳኝ ይዞታን ኢላማ ያደረገ ጥቃት የፈፀመበት ነው።

🔴 በቀይ ባህር ላይ (TUTOR) የተባለችው ዕቃ ጫኝ መርከብ ላይ ኢላማ ያደረገበትን ሁለተኛውን ዘመቻ ያካሄደ ሲሆን መርከቧን በባለቤትነት የተያዘው ኩባንያ ወደ ፍልስጤም ወደቦች እንዳይገባ የተላለፈውን ክልከላ ተከትሎ የተፈፀመ ጥቃት መሆኑንም ጦሩ አስታውቋል።

በሙስሊሙ ዓለም የተፈጠሩ ሁሉንም አዳዲስ መረጃዎች በተለይም በወቅታዊ የፍልስጤም ጉዳይ እውነተኛ እና ሚዛናዊ መረጃ ለማግኘት

ቴሌግራም https://t.me/Alif_Online_Official

ኡማላይፍ የሙሐመድ ትውልድ ገፆችን ፎሎው ያድርጉ

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

♻️ 🔻⚫️ የሰራያ አል ቁድስ ወታደራዊ ቃል አቀባይ አቡ ሀምዛ ዛሬ ባደረጉት ንግግር፡-

- ወንጀለኛው ጽዮናዊ አካል ባልታጠቁ ሰዎች ላይ አጠቃላይ የዘር ማጥፋት ወንጀል እየፈጸመ ነው።

- ለ \"እስራኤላዊያን\" እንናገራለን: - መንግስታችሁን አትስሙ; ወደ ሰፈራዎቻችሁ መመለስ የምትችሉት በጋዛ ላይ ያለውን ጦርነት በማቆም ብቻ ነው።

- ሰራያ አል ቁድስ ከተቃውሞ እጋሮቹ ጋር ጎን ለጎን በዌስት ባንክ እና በጋዛ የህልውና ጦርነት እያካሄደ ነው።

- ባለፉት ሳምንታት በሁሉም የወረራ ቦታዎች ላይ የጠላት ወታደሮችን እና አልሞ ተኳሾች ጭንቅላት ላይ ያነጣጠረ ብዙ የአልሞ መምታት ዘመቻ አድርገናል።

- በራፋህ፣ ጀባሊያ፣ አል-ዘይቱን እና በማዕከላዊ ጠቅላይ ግዛት ዳርቻ ላይ በደርዘን የሚቆጠሩ ተሽከርካሪዎችን በታንደም ላውንቼር፣ በከፍተኛ ፈንጂ በበርሜል ቦምቦች እና በአባቢል ተቀጣጣይ መሳሪያዎች ማውደማችንን እና ከጥቅም ውጪ ማድረጋችንን እናሳውቃለን።

- \"SkyLark\" \"Quadcopter\" እና ሌሎች የስለላ እና የስለላ አውሮፕላኖችን ጨምሮ 11 \"የእስራኤል\" አውሮፕላኖች በጋዛ ሰርጥ ውጊያ ውስጥ መትተን ጥለናል።

- በሊባኖስ፣ በሶሪያ እና በዌስት ባንክ ሸሂዶችን መክፈላችንን ቀጥለናል።

- በየቀኑ ማለት ይቻላል በራፋህ ፣ጃባሊያ እና “ኔትዛሪም” በደርዘን በሚቆጠሩ የሞርታር መሱሪያዎች እና ሮኬቶች በጠላት ሃይሎች እና ስብስቦቻቸው ላይ የምናደርገውን ጥቃት መቀጠላችንን እናሳውቃለን።

- ባለፉት ጥቂት ቀናት በጋዛ ድንበር   ቢር ሳቢ (ቤር-ሼባ), \"ስዴሮት\" እና አስቃላንን በሮኬት ደብድበናል እንዲሁም በተመሳሳይ ጊዜ በራፋህ ውስጥ ተስፋ የቆረጡ የጠላት ሃይሎችን እየተጋፈጥን ነው።

- የጠላት ምርኮኞችን ለመጠበቅ ውስብስብ የሆነ ውጊያ ላይ ነን።

- እስረኞችዎን ለማውጣት ብቸኛው መንገድ ከጋዛ መውጣት ፣ የእስረኞች ልውውጥ ስምምነትን ማካሄድ እና ጥቃቱን ማቆም ነው።

- አሁንም ጦራችን በጥሩ ሁኔታ ላይ መሆኑን ለጠላት እናረጋግጣለን።

- መጪው የጥፋት ሽብር ጠላት በውርደት ጋዛን ለቆ እንዲወጣ ያስገድዳል።

- በአል-አቅሳ ማዕበል ጦርነት የፈቃድ እና ግዙፍ መስዋእትነት ውጤቶች ቀስ በቀስ በፍልስጤም ጉዳይ ዙሪያ በተካሄደው አለም አቀፍ ሰልፍ ግልፅ እየሆኑ መጥተዋል።

- በየመን፣ ኢራቅ እና ሊባኖስ ላሉት የድጋፍ ግንባሮች በጠላት ሃይሎች ላይ ለሚያደርጉት የጥቃት ዘመቻ ሰላምታና ምስጋናችንን እናቀርባለን።

ቴሌግራም https://t.me/Alif_Online_Official

ኡማላይፍ የሙሐመድ ትውልድ

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

♻️🔻🟢 የአል-ቀሳም ብርጌድ ቃል አቀባይ አቡ ዑበይዳ:-

የእኛ ተዋጊዎች የጽዮናውያኑን ሃይል በጃባሊያ ካምፕ ውስጥ ከሚገኙት ዋሻዎች በአንዱ ውስጥ አስገብተው በዚሁ ዋሻ መግቢያ ላይ በተጠመደ ፈንጂ ጥቃት ፋጽመዋል።

ከዚያም ከዜሮ ርቀት ከዚህ ሃይል ጋር ቀጥተኛ ውጊያ በማድረግ እጅግ ስኬታማ ኦፕሬሺን አከናውነዋል።

ከዚያም ወታደሮቻችን ወደ ስፍራው የሚሮጡትን የማጠናከሪያ ሃይል አባላት በፈንጂ በማጥቃት በቀጥታ መተዋቸዋል።

ተዋጊዎቻችን በዚህ ኦፕሬሽን ጠላት ተታሎ የገባበትን ዋሻ ካፈነዱ በኋላ ሁሉም የዚህ ጠላት ሃይል አባላት እንዲገደሉ፣ እንዲቆስሉ እና እንዲማረኩ በማድረግ ወታደራዊ ቁሳቁሶቹን ከወሰዱ በኋላ ለቀው ወጥተዋል።

ወራሪው ሀይል የተያዙትን ሊያስለቅቅ ይቅርና ተጨማሪ ምርኮኛ ተጨምሮለታል።

አል-ቀሳም ብርጌድ ትላንት በርካቶችን ገድሎ ቀሪዎችን ማርኳል ለዚያም ነው በሐማስ ዋሻዎች ውስጥ መጠጋት የማያስፈልገው...

አለበለዚያ የሚሆነው በዚህ ቪዲዮ ላይ እንዳለው ከምድር በታች እየተጎተቱ መሄድ ነው።

ኦክቶበር 7 ከመሬት በላይ ጎትተዋቸው ነበር ትላንት ደግሞ ከመሬት በታች ጎትቷቸዋል።

አል ቀሳም ይፋ ካደረጋቸው የተማረኩ መሳሪያዎች አንዱ መሳሪያ የቼክ CZ Scorpion EVO 3 የተባለ ዘመናዊ መሳሪያ ነው (ቼክ መሳሪያ አቅራቢ መሆኔን ያዙልኝ)።

ይህ መሳሪያ በአብዛኛው ጥቅም ላይ የሚውለው በልዩ ወታደሮች በተለይም በባህር ሃይሎች ብቻ ነው! ስለዚህ ከተገደሉት እና ከተማረኩት ውስጥ  የባህር ኃይሉ ኮማንዶ ይገኝበታል ማለት ነው።

ተጨማሪ መረጃዎችን በቴልግም መከታተል ትችላላችሁ https://t.me/Alif_Online_Official

የሙሐመድ ትውልድ

18 views
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

♻️ 🔻 እስራኤል የራፋህ ዘመቻዋን እንድታቆም ፍርድ ቤቱ አዘዘ !

በአለም አቀፉ የፍትህ ፍርድ ቤት ደቡብ አፍሪካ በእስራኤል ላይ ያቀረበችውን እስቸኳይ ክስ ተከትሎ በሁለቱ አካላት መካከል ከተደረገው ክርክር በኋላ ዛሬ ፍርድ ቤቱ ብይን ሰጥቷል፡፡

የአለም አቀፉ የፍትህ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት እስራኤል በራፋህ ላይ የጀመረችው የመሬት ጥቃት አሁንም እንደቀጠለ እና ለሌላ መፈናቀል ምክንያት እንደሆነ ተናግረዋል፡፡

የአለም አቀፉ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት በመጋቢት ወር በፍርድ ቤቱ የፀደቁት ጊዜያዊ እርምጃዎች ለቅርብ ጊዜ ለውጦች ሙሉ ለሙሉ ምላሽ እንደማይሰጡ ተናግረዋል, ስለዚህም ለውጥ ያስፈልጋል ብለዋል፡፡

በዚህም የእስራኤል እና የፍልስጤም ጦርነትን በሚመለከት የተወሰዱትን ቀደምት ጊዜያዊ እርምጃዎችን ለመቀየር እና ተጨማሪ አዳዲስ ህጎችን ለመጨመር በደቡብ አፍሪካ የቀረበው ጥያቄ ትክክል ሆኖ አግኝተነዋል ብለዋል፡፡

ይሁን እንጂ በተቀረው የጋዛ ቋሚ የተኩስ አቁም ወይም ጦርነት ማቆምን በተመለከተ ምንም አይነት ውሳኔ አላሳለፈም።

የአለም አቀፉ ፍርድ ቤት ሃላፊ ነዋፍ ሰላም እስራኤል በራፋህ የምታደርገውን ጥቃት ለማስቆም ደቡብ አፍሪካ ባቀረበችው ጥያቄ ላይ ውሳኔ በሰጡበት ቅጽበት።

"እስራኤል በጋዛ የሚገኘውን የፍልስጤም ህዝብ አደጋ ላይ ሊጥል የሚችል በራፋ ግዛት ውስጥ የምታደርገውን ወታደራዊ ጥቃትም ሆነ ሌላ እርምጃዋን ሙሉ በሙሉም ሆነ በከፊል ማቆም አለባት።"

በተጨማሪም ፣ “ ያለ ምንም እንቅፋት ወደ ጋዛ ሰርጥ መግባትን ለማረጋገጥ ውጤታማ እርምጃዎችን መተግበር እና በማንኛውም የተባበሩት መንግስታት የሚመለከታቸው አካላት የዘር ማጥፋት ወንጀል እንዲመረምር፣ መረጃ ፍለጋ ተልዕኮ ወይም ምርመራ እንዲከናወን መፍቀድ አለባት ብለዋል።

ዓለም አቀፉ የፍትህ ፍርድ ቤት በ 13 ድጋፍ እና 2 ተቃውሞ እስራኤል በጋዛ የምታደርገውን ወታደራዊ ጥቃት በአስቸኳይ እንድታቆም አዟል።

ተጨማሪ መረጃዎችን በቴልግም መከታተል ትችላላችሁ https://t.me/Alif_Online_Official

የሙሐመድ ትውልድ

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group