UMMA TOKEN INVESTOR
Edit profile
About me

★Electrical and Computer Engineer from AAiT,AAU ★M. Sc Candidate in AI ★MA in Leadership ★Software Developer ★Programmer ★Former Memebership Coordinator @ESSS ★Ethical Hacker ★Founder and CEO

Translation is not possible.

የዓለም ህዝብ ግን አይገርምም⁉️

=======================

(ዓለም በዚህ ዘመን አይታው የማታውቀው የጦር ወንጀልና የዘር ጭፍጨፋ በጘዝ'ዛ)

||

✍ 365 km² ስፋት ባላት አነስተኛ ከተማ ውስጥ 2.3+ ሚሊዮን ዜጎች ተጠጋግተው ይኖሩባታል። በዚህች densely populated በሆነች ከተማ ላይ ለተከታታይ 3 ሳምንታት ያላባራ ከ12 ሺህ ቶን በላይ ቦምብ ሲዘንብ፤ በዚህም ሳቢያ፦

1) በትንሹ 7,028 የሚሆኑ ፈለስጢናዊ ሙስሊሞች ሲገደሉ፣

2) ከ70% በላይ የሚሆኑት ህፃናትና ሴቶች ሲሆኑ (2,913 ህፃናትና 1,709 ሴቶች)፣

3) 18,482 የሚሆኑት ለከፍተኛ የአካል ጉዳት ሲዳረጉ፣

4) ባለፉት 24 ሰዓታት ብቻ 481 የሚሆኑት ሲገደሉ (ከመካከላቸው 209 የሚሆኑት ህፃናት ናቸው።)፣

5) ከ1,650 በላይ የሚሆኑት ጀናዛቸው እንኳ ሳይገኝ እስካሁን ድረስ በቦምብ በፈራረሱት ህንፃዎች ስር ሲሆኑ (ከመካከላቸው 940 ህፃናት አሉበት።)፣

6) 731 የሚሆኑ ፈለስጢናዊ ሙሉ ቤተሰቦች ሲገደሉ፣

⑦) 101 የጤና ባለሙያዎች ሲገደሉና 100 የሚሆኑት ሲቆስሉ፣

⑧) 12 ሆስፒታሎችና 32 የጤና ማዕከላት በነዳጅ እጥረትና በቦምብ ጥቃት ከአገልግሎት ውጭ ሲሆኑ፣

9) በኢንኩቤተር ውስጥ የሚገኙ ከ130 በላይ የሚሆኑ ህፃናት ያሉበት ሆስፒታል ባጋጠመው በነዳጅ እጥረት ሳቢያ ነፍሳቸው በእንጥልጥል ላይ ሲገኝ፣

⑩) ከ1.5 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ ንጹሐን ከመኖሪያ ቤታቸው ተፈናቅለው በመጠለያ ካምፖች፣ በት/ቤቶች፣ በሆስፒታል ግቢዎች፣ በመስጂዶችና ቤተ ክርስቲያን ተጠልለው ሳለ በዛው ባሉበት ጥቃቱ ሲያገኛቸው…

(ከሰው ነፍስ አይበልጥምና ወደ አመድነት ስለተቀየሩት ውብ ህንፃዎችና መሠረተ ልማቶችማ አውርተን አንዘልቀውም።)

የሰለጠነ ተብዬው ዓለም አሁንም «ጦርነቱ ይቁም!» ከማለት ይልቅ «እስራኤል ራሷን የመከላከል መብት አላት፣ ሐማስ መጥፋቱን ማረጋገጥ አለባት፣ ከጎንሽ ነን፣ ሐማስ ሽብርተኛ ነው፣ በሐማስ ጥቃት ለሞቱተረ እስራኤላዊያን አዝነናል!…» እያሉ ነው።

ትንሽ አሻሻልን የሚሉት ደግሞ ጦርነቱ መቆም የለበትም፤ ግን የተወሰነች እርዳታ ይግባላቸው ይላሉ።

እስካሁን በጋዛ መብራት የለ፣ ውሃ የለ፣ ምግብ የለ፣ ነዳጅ የለ…። በዚህ የተነሳ የቆሰሉትና መደበኛ ህመም የሚታመሙትም መታከም አልቻሉም።

ዙሪያውን በከበባ ስለሆነ ለጠናበት ታማሚ የውጭ ሕክምና እንዲያገኝ ማድረግ አልተቻለም።

እስራኤል ከላይ በአየር ከምታዘንበው የቦምብ ዝናብ ባሻገር ከምግብና ውሃ እንዲሁም ከሕክምና ከልክላ በጅምላ ጭፍጨፋ የጦር ወንጀልና የዘር ማፅዳት ወንጀል በመፈጸም ላይ ትገኛለች። ይህ ሁሉ የሚሆነው ዓለም እያዬ በ21ኛው ክፍለ ዘመን ነው። ተመድ ተብዬውም ሆነ የትኛውም የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ነኝ የሚል ተቋም ሁሉ የውሃ ሽታ ሆኗል። የነርሱ ህግ እነርሱን ለማዳን እንጂ ለሌላው አይሠራም። እነርሱ ዘንድ የሙስሊም፣ የዓረብና የአፍሪካዊ ሞት ከውሻቸው ሞት በታች ነው።

ግን ነፍስ ሁሉ እኩል ናትና የእጃቸውን አንድ ቀን ማግኘት አይችሉም። ነገ ላይ በሌላ የነርሱ አካል ላይ ጥቃት ሲፈጸም በሚዲያቸውም ሆነ ባልተጻፈው ህጋቸው ከአጥናፍ እስከ አጥናፍ ሲለፍፉ እናገኛቸዋለን።

አላህ ውርደታቸውን ያቅርበው፤ ለተበዳዮች ነስሩን ያፍጥነው።

አላህ የአሸናፊዎች ሁሉ አሸናፊ የሆነ ጥበበኛና ታጋሽ ጌታ ነው። አንድ ቀን አይርላቸውም።

||

t.me/MuradTadesse

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

ህፃናትና ስልክ‼

============

✍ አንዳንድ ወላጆች ገና ጥቅምና ጉዳትን፣ ሐላልና ሐራምን ላልለዩ ለጋ ህፃናት ይጫዎቱበት ዘንድ ስልካቸውን ይሰጣሉ። ያውም ኢንተርኔት ከፍተው፣ ያውም ቲክቶክና መሰል ሚዲያዎች ላይ ቪድዮዎችን እንዲያዩ!

ይህ ተገቢ አይደለም። ከጥቅሙ ጉዳቱ ያመዝናል። ልጆች እናንተ ተመልከቱ ብላችሁ የከፈታችሁላቸውን ብቻ ሳይሆን ሌላም ነገር መጎርጎራቸው አይቀርም።

«ይሄ አያውቁም፣ ወደ ሌላ አይገቡም!…» የሚለውን ሽንገላችሁን ተውት። የዛሬ ልጆች ሳታስቡት ቀድመዋችሁ ሄደዋል። ት/ቤት አድርሳችኋቸው መጣችሁ እንጂ ጓደኞቻቸው እነማን እንደሆኑና ማን ጋር እንደሚውሉ አታውቁም።

ስልክ አትስጧቸው። በሐላሉ ዘና እንዲሉ ብላችሁ መስጠታችሁ አስፈላጊ መስሎ በታያችሁ ጊዜ ደግሞ ገደብ፣ ህግና ደንብ አብጁላቸው። ወይ በእናንተው ቁጥጥር ሆነው ወይም በሆነ ዘዴ ይመልከቱ።

አለበለዚያ ገና ከለጋነታቸው እናንተው ራሳችሁ በራሳችሁ ገንዘብ አበላሽታችኋቸው፤ ኋላ ሲጎለምሱ ልመልሳቸው ብትሉ እንኳ ከአቅማችሁ በላይ በሚሆንበት ደረጃ ላይ ሊደርሱ ይችላሉ።

ትልቅ ኃላፊነት አለባችሁ። በዚህ እድሚያቸው ቂርኣታቸውን መቅራት፣ ትምህርታቸውን ማጎበዝና በሌሎች በሚጠቅሟቸው ነገሮች እንዲጫዎቱ ማድረግ እንጂ ጧት ማታ የስልክ ሱሰኛ እንዲሆኑ ማድረግ የለባችሁም።

ውዱ ነቢይ ይህን ብለዋል፦

( كلُّكم راعٍ وكلُّكم مسؤولٌ عن رعيتِهِ…

والرجلُ راعٍ على أهلِ بيتِهِ…)

«ሁላችሁም ጠባቂዎች ናችሁ። ሁላችሁም ስለምትጠብቁት ነገር ትጠየቃላችሁ። … ወንድ (ባል) በቤተሰቡ ጉዳይ ጠባቂ ነው።»

[አል-ቡኻሪይ: 2554፥ 2409፣ ሙስሊም: 1829፣ አቡ ዳውድ: 2928፣ አ-ት'ቲርሚዚይ: 1705፣ አ-ን'ነሳኢይ: 9173፣ አሕመድ: 5167]

√ ሳይንሱ የሚለውንም ልጨምርላችሁ። አንድ ከ13–17 እድሜ ባላቸው ታዳጊዎች ላይ የተደረገ የ Pew Research Centre ሰርቬይ እንደሚጠቁመው ከሆነ፤ 44% ታዳጊዎች ከእንቅልፋቸው ወዲያው እንደነቁ ስልካቸውን ያያሉ።

ስልክ ማብዛታቸው ከሚያስከትልባቸው የጤና ችግሮች መካከል፤ የአንገትና የወገብ (ስፓይናል ኮርድ) ህመም፣ Teen Tendonitis (TTT)፣ የስልክ ሱሰኛ ስለሚሆኑ ያለ ስልክ ሲሆኑ ከፍተኛ የድብርት ስሜት ውስጥ መግባት፣ መጨናነቅ/ ስጋት (Anxiety) ፣ ውፍረት፣ ለካንሰር በሽታም ይዳርጋል የሚል አለ። ማለትም ለ acoustic neuroma ይዳርጋል። በርግጥ እስካሁን ኮንፊርም ባይደረግም ከስልኮች የሚመነጨው ጨረር (radiation) ከስልኩ ጋር የተነካካውን የሰውነታችን ክፍል (በተለይም እጅ፣ በተለይም ኢንተርኔት ሲከፈትና እጅ ላይ ስልኩ ሲሞቅ) DNAን የመጉዳት አቅም ሊኖረው ይችላል።

ሌላው ከባዱ ችግር የእይታ (የዓይን) ችግር ይፈጥራል። በተለይም ህፃናት ለጊዜው ተፅዕኖው ጎልቶ ባይታይባቸውም እድሚያቸው ሲጨምር ገና በጊዜ ዓይነ ስውር እንዳታደርጓቸው። የcell phone vision ምልክቶቹ stress, redness, burning sensation, blurred vision, and dry eyes ናቸው።

ተጨማሪ ፔፐሮችንና ጆርናሎችን ከፈለጋችሁ እነዚህን አንብቡ።

1) Cell Phones and Cancer Risk; National Cancer Institute

2) Aswitha Priya Sadagopan, et al.; Prevalence of Smartphone Users at Risk for Developing Cell Phone Vision Syndrome among College Students; Journal of Psychology & Psychotherapy (2017).

3) Sehar Shoukat; Cell phone addiction and psychological and physiological health in adolescents; EXCLI Journal (2019).

4) Amanda Lenhart, et al.; Teens and Mobile Phones; Pew Research Center (2010).

በአጭሩ ተጠንቀቁ። የጠቀማችኋቸው መስሏችሁ እንዳትጎዷቸው። ጭራሽ አንዳንዱ ወላጅማ ለራሳቸውም ስልክ ገዝቶ የሚሰጥ አለ። ልጁም «የኔ ጓደኞች ስልክ ይዘው እኔ ብቻ…» እያለ ያለቃቅሳል። ወላጅም የኔ ልጅ ከማን ያንሳል ብሎ ይገዛል። ተወው! አሁን ያልቅስ! ኋላ ዓይኑን አጥቶ ከሚያለቅስ! አሁን የጎዳኸው መስሎት ቢጠላህም ኋላ ሲገባህ ይወድሃል። በትህትና ለነርሱ ጥቅም ብላችሁ እንደሆነ የምትከለክሏቸው አብራሩላቸው። ግን እንዳልኳችሁ ከቴክ ነክ ነገር የራቁ በደዊይ እንዳይሆኑም ለትምህርት በሚሆን መልኩ በእናንተ ክትትል አሳዯቸው።

አላህ ያግዘን! ያግዛችሁ! በዲኑም በትምህርቱም ጠንካራ ልጅ እናፍራ።

||

ወንድማችሁ፦ ሙራድ ታደሰ

=========

ኖቬምበር 28, 2023 G.C.

||

t.me/MuradTadesse

https://ummalife.com/MuradTadesse

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

… ሰዓቲቱ አትቆምም‼

===============

✍ ውዱ ነቢይ ﷺ የቂያም ቀን የሰዓቲቱን መምጣት አመላካች የሆኑ ምልክቶችን በጠቀሱበት ሐዲሥ ላይ እንዲህ የሚል ይገኝበታል፦

(لا تَقومُ السَّاعةُ … وحَتَّى تَعودَ أرضُ العَرَبِ مُروجًا وأنهارًا )

«የዐረብ ምድር ወደ አረንጓደነትና ወንዞች ሳትቀየር ሰዓቲቱ አትቆምም።»

[ሙስሊም: 157]

*

የዚህን አካባቢ ምድረ በዳነት ዓይኔ አይቶብኛል። ጭራሽ እንዲህ ይሆናል ተብሎ የማይታሰበው ምድር አሁናዊ ገፅታዊ ይህ መሆኑን በፎቶ ሳይ… ያ አላህ ከማለት ውጭ ምን ይባላል!

ያ ረብ! ወደ አንተ መልካም መመለስን መልሰን‼

||

t.me/MuradTadesse

https://ummalife.com/MuradTadesse

image
image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

«ልጆቻችሁን ስለ ሶላት፣ ስለ ጾምና እስራኤልን ስለመዐጥላት አስተምሯቸው።»

በሃገረ ሞሮኮ የሚገኝ ታፔላ!

||

t.me/MuradTadesse

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

ሚስትነቱ ከቀረ ሙስሊም እህትህ መሆኗን አትዘንጋ‼

===================================

✍ ትዳር የእቃ እቃ ጫዎታ አይደለም። መፋታትን አስቦ ወደ ትዳር የሚገባ ያለ አይመስለኝም። በትዳር ውስጥ ኸይር ነገር ለማግኘት ታስቦና መልካም ዝርዮችን ለማፍራት ተብሎ በአላህ ላይ በመመካት ወደ ትዳር ይገባል። አላህ ከፈተና የጠበቀው ከገባበት በኋላ መልካም ነገርን ያገኛል። አላህ በጥበቡ ሲሻ ደግሞ ያልጠበቀው ነገር የሚያጋጥመው ይሆናል። አለፍ ሲልም ፊትና ይሆንበታል። በዚህ አይነት ሁኔታ ችግሩን በተቻለ መጠን መፍታት ካልተቻለ ሸሪዓው ፍቺን ፈቅዷል። ከዚያ ውጭ ግን በሆነ ባልሆነው ለትዳር የሚከፈልን መስዋዕትነት በመዘንጋትና ነፍስ ሳያውቁ እያገቡ መፋታት ጥሩ አይደለም።

የሚያሳዝነው ነገር በአሁኑ ወቅት ፍች በዝቷል። ከራሳቸው ጋር ሳይግባቡ ሲግባቡ የሚፋቱ ባለትዳሮች መብዛታቸው ላጤዎች ትዳርን ሆረር አድርገው እንዲያዩት ሆኖባቸዋል።

በተለይም ልጅ መውለድ ከተጀመረ በኋላ የሚፋቱ ባለትዳሮች ለልጆቻቸው እድገት ስቃይ እየሆኑ ነው። ከቤተሰቧ ተነጥላ ወደርሱ የሄደችን ሚስት ከቤተሰቧም አጋጭቶ እርሱም ሳያዋጣት ባዶ ቤት ጥሎ የሚጠፋ ባል በዝቷል። ጭራሽ እርጉዝ ናት የለ፣ አራስ ናት የለ፣ የያዘችው ህፃን ልጅ እንኳ የርሱ አብራክ ክፋይ የማይመስለው ስንትና ስንት ጨካኝ ወንድ አለ። አለመግባባት ሊኖር ይችላል። አለመግባባቱን በምክክርና አለፍ ሲል በሽምግልና መፍታት ካልተቻለ ፍቺ ይከተላል። ግን በደል መኖር የለበትም። ፍቺ ሲኖር ሚስትነቷ ቀረ እንጂ ሙስሊም እህትነቷ አልቀረም ሐቢቢ። ሴት ልጅ ከልብ ከወደደች የዋህ ስለሆነች ያልጠበቀችው ነገር ሲያጋጥማት ልቧ የማይጠገን ስብራት ሊያጋጥመው ይችላል፤ አለፍ ሲልም ራሷን ልትስት ትችላለች ለምትወስናቸው ነገሮች ሁሉ ቆም ብለህ አስብ።

ከቻልክ ኒያህን አጥርተህ በቻልከው ሁሉ ሐቋን በነጠበቅ ነገ አላህ ፊት በርሷ ሰበብ ምንዳ የምታገኝ መልካም ባል ሁን። መልካም ሰው ሁንላት። ካልቻልክ ግን ቢያንስ መጥፎ ባል ሆነህ በድለሃት በርሷ ሰበብ አላህ ፊት ከመጠየቅ ራስህን አድን። የምር ከልብህ ከገባህ፤ ለርሷ መልካም መሆንህ በዋናነት ጥቅሙ ከርሷ ይልቅ ላንተ ነው። ጀነት መግቢያ ሰበብህ እንጂ ከጀነት መከልከያህና ለእሳት መዳረጊያህ እንድትሆን አታድርግ።

ለምን? ውዱ ነቢያችን እንዲህ ብለውናል፦

(خيرُكُم خَيرُكُم لأَهْلِهِ وأَنا خيرُكُم لأَهْلي)

«በላጫችሁ ለቤተሰቡ መልካም የሆነው ነው። እኔ ለቤተሰቤ (መልካም በመሆን) በላጫችሁ ነኝ።»

[ሶሒሑ-ት'ቲርሚዚይ: 3895]

አየህ! ለቤተሰብህ መልካም ከሆንክ በላጭ ሰው ሆንክ!

*

√ ያኔ ልብ ነኪ የሆኑ ዘመን ተሻጋሪ የሆኑ ወሳኝ ወሳኝ የአደራ መልዕክቶችን ባስተላለፉበት የመሰናበቻው ሐጅ የዐረፋህ ኹጥባቸው ላይ ከተናገሯቸው መልዕክቶች መካከል አንዱ ምን እንደነበረ ታውቃለህ?

ልክ ከ2ኛው የዲን ምሰሶ ከሶላት ቀጥሎ «የሴቶችን ነገር አደራ!» ነበር ያሉት።

(…ألا واستَوصوا بالنِّساءِ خيرًا…)

[ሶሒሑ-ት'ቲርሚዚይ: 3087]

እና ሐቢቢ! ሴት ልጅ የነቢዩ አደራ ናትና ነቢይህ የሰጡህን አደራ ተንከባክበህ ይዘሃል ወይንስ አደራህን በልተሃል? መልሱን ላንተው!

ግን እኔ እንደ ወንድም የምመክርህ አደራህን ከበላህ ነገ የቂያም ቀን መልስህን ከወዲሁ እንድታዘጋጅ ነው። እስካሁን ያሳለፍከው በደል ካለና በህይዎት ካለች ደስ እስከሚላት ድረስ ዐውፍታ ከመጠየቅ ጀምሮ ካሳት። አስደስታት። አላህ አድሎህ ካልበደልካት ደግሞ ወደፊትም እስከ ዕለተ ሞትህ ድረስ ላለመበደልና አደራህን ጠብቀህ ለመያዝ የምትችለውን ሁሉ አድርግ።

ይህንን ስል መልካሙን ባልሽን ሐቁን የምታጓድይና በርሱ ላይ የምታጫርቺ እንስት መኖርሽን ረስቼ ስላልሆነ፤ ወደ አንቺ ሌላ ቀን እመለሳለሁ– በአላህ ፈቃድ። ግን እስከዛው ተስተካክለሽ ጠብቂኝ።

||

ወንድማችሁ፦ ሙራድ ታደሰ

========

ኖቬምበር 27, 2023 G.C.

||

t.me/MuradTadesse

ummalife.com/MuradTadesse

fb.com/MuraadTadesse

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

አባት❤️

The most underrated man👌

ረጅም እድሜና ጤና ለአባቶች!

ወላጆቻችሁ በህይዎት ካሉ ተጠቀሙባቸው። ሲሞቱ እንዳይቆጫችሁ!

ግን ለአባቶች የሚገባቸውን ያክል ዋጋ ሰጥተናቸዋል?

አባት አቢ ባባ.mp3
አባት አቢ ባባ.mp3
03:10
Add to my audio
Download
Send as a message
Share on my page
Share in the group