UMMA TOKEN INVESTOR

About me

★Electrical and Computer Engineer from AAiT,AAU ★M. Sc Candidate in AI ★MA in Leadership ★Software Developer ★Programmer ★Former Memebership Coordinator @ESSS ★Ethical Hacker ★Founder and CEO

Translation is not possible.

የዓለም ህዝብ ግን አይገርምም⁉️

=======================

(ዓለም በዚህ ዘመን አይታው የማታውቀው የጦር ወንጀልና የዘር ጭፍጨፋ በጘዝ'ዛ)

||

✍ 365 km² ስፋት ባላት አነስተኛ ከተማ ውስጥ 2.3+ ሚሊዮን ዜጎች ተጠጋግተው ይኖሩባታል። በዚህች densely populated በሆነች ከተማ ላይ ለተከታታይ 3 ሳምንታት ያላባራ ከ12 ሺህ ቶን በላይ ቦምብ ሲዘንብ፤ በዚህም ሳቢያ፦

1) በትንሹ 7,028 የሚሆኑ ፈለስጢናዊ ሙስሊሞች ሲገደሉ፣

2) ከ70% በላይ የሚሆኑት ህፃናትና ሴቶች ሲሆኑ (2,913 ህፃናትና 1,709 ሴቶች)፣

3) 18,482 የሚሆኑት ለከፍተኛ የአካል ጉዳት ሲዳረጉ፣

4) ባለፉት 24 ሰዓታት ብቻ 481 የሚሆኑት ሲገደሉ (ከመካከላቸው 209 የሚሆኑት ህፃናት ናቸው።)፣

5) ከ1,650 በላይ የሚሆኑት ጀናዛቸው እንኳ ሳይገኝ እስካሁን ድረስ በቦምብ በፈራረሱት ህንፃዎች ስር ሲሆኑ (ከመካከላቸው 940 ህፃናት አሉበት።)፣

6) 731 የሚሆኑ ፈለስጢናዊ ሙሉ ቤተሰቦች ሲገደሉ፣

⑦) 101 የጤና ባለሙያዎች ሲገደሉና 100 የሚሆኑት ሲቆስሉ፣

⑧) 12 ሆስፒታሎችና 32 የጤና ማዕከላት በነዳጅ እጥረትና በቦምብ ጥቃት ከአገልግሎት ውጭ ሲሆኑ፣

9) በኢንኩቤተር ውስጥ የሚገኙ ከ130 በላይ የሚሆኑ ህፃናት ያሉበት ሆስፒታል ባጋጠመው በነዳጅ እጥረት ሳቢያ ነፍሳቸው በእንጥልጥል ላይ ሲገኝ፣

⑩) ከ1.5 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ ንጹሐን ከመኖሪያ ቤታቸው ተፈናቅለው በመጠለያ ካምፖች፣ በት/ቤቶች፣ በሆስፒታል ግቢዎች፣ በመስጂዶችና ቤተ ክርስቲያን ተጠልለው ሳለ በዛው ባሉበት ጥቃቱ ሲያገኛቸው…

(ከሰው ነፍስ አይበልጥምና ወደ አመድነት ስለተቀየሩት ውብ ህንፃዎችና መሠረተ ልማቶችማ አውርተን አንዘልቀውም።)

የሰለጠነ ተብዬው ዓለም አሁንም «ጦርነቱ ይቁም!» ከማለት ይልቅ «እስራኤል ራሷን የመከላከል መብት አላት፣ ሐማስ መጥፋቱን ማረጋገጥ አለባት፣ ከጎንሽ ነን፣ ሐማስ ሽብርተኛ ነው፣ በሐማስ ጥቃት ለሞቱተረ እስራኤላዊያን አዝነናል!…» እያሉ ነው።

ትንሽ አሻሻልን የሚሉት ደግሞ ጦርነቱ መቆም የለበትም፤ ግን የተወሰነች እርዳታ ይግባላቸው ይላሉ።

እስካሁን በጋዛ መብራት የለ፣ ውሃ የለ፣ ምግብ የለ፣ ነዳጅ የለ…። በዚህ የተነሳ የቆሰሉትና መደበኛ ህመም የሚታመሙትም መታከም አልቻሉም።

ዙሪያውን በከበባ ስለሆነ ለጠናበት ታማሚ የውጭ ሕክምና እንዲያገኝ ማድረግ አልተቻለም።

እስራኤል ከላይ በአየር ከምታዘንበው የቦምብ ዝናብ ባሻገር ከምግብና ውሃ እንዲሁም ከሕክምና ከልክላ በጅምላ ጭፍጨፋ የጦር ወንጀልና የዘር ማፅዳት ወንጀል በመፈጸም ላይ ትገኛለች። ይህ ሁሉ የሚሆነው ዓለም እያዬ በ21ኛው ክፍለ ዘመን ነው። ተመድ ተብዬውም ሆነ የትኛውም የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ነኝ የሚል ተቋም ሁሉ የውሃ ሽታ ሆኗል። የነርሱ ህግ እነርሱን ለማዳን እንጂ ለሌላው አይሠራም። እነርሱ ዘንድ የሙስሊም፣ የዓረብና የአፍሪካዊ ሞት ከውሻቸው ሞት በታች ነው።

ግን ነፍስ ሁሉ እኩል ናትና የእጃቸውን አንድ ቀን ማግኘት አይችሉም። ነገ ላይ በሌላ የነርሱ አካል ላይ ጥቃት ሲፈጸም በሚዲያቸውም ሆነ ባልተጻፈው ህጋቸው ከአጥናፍ እስከ አጥናፍ ሲለፍፉ እናገኛቸዋለን።

አላህ ውርደታቸውን ያቅርበው፤ ለተበዳዮች ነስሩን ያፍጥነው።

አላህ የአሸናፊዎች ሁሉ አሸናፊ የሆነ ጥበበኛና ታጋሽ ጌታ ነው። አንድ ቀን አይርላቸውም።

||

t.me/MuradTadesse

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

ምሰሶ አልባው መስጂድ በሃገረ ስዑዲ‼

===========================

✍ በሳዑዲ ዓረቢያው ተቡክ ዩኒቨርስቲ ስለተገነባው ምሰሶ አልባ ዘመናዊ መስጂድ በጥቂቱ፦

√ የመስጂዱ አጠቃላይ ስፋት 8,000 ካሬ ሜትር ሲሆን፤ 3,500 ሰጋጆችንም ያስተናግዳል።

*

√ እያንዳንዳቸው 50 ሜትር ቁመት ያላቸው ሁለት ሚናሮች አሉት። ጣራው በ 5,887 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ በሞዛይክ ያጌጠ የጉልላት ቅርጽ አለው።

*

√ የመስጂዱ የፊት ለፊት ገፅታዎች በከፍተኛ ደረጃ የብርሃን ማስተላለፊያ ድርብ መስታወት ያላቸው ሲሆን ግድግዳዎቹ እና ወለሎቹ በግራናይት እና በእብነ በረድ ተሸፍነዋል።

*

√ የመስጂዱ የውጪ አደባባዮች እና የመኪና ማቆሚያ ስፍራዎች አጠቃላይ ስፋት 30,300 ካሬ ሜትር ሲሆን የመኪና ማቆሚያዎቹ 380 ተሽከርካሪዎችን የመያዝ አቅም አላቸው።

*

√ መስጂዱ በተፈጥሮው የብርሃን ስርዓት በጉልላቱ እና በመስታወት ግድግዳዎች፣ በማዕከላዊ አየር ማቀዝቀዣ፣ ​​በቢኤምኤስ አስተዳደር እና ቁጥጥር ስርዓት፣ በእሳት አደጋ ጊዜ የማንቂያ ስርዓት ያለው ነው።

*

√ መግቢያዎቹ በግራናይት አደባባዮች የተሸፈኑ ሲሆን የመስጂዱ ግቢ ወለል የእብነ በረድ ንጣፎች እና የመስታወት ግድግዳዎች አሉት።

©: ሀሩን ሚድያ

||

t.me/MuradTadesse

image
image
image
image
image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

አንድ ሰው ለአንድ ጥበበኛ «ምከረኝ?» አለው።

ጥበበኛውም «አላህ እከለከለህ ነገር ላይ እንዳያይህ፤ ባዘዘብህ ቦታ ላይም እንዳያጣህ!»

ህምምም…!

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

መልካም ሚስት ደሃ የሆነ ባሏን ንጉስ መስሎ እንዲሰማው ታደርገዋለች።

መጥፎዋ ደግሞ ባለሃብቱን ባሏን ባሪያ መስሎ እንዲሰማው ታደርገዋለች።

ላላገባችሁ አላህ መልካም ሚስት ይወፍቃችሁ፤ ላገባችሁ አላህ መልካም ሚስት ያድርግላችሁ!

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

ያሳዝናል‼

========

✍ የአማራ ክልል ሙስሊም ማኅበረሰብ አሁን ያለበት አጣብቂኝ ተጨባጭ ያሳዝናል።

በአንድ በኩል «ዐቢይ አሕመድ ሙስሊም ነው፤ የዚህ እስላም መንግስት ደጋፊና ተላላኪ ነህ፤ ካልሆንክ ከኛ ጋር ዝመትና ተዋጋ!» ተብሎ ያለ ወንጀሉ ይታገታል፣ ይዘረፋል፣ ይደበደባል፣ አለፍ ሲል ደግሞ በዘግናኝ ሁኔታ ይገደላል።

በሌላ በኩል ራሱን እንዳይከላከል እንኳ የመንግስት መከላከያ በጥርጣሬ ዓይን ሙስሊሙን ተመልክቶ ፋኖ የተሰኘው ኃይል ከዘረፈው የተረፈውን መሳሪያ ወስዶባቸዋል።

በሞጣ፣ በባህር ዳርና አካባቢዋ፣ በጎንደር፣ በወሎ፣ በሸዋ… አላስፈላጊ ጫና ውስጥ ይገኛል።

በተለይም በጎጃምና በጎንደር ከባድ አጣብቂኝ ውስጥ ነው። የጎጃም ኃይል በዚያ አካባቢ አንድም ሙስሊም በሰላም መኖር የለበትም የሚል እቅድ ያነገበ ይመስል፤ ሰሞኑን በባህር ዳርና በምስራቅ ጎጃሟ ሞጣ ተከታታይ እገታና የግድያ ወንጀል በመፈፀም ላይ ይገኛል።

በዛሬው ዕለትም ወንድማችን ገደፋው ሐሰንን ሞጣ ላይ ገድለውታል።

መንግስት ይህንን ሰላማዊ ሙስሊም ማኅበረሰብ ደህንነቱን ማስጠበቅ አልቻለም። አቅም አጥቶ ነው እንዳንል በቦታው የመንግስት ኃይሎች ይታያሉ። የሙስሊሙን ህጋዊ መሳሪያ ከመግፈፍ ንጹሐኑን ሙስሊም እያገተና እየገደለ የሚገኝን ጽንፈኛ ኃይል ስርዓት ማስያዝ ይበልጥ ነበር።

አሁንም ቢሆን የሚመለከተው የመንግስት አካል በዚያ አካባቢ የሚገኝን የራሱን ኃይል ጭምር ፈትሾ የክልሉን ሙስሊም ማኅበረሰብና ሰላማዊ ዜጋ ደህንነትና ህልውና ሊያስጠብቅ ይገባል።

የዚህ ክልል ሙስሊም በክልሉና ከክልሉ ውጭ በሁለት ቢላዋ መታረዱ የሚቆምበት ጊዜ ይናፍቃል። አላህ ሰላሙን ይመልስለትና!

አሁንም እንላለን፤ ፍትሕ ለአማራ ክልል ሙስሊሞች‼

||

t.me/MuradTadesse

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

Eid Mubarek‼

Send as a message
Share on my page
Share in the group