UMMA TOKEN INVESTOR

About me

★Electrical and Computer Engineer from AAiT,AAU ★M. Sc Candidate in AI ★MA in Leadership ★Software Developer ★Programmer ★Former Memebership Coordinator @ESSS ★Ethical Hacker ★Founder and CEO

Translation is not possible.

የዓለም ህዝብ ግን አይገርምም⁉️

=======================

(ዓለም በዚህ ዘመን አይታው የማታውቀው የጦር ወንጀልና የዘር ጭፍጨፋ በጘዝ'ዛ)

||

✍ 365 km² ስፋት ባላት አነስተኛ ከተማ ውስጥ 2.3+ ሚሊዮን ዜጎች ተጠጋግተው ይኖሩባታል። በዚህች densely populated በሆነች ከተማ ላይ ለተከታታይ 3 ሳምንታት ያላባራ ከ12 ሺህ ቶን በላይ ቦምብ ሲዘንብ፤ በዚህም ሳቢያ፦

1) በትንሹ 7,028 የሚሆኑ ፈለስጢናዊ ሙስሊሞች ሲገደሉ፣

2) ከ70% በላይ የሚሆኑት ህፃናትና ሴቶች ሲሆኑ (2,913 ህፃናትና 1,709 ሴቶች)፣

3) 18,482 የሚሆኑት ለከፍተኛ የአካል ጉዳት ሲዳረጉ፣

4) ባለፉት 24 ሰዓታት ብቻ 481 የሚሆኑት ሲገደሉ (ከመካከላቸው 209 የሚሆኑት ህፃናት ናቸው።)፣

5) ከ1,650 በላይ የሚሆኑት ጀናዛቸው እንኳ ሳይገኝ እስካሁን ድረስ በቦምብ በፈራረሱት ህንፃዎች ስር ሲሆኑ (ከመካከላቸው 940 ህፃናት አሉበት።)፣

6) 731 የሚሆኑ ፈለስጢናዊ ሙሉ ቤተሰቦች ሲገደሉ፣

⑦) 101 የጤና ባለሙያዎች ሲገደሉና 100 የሚሆኑት ሲቆስሉ፣

⑧) 12 ሆስፒታሎችና 32 የጤና ማዕከላት በነዳጅ እጥረትና በቦምብ ጥቃት ከአገልግሎት ውጭ ሲሆኑ፣

9) በኢንኩቤተር ውስጥ የሚገኙ ከ130 በላይ የሚሆኑ ህፃናት ያሉበት ሆስፒታል ባጋጠመው በነዳጅ እጥረት ሳቢያ ነፍሳቸው በእንጥልጥል ላይ ሲገኝ፣

⑩) ከ1.5 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ ንጹሐን ከመኖሪያ ቤታቸው ተፈናቅለው በመጠለያ ካምፖች፣ በት/ቤቶች፣ በሆስፒታል ግቢዎች፣ በመስጂዶችና ቤተ ክርስቲያን ተጠልለው ሳለ በዛው ባሉበት ጥቃቱ ሲያገኛቸው…

(ከሰው ነፍስ አይበልጥምና ወደ አመድነት ስለተቀየሩት ውብ ህንፃዎችና መሠረተ ልማቶችማ አውርተን አንዘልቀውም።)

የሰለጠነ ተብዬው ዓለም አሁንም «ጦርነቱ ይቁም!» ከማለት ይልቅ «እስራኤል ራሷን የመከላከል መብት አላት፣ ሐማስ መጥፋቱን ማረጋገጥ አለባት፣ ከጎንሽ ነን፣ ሐማስ ሽብርተኛ ነው፣ በሐማስ ጥቃት ለሞቱተረ እስራኤላዊያን አዝነናል!…» እያሉ ነው።

ትንሽ አሻሻልን የሚሉት ደግሞ ጦርነቱ መቆም የለበትም፤ ግን የተወሰነች እርዳታ ይግባላቸው ይላሉ።

እስካሁን በጋዛ መብራት የለ፣ ውሃ የለ፣ ምግብ የለ፣ ነዳጅ የለ…። በዚህ የተነሳ የቆሰሉትና መደበኛ ህመም የሚታመሙትም መታከም አልቻሉም።

ዙሪያውን በከበባ ስለሆነ ለጠናበት ታማሚ የውጭ ሕክምና እንዲያገኝ ማድረግ አልተቻለም።

እስራኤል ከላይ በአየር ከምታዘንበው የቦምብ ዝናብ ባሻገር ከምግብና ውሃ እንዲሁም ከሕክምና ከልክላ በጅምላ ጭፍጨፋ የጦር ወንጀልና የዘር ማፅዳት ወንጀል በመፈጸም ላይ ትገኛለች። ይህ ሁሉ የሚሆነው ዓለም እያዬ በ21ኛው ክፍለ ዘመን ነው። ተመድ ተብዬውም ሆነ የትኛውም የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ነኝ የሚል ተቋም ሁሉ የውሃ ሽታ ሆኗል። የነርሱ ህግ እነርሱን ለማዳን እንጂ ለሌላው አይሠራም። እነርሱ ዘንድ የሙስሊም፣ የዓረብና የአፍሪካዊ ሞት ከውሻቸው ሞት በታች ነው።

ግን ነፍስ ሁሉ እኩል ናትና የእጃቸውን አንድ ቀን ማግኘት አይችሉም። ነገ ላይ በሌላ የነርሱ አካል ላይ ጥቃት ሲፈጸም በሚዲያቸውም ሆነ ባልተጻፈው ህጋቸው ከአጥናፍ እስከ አጥናፍ ሲለፍፉ እናገኛቸዋለን።

አላህ ውርደታቸውን ያቅርበው፤ ለተበዳዮች ነስሩን ያፍጥነው።

አላህ የአሸናፊዎች ሁሉ አሸናፊ የሆነ ጥበበኛና ታጋሽ ጌታ ነው። አንድ ቀን አይርላቸውም።

||

t.me/MuradTadesse

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

በተዘጋብህ በር አትፀፀት‼

ከፊት ለፊትህ የተዘጋውን በር ከጀርባው ያለውን አደጋ ብታውቅ ኖሮ፤ ማማረርህን ትተህ በመዘጋቱ አላህን በብዙ ታመሰግነው ነበር።

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

الذكاء غلب القوة

ከጉልበትህ በላይ ጭንቅላትህን ተጠቀም። የግድ ጉልበት ካላወጣህ ያልሠራህ አይምሰልህ።

6 views
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

ያ አላህ!

«የዱንያ ሙቀትና ግለትን በሙከየፍ (በመሮሃ) እንከላከላለን። ህፃናትን ለሚያሸብተው ቀን ሙቀትስ ምን አዘጋጅተናል⁉️»

አላህ ዘንድ ያለውስ الحر ግን እንደት ይሆን ያ ረብ?

اللهم اجرنا من النار🤲

||

t.me/MuradTadesse

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

ሑጃጅ የሆነ ካለ ወይም ቤተሰብና ጓደኛ ያለው ካለ ይህ ጽሑፍ ቢረዝምም እንደምንም እስከመጨረሻው ያንብበው።

የቻለ በሌሎች ቋንቋዎች ይተርጉምና ያሰራጨው፤ ለኔም ይንገረኝ። በተለይ በኦሮምኛና ሱማሊኛ!

https://t.me/MuradTadesse/36125

https://t.me/MuradTadesse/36126

https://t.me/MuradTadesse/36127

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

ይህን የኤአይ ምስል ሚሊዮኖች በማህበራዊ ሚዲያ ተጋርተውታል። ንጹሕ አስተሳሰብ ያላቸው ሰብዓዊነትን ያልሸጡ ዜጎችም ቻሌንጁን ተቀላቅለዋል። ወራሪዋ መጀመሪያ ከሰሜን ጋዛ ይውጡና ወደ ደቡብ ጋዛ ይሂዱ አለች። ሰው እሪሪሪ አለ፣ አሽቄዎቿ ሳይቀሩ። ትንሽ ቆየችና ሰሜኑን አውድማ ስትጨርስ ወደ ደቡብ አመራች። ኻን ዩኑስና ሌሎችንም ካወደመች በኋላ ከደቡቡም ይውጡና በግብፅ ድንበር በኩል ወደ ራፋህ መጠለያ ካምፕ ይግቡ አለች። ትንሽ ተጮኸና ዝም አሏት። ደቡቡን አውድማ ስትጨርስ ወደ ራፋህም አመራች። ከወዲያ የኮንክሪት ግምብ ነው፣ ከወዲህ እሳት ነው። ወደየት ይሂዱ ፈለስጢናውያን? በዛው ላይ መጨፍጨፍ ጀመረች። አሁን ሁሉንም አዳርሳ ስትጨርስ ውጤት አጣችበት መሰል አስታርቁኝ ማለት ጀመረች። አላህ በእሳት ያቃጥላችሁ።

||

t.me/MuradTadesse

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group