UMMA TOKEN INVESTOR

About me

● ICT and CTE Teacher ● Basic Computer Skills Trainer ● Programming Concept Trainer t.me/ReshadMuzemil

Табасаранан алхьа кха дац.
🌙 ለ6ኛ እና ለ8ኛ ክፍል ተፈታኝ ሙስሊም ጀግኖች እና ለወላጆች!
ትምህርትን በኢማን እና በትጋት ወደ ስኬት 🚀
ውድ ልጆቻችን እና ወላጆች! አሁን እየተፈተናችሁት ላለው ሞዴል ፈተና፣ ለመጪዎቹ ተከታታይ ልምምዶች እና ለዋናው የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ፈተና በሙሉ ልብና በተረጋጋ መንፈስ ለመዘጋጀት እነዚህን ነጥቦች ልብ ልንል ይገባል! ፈተና የዱንያ (የዚህ ዓለም) መለኪያ እንጂ የሁለንተናችን መመዘኛ አለመሆኑን በመረዳት አላህ ከኛ ጋር ነው! በሚል ጠንካራ እምነት እንዘጋጅ።
👦👧 ክፍል 1፡ ለጀግና ተማሪዎቻችን
1. ተወኩል (በአላህ መመካት) እና ትጋት
አሁን ያሉት ሞዴል ፈተናዎች ስህተታችሁን የምታውቁበት እና ራሳችሁን ለዋናው ፈተና የምታሻሽሉበት ትልቅ እድል መሆኑን አትርሱ።
✅ አላህ (ሱ.ወ) እንዲህ ይላል፡- "የሚቻላችሁን አድርጉ፤ እኔም እረዳችኋለሁ።" እናንተ ትጉ፣ አላህ (ሱ.ወ) ደግሞ በረካውን (በረከቱን) ይጨምራል።
✅ ዱዓ (ፀሎት) የመሳሪያችሁ መሳሪያ ነው። ሁሌም አላህን ለእውቀት ብርሃንና ለስኬት ለምኑት።
2. ቂም የለሽ ልብ ለዒልም (እውቀት) ብርሃን
✅ ከጓደኛም ሆነ ከሌላ ሰው ጋር ያለባችሁን አለመግባባት ወይም ቅሬታ ይቅር ተባባሉ። ልብን ከጥላቻ ማጽዳት ለአእምሮ ሰላምን ይሰጣል።
3. በኢስላማዊ ስነምግባር (አደብ) ማጥናት
✅ አብራችሁ ስታጠኑም ሆነ ብቻችሁን አላህን መፍራት ዋነኛው መመሪያችሁ ይሁን።
🛑 የመጨረሻ እና ወሳኝ ማስጠንቀቂያ!
ፈተና ላይ ስትቀመጡ በፍጹም መፈፀም የሌለባችሁ አንድ ስህተት አለ!
⭕️ መኮረጅ (ማጭበርበር): ከአላህም ሆነ ከፈተናው አሰጣጥ አንፃር መኮረጅ ፈጽሞ የተከለከለ ነው። በሌላ ተማሪ ስራ መኮረጅ ወይም የፈተና ደንብን መጣስ የሁሉንም የፈተና ውጤት ለመሰረዝ ይዳርጋል። አላህ (ሱ.ወ) በሂደት እንጂ በማጭበርበር የሚመጣን ውጤት በረካውን አይሰጥበትም! በራስ ችሎታ ብቻ ለመስራት ቁርጠኛ ሁኑ!
📝 በሁሉም የፈተና ሳምንታት ልትተገብሩት የሚገቡ ጥንቃቄዎች
✅ ሰላት በወቅቱ: ሰላትን በአግባቡ መፈፀም ነፍስን ያረጋጋል፣ ስሜትን ይቆጣጠራል፣ አእምሮን ያሳርፋል።
✅ ዚክር (የአላህን ማውሳት): ወደ ፈተና ስትሄዱም ሆነ ስትቀመጡ አላህን አስታውሱ።
✅ የእንቅልፍ ሰዓት: ሰውነትና አእምሮ በቂ እረፍት ካላገኙ አያገለግሉምና በጊዜ ተኙ።
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
👨‍👩‍👧‍👦 ክፍል 2፡ ለውድ ወላጆች/አሳዳጊዎች
1. ዱዓ እና ብርታት:
◆ የወላጆች ዱዓ ተቀባይነት አለው! ጌታችን አላህ (ሱ.ወ) ልጆቻችሁን በዒልም እንዲያብቁ፣ ልቦናቸውን እንዲከፍትላቸው እና ጭንቀትን እንዲያስወግድላቸው በብዛት ዱዓ አድርጉ።
2. አዎንታዊ ቃላት እና ተስፋ:
◆ "የቻልክውን ያህል ጥረት አድርግ፣ ውጤት የሚሰጠው አላህ ነው" በሏቸው። ትጋታቸውን አድንቁ፣ እንጂ በውጤቱ አትዝለፉ።
መጨረሻው ድል ነው!
አላህ (ሱ.ወ) ትጋታችሁን አይጥልም። በታማኝነትና በሰላም ተፈትናችሁ ስኬትን ተጎናጸፉ!
ጌታችን አላህ (ሱ.ወ) ይርዳችሁ!
ሁሉንም ነገር ያግራላችሁ፤ ለሙስሊሙ ማህበረሰብና ለሁሉም ሰው የሚጠቅም ዕውቀት ይስጣችሁ።
መልካም ፈተና! 🤲✨
✍️ በረሻድ ኢብኑ ሙዘሚል
image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Табасаранан алхьа кха дац.
📧 ስኬት ያለበት ውድቀት 📧
1. ወደኋላ መመለስ ለትልቅ ዝላይ ነው!
በህይወታችን ጉዞ ነገሮች እንዳሰብነው ላይሆኑ ይችላሉ፤ አንድ ሁለት እርምጃዎችን ወደኋላ ልንሄድ አሊያም ልንወድቅ እንችላለን። በዚህ ጊዜ ብዙዎቻችን ተስፋ እንቆርጣለን።
ነገር ግን ወንድምና እህቶቼ፤ የተፈጥሮን ንጉስ አንበሳን ልብ ብለን እንመልከት! አንበሳ ትልቅ የሆነን ገደል ለመዝለል በፈለገ ጊዜ፣ ዝም ብሎ አይዘልም፤ ብዙ እርምጃዎችን ወደኋላ ሄዶና ጉልበቱን አሰባስቦ ነው ያን ገደል በአስገራሚ ሁኔታ የሚዘለው‼️ በተመሳሳይ አንበሳው የሆነ ነገር ለማደን ሲፈልግ፣ ሁለት እርምጃዎችን ወደኋላ አፈግፍጎ ነው አደናውን በድል የሚያጠናቅቀው።
እኛም ህይወት ወደኋላ በገፈተረችን ሰዓት "በቃ ተሸንፈናል" ብለን ተስፋ ልንቆርጥ አይገባም፤ ህይወት ወደኋላ ስትገፈትረን ወይም ስንወድቅ፣ ራሷ ህይወት እኛን ለባሰ ድል እና ለትልቅ ዝላይ እያዘጋጀችን መሆኑን እናስተውል‼️
2. ለስኬት ግንባታ "ሙከራ" ወሳኝ ነው!
ዛሬ ላይ ተገፍትረን ነገ ከፍ ብለን የስኬት ማማ ላይ ለመድረስ ደግሞ አንድ ነገር ያስፈልገናል፤ እሱም "ሙከራ" ነው።
የሚያምሩ ቤቶችን መሥራት ካለብን፣ ለዚህ የሚሆን ጠንካራና የሚያማምሩ ለቤት ግንባታ የሚሆኑ ግብዓቶችን ማዘጋጀት ይኖርብናል፤ ይህ ዝግጅታችን ነው ቤቱን ያማረ ሊያደርገው የሚችለው። ልክ እንደዚሁ በህይወታችንም ከፍ ብለን ለመጓዝና የስኬት ማማ ላይ ለመድረስ፤ ብዙ የሆኑ፣ ደከመኝ ሰለቸኝ የሌለባቸው፣ ጠንካራና የሚያማምሩ ሙከራዎች ያስፈልጉናል‼️ ያለ ጠንካራ ሙከራ የሚገኝ ስኬት የለምና።
3. መሞከር ማሸነፍ ነው!
ፍርሃት የሽንፈት መጀመሪያ ነው። ሙከራን ፈርተን ልናሸንፍ አንችልም‼️ ደጋግመው የሚሞክሩ ደግሞ መቼም ሊሸነፉ አይችሉም፤ ምክንያቱም እያንዳንዱ ሙከራ ወደ ስኬት የሚያቀርብ እርምጃ ነውና።
════════════════
▶ ቀን ለጨለማ ብርኃን ታስተምራታለች‼️
▶ ሙከራ ለስኬት ከፍ ማለትን ታስለምዳታለች‼️
▶ ውድቀት ብዙ ችግር አለበት ስቃዩም የከፋ ነው፤ ነገር ግን ይህ ችግርና ስቃይ ለኛ ለሰዎች ተነስቶ መሄድን ያስተምረናል‼️
════════════════
✍️ በረሻድ ኢብኑ ሙዘሚል
Join our channel
t.me/Grade1_4Info
t.me/Grade5and6Info
t.me/Grade7Info
t.me/Grade8Info
t.me/Grade9Info
t.me/Grade10Info
t.me/Grade11and12Info
t.me/BasicComputer_Skills
image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Табасаранан алхьа кха дац.
ይሄው ለማንም እንደሚታየው ቡርሃኑዲን አልሐለቢይ ማለትም ሲብጡ ኢብኒል ዐጀሚ ራሱ ሀካሪን “ሸይኹል ኢስላም” ብለው ነው የጠሯቸው። ሐሰን ታጁ ይህንንም ቆርጦ አስቀርቶታል። ሰው እንዴት በዚህ ልክ በውሸት ሱስ ናላው ይዞራል! ክፉ ልክፍት!
4ኛ:- ደግሞም “ሐዲሥ በመፈብረክ ተወንጅሏል” ያሉት እሳቸው አይደሉም። ይህም የሐሰን ታጁ ሌላ ቅጥፈት ነው። ታሪክ የሚገልፅ ሰው ጥሩውንም መጥፎውንም የተባለውን ማስፈር ስለነበረባቸው ነው የኢብኑ ነጃርን ንግግር ያሰፈሩት እንጂ እሳቸውማ “ሸይኹል ኢስላም” ነው ያሉት።
#ቅጥፈት_አምስት
“እዚህ ላይ የታዘብኩት ነገር በአንዳንድ ወገኖች ዘንድ ‹‹ሸይኹል ኢስላም›› የሚለዉ ማዕረግ ከዕዉቀትና በስብዕና ጥራት ይልቅ በቡድን ስሜት በዘፈቀደ ሊሰጥ የመቻሉን ነገር ነዉ፡፡”
መልስ፦
1ኛ፦ በዚህ መልኩ የሚወነጅለው ዘሀቢን፣ ኢብኑል ቀዪምን እና አልባኒን ነው። ነገር ግን ሀካሪን “ሸይኹል ኢስላም” እያሉ የጠሩ አስር ዓሊሞችን ዘርዝሬያለሁ። ሁሉም ሐሰን ታጁ የውንጀላ ጣቱን አይሰነዝርባቸውም ብዬ የምገምታቸውን ብቻ ነው ያቀረብኩት። ሰበብ ላለመስጠት ስል እሱ በቡድንተኝነት ስሜት የሚወርፋቸውን ዘሀቢን፣ ኢብኑል ቀዪምን፣ ኢብኑ ዐብዲል ሃዲን ማካተት አልፈለግኩም።
ሀካሪን ሸይኹል ኢስላም ከማለት በተጨማሪ ኢብኑል ጀዊዚይ፣ ኢብኑ ኸሊካን እና ሌሎችም ኸይራቸውና ዒባዳቸው የበዛ፣ ከአህለሱናህ የሆኑ ሰው ናቸው” እያሉ ገልፀዋቸዋለዋል። [አልሙንተዞም፡ 17/7] [ወፈያት፡ 3/345] እነዚህን ሁሉ በቡድንተኝነት ይወርፋቸው ይሆን?
ማጠቃለያ፦
ሐሰን ታጁ ትናንት በለጠፋት በአንዲት አጭር የፌስቡክ ልጥፍ ስንት ውሸት እንደ ዋሸ ተመልከቱ። ሰው እንዴት በኢስላም ስም እየፃፈ በዚህ ልክ ይቀልላል! በነገራችን ላይ ስራዎቹ በሙሉ እንደዚህ ናቸው። እፍኝ መነሻ ይይዝና ማያያዣውም፣ መዳረሻውም እንዳለ በውሸት የተጥለቀለቀ ድምዳሜ ነው የሚሰራው። ውሸትን የጠላቶቹ መለያ መታወቂያ ያደረገው ጌታ ጥራት ይገባው ይላሉ ኢብኑ ተይሚያ ረሒመሁላህ።
(ኢብኑ ሙነወር፣ ጁማደል ኡላ 30/1447)
=
የቴሌግራም ቻናል፦ t.me/IbnuMunewor
2/2
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Табасаранан алхьа кха дац.
ይሄው ለማንም እንደሚታየው ቡርሃኑዲን አልሐለቢይ ማለትም ሲብጡ ኢብኒል ዐጀሚ ራሱ ሀካሪን “ሸይኹል ኢስላም” ብለው ነው የጠሯቸው። ሐሰን ታጁ ይህንንም ቆርጦ አስቀርቶታል። ሰው እንዴት በዚህ ልክ በውሸት ሱስ ናላው ይዞራል! ክፉ ልክፍት!
4ኛ:- ደግሞም “ሐዲሥ በመፈብረክ ተወንጅሏል” ያሉት እሳቸው አይደሉም። ይህም የሐሰን ታጁ ሌላ ቅጥፈት ነው። ታሪክ የሚገልፅ ሰው ጥሩውንም መጥፎውንም የተባለውን ማስፈር ስለነበረባቸው ነው የኢብኑ ነጃርን ንግግር ያሰፈሩት እንጂ እሳቸውማ “ሸይኹል ኢስላም” ነው ያሉት።
#ቅጥፈት_አምስት
“እዚህ ላይ የታዘብኩት ነገር በአንዳንድ ወገኖች ዘንድ ‹‹ሸይኹል ኢስላም›› የሚለዉ ማዕረግ ከዕዉቀትና በስብዕና ጥራት ይልቅ በቡድን ስሜት በዘፈቀደ ሊሰጥ የመቻሉን ነገር ነዉ፡፡”
መልስ፦
1ኛ፦ በዚህ መልኩ የሚወነጅለው ዘሀቢን፣ ኢብኑል ቀዪምን እና አልባኒን ነው። ነገር ግን ሀካሪን “ሸይኹል ኢስላም” እያሉ የጠሩ አስር ዓሊሞችን ዘርዝሬያለሁ። ሁሉም ሐሰን ታጁ የውንጀላ ጣቱን አይሰነዝርባቸውም ብዬ የምገምታቸውን ብቻ ነው ያቀረብኩት። ሰበብ ላለመስጠት ስል እሱ በቡድንተኝነት ስሜት የሚወርፋቸውን ዘሀቢን፣ ኢብኑል ቀዪምን፣ ኢብኑ ዐብዲል ሃዲን ማካተት አልፈለግኩም።
ሀካሪን ሸይኹል ኢስላም ከማለት በተጨማሪ ኢብኑል ጀዊዚይ፣ ኢብኑ ኸሊካን እና ሌሎችም ኸይራቸውና ዒባዳቸው የበዛ፣ ከአህለሱናህ የሆኑ ሰው ናቸው” እያሉ ገልፀዋቸዋለዋል። [አልሙንተዞም፡ 17/7] [ወፈያት፡ 3/345] እነዚህን ሁሉ በቡድንተኝነት ይወርፋቸው ይሆን?
ማጠቃለያ፦
ሐሰን ታጁ ትናንት በለጠፋት በአንዲት አጭር የፌስቡክ ልጥፍ ስንት ውሸት እንደ ዋሸ ተመልከቱ። ሰው እንዴት በኢስላም ስም እየፃፈ በዚህ ልክ ይቀልላል! በነገራችን ላይ ስራዎቹ በሙሉ እንደዚህ ናቸው። እፍኝ መነሻ ይይዝና ማያያዣውም፣ መዳረሻውም እንዳለ በውሸት የተጥለቀለቀ ድምዳሜ ነው የሚሰራው። ውሸትን የጠላቶቹ መለያ መታወቂያ ያደረገው ጌታ ጥራት ይገባው ይላሉ ኢብኑ ተይሚያ ረሒመሁላህ።
(ኢብኑ ሙነወር፣ ጁማደል ኡላ 30/1447)
=
የቴሌግራም ቻናል፦ t.me/IbnuMunewor
2/2
image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Табасаранан алхьа кха дац.
የቆርጦ ቅጠላው ንጉስ ዘመቻ በዘሀቢ እና በዑሉው ኪታባቸው
~
ኢብኑ ዐቂል እንዲህ ይላሉ፦
“አሽዐሪዮች ከአህሉል ሐዲሥ ጋር ባላቸው ሙግት ላይ ይዋሹባቸው ነበር።” [ረድ ዐለ'ል ዐሻዒራ፣ ኢብኑ ዐቂል፡ 91]
አቡ ኢስማዒል አልሀረዊን ለማጠልሸት ከሚሕራባቸው ውስጥ ከመስገጃቸው ስር ከነሐስ የተሰራ ጣኦት እስከ ማስቀመጥ የደረሱ ናቸው አሽዐሪዮች። [አሲየር፡ 18/512] “አላህ ወደ ቅርቢቷ ሰማይ ይወርዳል። ልክ እንደዚህ አወራረዴ!” ብሎ ከሚንበሩ ደረጃ ወርዷል ብለው ኢብኑ ተይሚያም እንዲሁ ዋሽተውባቸዋል። [ሪሕለቱ ኢብኒ በጡጣ፡ 110]
ሐሰን ታጁ እያደረገ ያለውም ይህንኑ ነው። የኢማሙ አሕመድን "ረድ 0ለ'ዘናዲቃ" እና የልጃቸው የዐብደላህን "አስሱናህ" ኪታቦች የፈጠራ ድርሰቶች ናቸው ብሎ የለየለት ቅጥፈት ፃፈ። የኢብኑል ቀይም "ጁዩሽ" ላይ ተሳለቀ። አሁን ደግሞ የቅጥፈት ጦሩ ወደ ዘሀቢ እና ወደ አልዑሉው ኪታባቸው ነው የዞረው። ባለፈው የኢማሙ አሕመድን ኪታብ ለማጣጣል የዘሀቢን ንግግር ቆርጦ ያቀረበበትን አይተናል። አሁንስ ምን ሰበብ አደረገ? በሰበብነት የመዘዘው የአቡል ሐሰን አልሀካሪን አጭር ግለ ታሪክ ነው። አልሀካሪ በሰነድ የተደገፈ “ዐቂደቱ ሻፊዒይ” የተሰኘ ኪታብ አላቸው። በዚህ ኪታብ ውስጥ ኢማሙ ሻፊዒይ ረሒመሁላህ ቀደምቶቻቸውን ያገኙበት እና የእሳቸውም ዐቂዳ አላህ ከዐርሹ በላይ ነው የሚል እንደሆነ የገለፁበት አለ። ዘሀቢ ይህንን ዐቂዳ “ሸይኹል ኢስላም አልሀካሪ ዘግቦታል” ብለው በ“አልዑሉው” ኪታባቸው አስፍረዋል። ሐሰን ታጁ ይህንን መነሻ በማድረግ ባጭር ፅሁፍ ብዙ የመቅጠፍ ክህሎቱን አሳይቶናል። ንግግሩን ቃል በቃል እያሰፈርኩ ምላሽ እሰጣለሁ። ይሄው፦
#ቅጥፈት_አንድ
“የኢማም ዘሀቢን ‹‹አል-ዑሉዉ›› ኪታብ ሳነብ አቡል ሀሰን አልሀካሪ ስለተባሉ ስብእና በሀዲስ ሊቃዉንት የተሰጡ አስተያየቶችና ዘሀቢ ሰዉየዉን የጠሩበት ማዕረግ ትኩረቴን ሳቡት፡፡”
መልስ፦
አል-ዑሉዉ ኪታብ ላይ ስለ ሀካሪ ከዘሀቢ ምስክርነት ውጭ የሌሎች የሐዲሥ ሊቃውንት ምንም አይነት አስተያየት የለም። ይሄ ሰውዬ እንዲሁ ከመሬት አንስቶ ነው የሚቀደደው።
#ቅጥፈት_ሁለት
{“እብንሀጀረል ዐስቀላኒ ስለሰዉየዉ የሚከተለዉን አስተያየት አስፍረዋል፡-
متهم بوضع الحديث وتركيب الأسانيد
‹‹ሀዲስ በመፈብረክና የቅጥፈት ሰነድ በማደራጀት ተሀይሷል፤››}
መልስ፦
በዚህ ንግግር ውስጥ ድርብርብ ጥፋት ነው ያለው።
1ኛ. ቀጥታ እሱ ያለው ቦታ ላይ ስትገልጡ ኢብኑ ሐጀር ስለ ሀካሪ ሀ ብለው ተርጀማቸውን የጀመሩት “ዐሊይ ብኑ አሕመድ፣ #ሸይኹል_ኢስላም አቡል ሐሰን አልሀካሪይ” ብለው ነው። ይህንን ሆነ ብሎ ቆርጦ አስቀርቶታል። ለምን? ካልዋሸ ጨዋታው አይደምቅለትም። በዚሁ ኪታብ ሌላ ሁለት ቦታ ላይ እንዲሁ ሀካሪን ሸይኹል ኢስላም ብለው ጠርተውታል። [ሊሳኑል ሚዛን፡ 2/306] እና [5/337]
2ኛ. እንዲያውም “ሀዲስ በመፈብረክና የቅጥፈት ሰነድ በማደራጀት ተሀይሷል” ያሉት ኢብኑ ሐጀር አይደሉም። ይሄ በኢብኑ ነጃር ስም የቀረበ ውንጀላ ሲሆን በሚገርም ሁኔታ ያቀረቡት ዘሀቢ ናቸው። [ሚዛኑል ኢዕቲዳል፡ 3/112] ኢብኑ ሐጀር እንዲያውም "አዘጋጁ (ዘሀቢ) የኢብኑ ነጃርን ስራ ያየ አይመስልም" በማለት የዘገባ ክፍተቱ እንዲታይ በማድረግ መከላከያ ነው ያቀረቡት። ስንት ጥፋት እንደፈፀመ ተመልከቱ። የኢብኑ ሐጀር "ሊሳኑል ሚዛን" ኪታብ የዘሀቢን "ሚዛኑል ኢዕቲዳል" ተህዚብ በማድረግ የተዘጋጀ እንደሆነ ባይገባው ይሆን ብዬ ዑዝር እንዳልሰጠው ራሱ በጠቀሰው የኢብኑ ሐጀር ኪታብ ላይ የሚገኘውን ፍፁም ተቃራኒ መልእክት እንዲሰጥ አድርጎ ቆራርጦና አዛብቶ ነው ያቀረበው። ተጨማሪ ማሳያ ላቅርብ፡
3ኛ፦ ኢብኑ ሐጀር እንኳን እሱ ባለው መልኩ ሀካሪን ሊወነጅሉ እንዲያውም ደጋግመው ነው “ሸይኹል ኢስላም” ብለው የገለጿቸው። የሌሎችንም አድናቆት አስፍረዋል። ለምሳሌ የሕያ ብኑ መንደህ፡ "የሶላት፣ የዒባዳ፣ የኢጅቲሃድ ሰው ነበር" እንዳላቸው፣ ሰምዓኒይ "ዒባዳው የበዛ፣ ዛሂድነቱ ያማረ፣ ኒያው የጠራ፣ የህዝብ ቅቡልነት ያለው፣ የተከበረ ሰው ነበር" እንዳላቸው፣ እንዲሁም 0ብዱልገፋር አልከርጂ "አይኖቼ እንደሱ አይነትን ዛሂድና ደግ ሰው አላዩም" ብለው እንደገጿቸው አስፍረዋል። ይሄ ሁሉ የኢብኑ ሐጀር ሊሳኑል ሚዛን ላይ ሐሰን ታጁ በጠቀሰው ገፅ ውስጥ የሚገኝ ነው። ሐሰን ታጁ በዚህ መጠን የለየለት ወናፍ የሆነው ምን ቢነካው ነው ግን? ሱብሓነላህ!! ሰው እንዴት በራሱ ኣኺራ ላይ ይቆምራል?!
#ቅጥፈት_ሶስት
“የገረመኝ ነገር ሀዲስ ፈብርኮ በማሰራጨት ልምድ የተነቀፈን እንዲህ አይነት ስብእና ዘሀቢ ‹‹ሸይኹል ኢስላም›› በሚል ማዕረግ ጠርተዉታል።”
መልስ፦
እውን ሀካሪን ''ሸይኹል ኢስላም" ብለው የጠሩት ዘሀቢ ብቻ ናቸው? በጭራሽ! ይሄውና
1. ዐብዱልገፋር አልከረጂይ [አስሲየር፡ 19/68]
2. አስሰምዓኒይ (562 ሂ.) [አልአንሳብ፡ ቁ. 5260]
3ኢብኑ ዐሳኪር (571 ሂ.) [ታሪኹ ዲመሽቅ፡ 41/239]
4. ኢብኑል ሙስተውፊ (637 ሂ.) [ታሪኹ ኢርቢል፡ 1/272]
5. ኢብኑ ኸሊካን (681 ሂ.) [ወፈያቱል አዕያን፡ 3/345]
6. ኢብኑል ሙለቂን (804 ሂ.) [ጦበቃቱል አውሊያእ፡ 451]
7. ቡርሀኑዲን አልሐለቢ (841 ሂ.) [አልከሽፉል ሐሢሥ፡ 184 ቁ 497]
8. ኢብኑ ሐጀር (848 ሂ.) [ሊሳኑል ሚዛን፡ 2/306፣ 4/195 እና 5/337]
9. ተቂዩዲን አቡልፈድል ሙሐመድ ብኑ ሙሐመድ አልሃሺሚይ (871 ሂ.) [ለሕዙል አልሓዝ ቢዘይሊ ጦበቃቲል ሑፋዝ፡ 81]
10. ዐብዱልሐይ ብኑ አሕመድ ኢብኑል ዒማድ (1089 ሂ.) [ሸዘራቱ ዘሀብ፡ 5/370]
እነዚህ ሁሉ ሀካሪን “ሸይኹል ኢስላም” ብለው የጠሩ ናቸው። እነዚህ እኔ ሳስስ የገጠሙኝ ናቸው። በደንብ ዳሰሳ ቢደረግ ሌሎችም ሊኖሩ እንደሚችሉ እገምታለሁ። ይህንን ያዙና ተጠቃሹን ሰው ማለትም ሀካሪን ከዑለማእ ተነጥለው ዘሀቢ ብቻቸውን “ሸይኹል ኢስላም” በሚል ማዕረግ እንደጠሩ አድርጎ የቀጠፈውን ተመልከቱ። የቅጥፈት ማሽን የሆነ ፍጥረት!
#ቅጥፈት_አራት
“እብኑል ዑጅሚ የተባሉ የሀዲስ አስተላላፊ ስብእናዎች አጥኝም ይህንኑ መስክረዋል፡፡”
መልስ፦
1ኛ. በመጀመሪያ ዑጅሚ ሳይሆን ዐጀሚ ነው። እንዲህ አይነት ስህተቶቹ በየ ፅሁፎቹ፣ በየ መፃህፍቱ በጣም ብዙ ስለሆኑ መከታተል ይከብዳል።
2ኛ. ኪታቡ የሲብጡ ኢብኒል ዐጀሚ (የኢብኑል ዐጀሚ የልጅ ልጅ) እንጂ ቀጥታ የኢብኑል ዐጀሚ አይደለም። የኪታቡ ባለቤት ቡርሀኑዲን አልሐለቢ በሚል ነው የሚታወቁት።
3ኛ፦ በጠቀሰው ኪታብ የጠቀሰው ገፅ ላይ ስትገቡ ቀጥታ የምታገኙት እንዲህ የሚል ነው፦
عَليّ بن أَحْمد شيخ الْإِسْلَام أَبُو الْحسن الهكاري قَالَ بن النجار مُتَّهم بِوَضْع الحَدِيث وتركيب الْأَسَانِيد قَالَه الذَّهَبِيّ فِي تَرْجَمَة عبد السَّلَام بن مُحَمَّد
“ዐሊይ ብኑ አሕመድ፣ #ሸይኹል_ኢስላም አቡል ሐሰን አልሀካሪይ። ኢብኑ ነጃር፡ ‘ሐዲሥ በመፈብረክና የቅጥፈት ሰነድ በማደራጀት የሚታማ ነው’ ብለዋቸዋል። ይህንን የገለፁት ዘሀቢይ ናቸው፣ በዐብዱሰላም ብኑ ሙሐመድ ታሪክ ስር።” [አልከሽፉል ሐሢሥ፡ 497]
1/2
image
Send as a message
Share on my page
Share in the group