የቆርጦ ቅጠላው ንጉስ ዘመቻ በዘሀቢ እና በዑሉው ኪታባቸው
~
ኢብኑ ዐቂል እንዲህ ይላሉ፦
“አሽዐሪዮች ከአህሉል ሐዲሥ ጋር ባላቸው ሙግት ላይ ይዋሹባቸው ነበር።” [ረድ ዐለ\'ል ዐሻዒራ፣ ኢብኑ ዐቂል፡ 91]
አቡ ኢስማዒል አልሀረዊን ለማጠልሸት ከሚሕራባቸው ውስጥ ከመስገጃቸው ስር ከነሐስ የተሰራ ጣኦት እስከ ማስቀመጥ የደረሱ ናቸው አሽዐሪዮች። [አሲየር፡ 18/512] “አላህ ወደ ቅርቢቷ ሰማይ ይወርዳል። ልክ እንደዚህ አወራረዴ!” ብሎ ከሚንበሩ ደረጃ ወርዷል ብለው ኢብኑ ተይሚያም እንዲሁ ዋሽተውባቸዋል። [ሪሕለቱ ኢብኒ በጡጣ፡ 110]
ሐሰን ታጁ እያደረገ ያለውም ይህንኑ ነው። የኢማሙ አሕመድን "ረድ 0ለ\'ዘናዲቃ" እና የልጃቸው የዐብደላህን "አስሱናህ" ኪታቦች የፈጠራ ድርሰቶች ናቸው ብሎ የለየለት ቅጥፈት ፃፈ። የኢብኑል ቀይም "ጁዩሽ" ላይ ተሳለቀ። አሁን ደግሞ የቅጥፈት ጦሩ ወደ ዘሀቢ እና ወደ አልዑሉው ኪታባቸው ነው የዞረው። ባለፈው የኢማሙ አሕመድን ኪታብ ለማጣጣል የዘሀቢን ንግግር ቆርጦ ያቀረበበትን አይተናል። አሁንስ ምን ሰበብ አደረገ? በሰበብነት የመዘዘው የአቡል ሐሰን አልሀካሪን አጭር ግለ ታሪክ ነው። አልሀካሪ በሰነድ የተደገፈ “ዐቂደቱ ሻፊዒይ” የተሰኘ ኪታብ አላቸው። በዚህ ኪታብ ውስጥ ኢማሙ ሻፊዒይ ረሒመሁላህ ቀደምቶቻቸውን ያገኙበት እና የእሳቸውም ዐቂዳ አላህ ከዐርሹ በላይ ነው የሚል እንደሆነ የገለፁበት አለ። ዘሀቢ ይህንን ዐቂዳ “ሸይኹል ኢስላም አልሀካሪ ዘግቦታል” ብለው በ“አልዑሉው” ኪታባቸው አስፍረዋል። ሐሰን ታጁ ይህንን መነሻ በማድረግ ባጭር ፅሁፍ ብዙ የመቅጠፍ ክህሎቱን አሳይቶናል። ንግግሩን ቃል በቃል እያሰፈርኩ ምላሽ እሰጣለሁ። ይሄው፦
#ቅጥፈት_አንድ
“የኢማም ዘሀቢን ‹‹አል-ዑሉዉ›› ኪታብ ሳነብ አቡል ሀሰን አልሀካሪ ስለተባሉ ስብእና በሀዲስ ሊቃዉንት የተሰጡ አስተያየቶችና ዘሀቢ ሰዉየዉን የጠሩበት ማዕረግ ትኩረቴን ሳቡት፡፡”
መልስ፦
አል-ዑሉዉ ኪታብ ላይ ስለ ሀካሪ ከዘሀቢ ምስክርነት ውጭ የሌሎች የሐዲሥ ሊቃውንት ምንም አይነት አስተያየት የለም። ይሄ ሰውዬ እንዲሁ ከመሬት አንስቶ ነው የሚቀደደው።
#ቅጥፈት_ሁለት
{“እብንሀጀረል ዐስቀላኒ ስለሰዉየዉ የሚከተለዉን አስተያየት አስፍረዋል፡-
متهم بوضع الحديث وتركيب الأسانيد
‹‹ሀዲስ በመፈብረክና የቅጥፈት ሰነድ በማደራጀት ተሀይሷል፤››}
መልስ፦
በዚህ ንግግር ውስጥ ድርብርብ ጥፋት ነው ያለው።
1ኛ. ቀጥታ እሱ ያለው ቦታ ላይ ስትገልጡ ኢብኑ ሐጀር ስለ ሀካሪ ሀ ብለው ተርጀማቸውን የጀመሩት “ዐሊይ ብኑ አሕመድ፣ #ሸይኹል_ኢስላም አቡል ሐሰን አልሀካሪይ” ብለው ነው። ይህንን ሆነ ብሎ ቆርጦ አስቀርቶታል። ለምን? ካልዋሸ ጨዋታው አይደምቅለትም። በዚሁ ኪታብ ሌላ ሁለት ቦታ ላይ እንዲሁ ሀካሪን ሸይኹል ኢስላም ብለው ጠርተውታል። [ሊሳኑል ሚዛን፡ 2/306] እና [5/337]
2ኛ. እንዲያውም “ሀዲስ በመፈብረክና የቅጥፈት ሰነድ በማደራጀት ተሀይሷል” ያሉት ኢብኑ ሐጀር አይደሉም። ይሄ በኢብኑ ነጃር ስም የቀረበ ውንጀላ ሲሆን በሚገርም ሁኔታ ያቀረቡት ዘሀቢ ናቸው። [ሚዛኑል ኢዕቲዳል፡ 3/112] ኢብኑ ሐጀር እንዲያውም "አዘጋጁ (ዘሀቢ) የኢብኑ ነጃርን ስራ ያየ አይመስልም" በማለት የዘገባ ክፍተቱ እንዲታይ በማድረግ መከላከያ ነው ያቀረቡት። ስንት ጥፋት እንደፈፀመ ተመልከቱ። የኢብኑ ሐጀር "ሊሳኑል ሚዛን" ኪታብ የዘሀቢን "ሚዛኑል ኢዕቲዳል" ተህዚብ በማድረግ የተዘጋጀ እንደሆነ ባይገባው ይሆን ብዬ ዑዝር እንዳልሰጠው ራሱ በጠቀሰው የኢብኑ ሐጀር ኪታብ ላይ የሚገኘውን ፍፁም ተቃራኒ መልእክት እንዲሰጥ አድርጎ ቆራርጦና አዛብቶ ነው ያቀረበው። ተጨማሪ ማሳያ ላቅርብ፡
3ኛ፦ ኢብኑ ሐጀር እንኳን እሱ ባለው መልኩ ሀካሪን ሊወነጅሉ እንዲያውም ደጋግመው ነው “ሸይኹል ኢስላም” ብለው የገለጿቸው። የሌሎችንም አድናቆት አስፍረዋል። ለምሳሌ የሕያ ብኑ መንደህ፡ "የሶላት፣ የዒባዳ፣ የኢጅቲሃድ ሰው ነበር" እንዳላቸው፣ ሰምዓኒይ "ዒባዳው የበዛ፣ ዛሂድነቱ ያማረ፣ ኒያው የጠራ፣ የህዝብ ቅቡልነት ያለው፣ የተከበረ ሰው ነበር" እንዳላቸው፣ እንዲሁም 0ብዱልገፋር አልከርጂ "አይኖቼ እንደሱ አይነትን ዛሂድና ደግ ሰው አላዩም" ብለው እንደገጿቸው አስፍረዋል። ይሄ ሁሉ የኢብኑ ሐጀር ሊሳኑል ሚዛን ላይ ሐሰን ታጁ በጠቀሰው ገፅ ውስጥ የሚገኝ ነው። ሐሰን ታጁ በዚህ መጠን የለየለት ወናፍ የሆነው ምን ቢነካው ነው ግን? ሱብሓነላህ!! ሰው እንዴት በራሱ ኣኺራ ላይ ይቆምራል?!
#ቅጥፈት_ሶስት
“የገረመኝ ነገር ሀዲስ ፈብርኮ በማሰራጨት ልምድ የተነቀፈን እንዲህ አይነት ስብእና ዘሀቢ ‹‹ሸይኹል ኢስላም›› በሚል ማዕረግ ጠርተዉታል።”
መልስ፦
እውን ሀካሪን \'\'ሸይኹል ኢስላም" ብለው የጠሩት ዘሀቢ ብቻ ናቸው? በጭራሽ! ይሄውና
1. ዐብዱልገፋር አልከረጂይ [አስሲየር፡ 19/68]
2. አስሰምዓኒይ (562 ሂ.) [አልአንሳብ፡ ቁ. 5260]
3ኢብኑ ዐሳኪር (571 ሂ.) [ታሪኹ ዲመሽቅ፡ 41/239]
4. ኢብኑል ሙስተውፊ (637 ሂ.) [ታሪኹ ኢርቢል፡ 1/272]
5. ኢብኑ ኸሊካን (681 ሂ.) [ወፈያቱል አዕያን፡ 3/345]
6. ኢብኑል ሙለቂን (804 ሂ.) [ጦበቃቱል አውሊያእ፡ 451]
7. ቡርሀኑዲን አልሐለቢ (841 ሂ.) [አልከሽፉል ሐሢሥ፡ 184 ቁ 497]
8. ኢብኑ ሐጀር (848 ሂ.) [ሊሳኑል ሚዛን፡ 2/306፣ 4/195 እና 5/337]
9. ተቂዩዲን አቡልፈድል ሙሐመድ ብኑ ሙሐመድ አልሃሺሚይ (871 ሂ.) [ለሕዙል አልሓዝ ቢዘይሊ ጦበቃቲል ሑፋዝ፡ 81]
10. ዐብዱልሐይ ብኑ አሕመድ ኢብኑል ዒማድ (1089 ሂ.) [ሸዘራቱ ዘሀብ፡ 5/370]
እነዚህ ሁሉ ሀካሪን “ሸይኹል ኢስላም” ብለው የጠሩ ናቸው። እነዚህ እኔ ሳስስ የገጠሙኝ ናቸው። በደንብ ዳሰሳ ቢደረግ ሌሎችም ሊኖሩ እንደሚችሉ እገምታለሁ። ይህንን ያዙና ተጠቃሹን ሰው ማለትም ሀካሪን ከዑለማእ ተነጥለው ዘሀቢ ብቻቸውን “ሸይኹል ኢስላም” በሚል ማዕረግ እንደጠሩ አድርጎ የቀጠፈውን ተመልከቱ። የቅጥፈት ማሽን የሆነ ፍጥረት!
#ቅጥፈት_አራት
“እብኑል ዑጅሚ የተባሉ የሀዲስ አስተላላፊ ስብእናዎች አጥኝም ይህንኑ መስክረዋል፡፡”
መልስ፦
1ኛ. በመጀመሪያ ዑጅሚ ሳይሆን ዐጀሚ ነው። እንዲህ አይነት ስህተቶቹ በየ ፅሁፎቹ፣ በየ መፃህፍቱ በጣም ብዙ ስለሆኑ መከታተል ይከብዳል።
2ኛ. ኪታቡ የሲብጡ ኢብኒል ዐጀሚ (የኢብኑል ዐጀሚ የልጅ ልጅ) እንጂ ቀጥታ የኢብኑል ዐጀሚ አይደለም። የኪታቡ ባለቤት ቡርሀኑዲን አልሐለቢ በሚል ነው የሚታወቁት።
3ኛ፦ በጠቀሰው ኪታብ የጠቀሰው ገፅ ላይ ስትገቡ ቀጥታ የምታገኙት እንዲህ የሚል ነው፦
عَليّ بن أَحْمد شيخ الْإِسْلَام أَبُو الْحسن الهكاري قَالَ بن النجار مُتَّهم بِوَضْع الحَدِيث وتركيب الْأَسَانِيد قَالَه الذَّهَبِيّ فِي تَرْجَمَة عبد السَّلَام بن مُحَمَّد
“ዐሊይ ብኑ አሕመድ፣ #ሸይኹል_ኢስላም አቡል ሐሰን አልሀካሪይ። ኢብኑ ነጃር፡ ‘ሐዲሥ በመፈብረክና የቅጥፈት ሰነድ በማደራጀት የሚታማ ነው’ ብለዋቸዋል። ይህንን የገለፁት ዘሀቢይ ናቸው፣ በዐብዱሰላም ብኑ ሙሐመድ ታሪክ ስር።” [አልከሽፉል ሐሢሥ፡ 497]
1/2
የቆርጦ ቅጠላው ንጉስ ዘመቻ በዘሀቢ እና በዑሉው ኪታባቸው
~
ኢብኑ ዐቂል እንዲህ ይላሉ፦
“አሽዐሪዮች ከአህሉል ሐዲሥ ጋር ባላቸው ሙግት ላይ ይዋሹባቸው ነበር።” [ረድ ዐለ'ል ዐሻዒራ፣ ኢብኑ ዐቂል፡ 91]
አቡ ኢስማዒል አልሀረዊን ለማጠልሸት ከሚሕራባቸው ውስጥ ከመስገጃቸው ስር ከነሐስ የተሰራ ጣኦት እስከ ማስቀመጥ የደረሱ ናቸው አሽዐሪዮች። [አሲየር፡ 18/512] “አላህ ወደ ቅርቢቷ ሰማይ ይወርዳል። ልክ እንደዚህ አወራረዴ!” ብሎ ከሚንበሩ ደረጃ ወርዷል ብለው ኢብኑ ተይሚያም እንዲሁ ዋሽተውባቸዋል። [ሪሕለቱ ኢብኒ በጡጣ፡ 110]
ሐሰን ታጁ እያደረገ ያለውም ይህንኑ ነው። የኢማሙ አሕመድን "ረድ 0ለ'ዘናዲቃ" እና የልጃቸው የዐብደላህን "አስሱናህ" ኪታቦች የፈጠራ ድርሰቶች ናቸው ብሎ የለየለት ቅጥፈት ፃፈ። የኢብኑል ቀይም "ጁዩሽ" ላይ ተሳለቀ። አሁን ደግሞ የቅጥፈት ጦሩ ወደ ዘሀቢ እና ወደ አልዑሉው ኪታባቸው ነው የዞረው። ባለፈው የኢማሙ አሕመድን ኪታብ ለማጣጣል የዘሀቢን ንግግር ቆርጦ ያቀረበበትን አይተናል። አሁንስ ምን ሰበብ አደረገ? በሰበብነት የመዘዘው የአቡል ሐሰን አልሀካሪን አጭር ግለ ታሪክ ነው። አልሀካሪ በሰነድ የተደገፈ “ዐቂደቱ ሻፊዒይ” የተሰኘ ኪታብ አላቸው። በዚህ ኪታብ ውስጥ ኢማሙ ሻፊዒይ ረሒመሁላህ ቀደምቶቻቸውን ያገኙበት እና የእሳቸውም ዐቂዳ አላህ ከዐርሹ በላይ ነው የሚል እንደሆነ የገለፁበት አለ። ዘሀቢ ይህንን ዐቂዳ “ሸይኹል ኢስላም አልሀካሪ ዘግቦታል” ብለው በ“አልዑሉው” ኪታባቸው አስፍረዋል። ሐሰን ታጁ ይህንን መነሻ በማድረግ ባጭር ፅሁፍ ብዙ የመቅጠፍ ክህሎቱን አሳይቶናል። ንግግሩን ቃል በቃል እያሰፈርኩ ምላሽ እሰጣለሁ። ይሄው፦
“የኢማም ዘሀቢን ‹‹አል-ዑሉዉ›› ኪታብ ሳነብ አቡል ሀሰን አልሀካሪ ስለተባሉ ስብእና በሀዲስ ሊቃዉንት የተሰጡ አስተያየቶችና ዘሀቢ ሰዉየዉን የጠሩበት ማዕረግ ትኩረቴን ሳቡት፡፡”
መልስ፦
አል-ዑሉዉ ኪታብ ላይ ስለ ሀካሪ ከዘሀቢ ምስክርነት ውጭ የሌሎች የሐዲሥ ሊቃውንት ምንም አይነት አስተያየት የለም። ይሄ ሰውዬ እንዲሁ ከመሬት አንስቶ ነው የሚቀደደው።
{“እብንሀጀረል ዐስቀላኒ ስለሰዉየዉ የሚከተለዉን አስተያየት አስፍረዋል፡-
متهم بوضع الحديث وتركيب الأسانيد
‹‹ሀዲስ በመፈብረክና የቅጥፈት ሰነድ በማደራጀት ተሀይሷል፤››}
መልስ፦
በዚህ ንግግር ውስጥ ድርብርብ ጥፋት ነው ያለው።
1ኛ. ቀጥታ እሱ ያለው ቦታ ላይ ስትገልጡ ኢብኑ ሐጀር ስለ ሀካሪ ሀ ብለው ተርጀማቸውን የጀመሩት “ዐሊይ ብኑ አሕመድ፣ #ሸይኹል_ኢስላም አቡል ሐሰን አልሀካሪይ” ብለው ነው። ይህንን ሆነ ብሎ ቆርጦ አስቀርቶታል። ለምን? ካልዋሸ ጨዋታው አይደምቅለትም። በዚሁ ኪታብ ሌላ ሁለት ቦታ ላይ እንዲሁ ሀካሪን ሸይኹል ኢስላም ብለው ጠርተውታል። [ሊሳኑል ሚዛን፡ 2/306] እና [5/337]
2ኛ. እንዲያውም “ሀዲስ በመፈብረክና የቅጥፈት ሰነድ በማደራጀት ተሀይሷል” ያሉት ኢብኑ ሐጀር አይደሉም። ይሄ በኢብኑ ነጃር ስም የቀረበ ውንጀላ ሲሆን በሚገርም ሁኔታ ያቀረቡት ዘሀቢ ናቸው። [ሚዛኑል ኢዕቲዳል፡ 3/112] ኢብኑ ሐጀር እንዲያውም "አዘጋጁ (ዘሀቢ) የኢብኑ ነጃርን ስራ ያየ አይመስልም" በማለት የዘገባ ክፍተቱ እንዲታይ በማድረግ መከላከያ ነው ያቀረቡት። ስንት ጥፋት እንደፈፀመ ተመልከቱ። የኢብኑ ሐጀር "ሊሳኑል ሚዛን" ኪታብ የዘሀቢን "ሚዛኑል ኢዕቲዳል" ተህዚብ በማድረግ የተዘጋጀ እንደሆነ ባይገባው ይሆን ብዬ ዑዝር እንዳልሰጠው ራሱ በጠቀሰው የኢብኑ ሐጀር ኪታብ ላይ የሚገኘውን ፍፁም ተቃራኒ መልእክት እንዲሰጥ አድርጎ ቆራርጦና አዛብቶ ነው ያቀረበው። ተጨማሪ ማሳያ ላቅርብ፡
3ኛ፦ ኢብኑ ሐጀር እንኳን እሱ ባለው መልኩ ሀካሪን ሊወነጅሉ እንዲያውም ደጋግመው ነው “ሸይኹል ኢስላም” ብለው የገለጿቸው። የሌሎችንም አድናቆት አስፍረዋል። ለምሳሌ የሕያ ብኑ መንደህ፡ "የሶላት፣ የዒባዳ፣ የኢጅቲሃድ ሰው ነበር" እንዳላቸው፣ ሰምዓኒይ "ዒባዳው የበዛ፣ ዛሂድነቱ ያማረ፣ ኒያው የጠራ፣ የህዝብ ቅቡልነት ያለው፣ የተከበረ ሰው ነበር" እንዳላቸው፣ እንዲሁም 0ብዱልገፋር አልከርጂ "አይኖቼ እንደሱ አይነትን ዛሂድና ደግ ሰው አላዩም" ብለው እንደገጿቸው አስፍረዋል። ይሄ ሁሉ የኢብኑ ሐጀር ሊሳኑል ሚዛን ላይ ሐሰን ታጁ በጠቀሰው ገፅ ውስጥ የሚገኝ ነው። ሐሰን ታጁ በዚህ መጠን የለየለት ወናፍ የሆነው ምን ቢነካው ነው ግን? ሱብሓነላህ!! ሰው እንዴት በራሱ ኣኺራ ላይ ይቆምራል?!
“የገረመኝ ነገር ሀዲስ ፈብርኮ በማሰራጨት ልምድ የተነቀፈን እንዲህ አይነት ስብእና ዘሀቢ ‹‹ሸይኹል ኢስላም›› በሚል ማዕረግ ጠርተዉታል።”
መልስ፦
እውን ሀካሪን ''ሸይኹል ኢስላም" ብለው የጠሩት ዘሀቢ ብቻ ናቸው? በጭራሽ! ይሄውና
1. ዐብዱልገፋር አልከረጂይ [አስሲየር፡ 19/68]
2. አስሰምዓኒይ (562 ሂ.) [አልአንሳብ፡ ቁ. 5260]
3ኢብኑ ዐሳኪር (571 ሂ.) [ታሪኹ ዲመሽቅ፡ 41/239]
4. ኢብኑል ሙስተውፊ (637 ሂ.) [ታሪኹ ኢርቢል፡ 1/272]
5. ኢብኑ ኸሊካን (681 ሂ.) [ወፈያቱል አዕያን፡ 3/345]
6. ኢብኑል ሙለቂን (804 ሂ.) [ጦበቃቱል አውሊያእ፡ 451]
7. ቡርሀኑዲን አልሐለቢ (841 ሂ.) [አልከሽፉል ሐሢሥ፡ 184 ቁ 497]
8. ኢብኑ ሐጀር (848 ሂ.) [ሊሳኑል ሚዛን፡ 2/306፣ 4/195 እና 5/337]
9. ተቂዩዲን አቡልፈድል ሙሐመድ ብኑ ሙሐመድ አልሃሺሚይ (871 ሂ.) [ለሕዙል አልሓዝ ቢዘይሊ ጦበቃቲል ሑፋዝ፡ 81]
10. ዐብዱልሐይ ብኑ አሕመድ ኢብኑል ዒማድ (1089 ሂ.) [ሸዘራቱ ዘሀብ፡ 5/370]
እነዚህ ሁሉ ሀካሪን “ሸይኹል ኢስላም” ብለው የጠሩ ናቸው። እነዚህ እኔ ሳስስ የገጠሙኝ ናቸው። በደንብ ዳሰሳ ቢደረግ ሌሎችም ሊኖሩ እንደሚችሉ እገምታለሁ። ይህንን ያዙና ተጠቃሹን ሰው ማለትም ሀካሪን ከዑለማእ ተነጥለው ዘሀቢ ብቻቸውን “ሸይኹል ኢስላም” በሚል ማዕረግ እንደጠሩ አድርጎ የቀጠፈውን ተመልከቱ። የቅጥፈት ማሽን የሆነ ፍጥረት!
“እብኑል ዑጅሚ የተባሉ የሀዲስ አስተላላፊ ስብእናዎች አጥኝም ይህንኑ መስክረዋል፡፡”
መልስ፦
1ኛ. በመጀመሪያ ዑጅሚ ሳይሆን ዐጀሚ ነው። እንዲህ አይነት ስህተቶቹ በየ ፅሁፎቹ፣ በየ መፃህፍቱ በጣም ብዙ ስለሆኑ መከታተል ይከብዳል።
2ኛ. ኪታቡ የሲብጡ ኢብኒል ዐጀሚ (የኢብኑል ዐጀሚ የልጅ ልጅ) እንጂ ቀጥታ የኢብኑል ዐጀሚ አይደለም። የኪታቡ ባለቤት ቡርሀኑዲን አልሐለቢ በሚል ነው የሚታወቁት።
3ኛ፦ በጠቀሰው ኪታብ የጠቀሰው ገፅ ላይ ስትገቡ ቀጥታ የምታገኙት እንዲህ የሚል ነው፦
عَليّ بن أَحْمد شيخ الْإِسْلَام أَبُو الْحسن الهكاري قَالَ بن النجار مُتَّهم بِوَضْع الحَدِيث وتركيب الْأَسَانِيد قَالَه الذَّهَبِيّ فِي تَرْجَمَة عبد السَّلَام بن مُحَمَّد
“ዐሊይ ብኑ አሕመድ፣ #ሸይኹል_ኢስላም አቡል ሐሰን አልሀካሪይ። ኢብኑ ነጃር፡ ‘ሐዲሥ በመፈብረክና የቅጥፈት ሰነድ በማደራጀት የሚታማ ነው’ ብለዋቸዋል። ይህንን የገለፁት ዘሀቢይ ናቸው፣ በዐብዱሰላም ብኑ ሙሐመድ ታሪክ ስር።” [አልከሽፉል ሐሢሥ፡ 497]
1/2