UMMA TOKEN INVESTOR

About me

ምን ነበርን ኢስላምን ባናገኝ ? አልሀምዱሊላህ ኢስላምን ለከውኑ ለለገስከው አላህ

Translation is not possible.

የዶክተር ዛኪር የፍርድ ሂደት ተጠናቀቀ፣ 320ሺ ዶላር ካሳውንም ለፍልስጤማውያን ይሁንልኝ ብሏል።

ጉዳዩ እንዲህ ነው። በአንድ ወቅት ዶክተር ዛኪር የማሌዥያ ራስገዝ አስተዳደር ወደሆነችው ፒናንግ ንግግር ያደርግ ዘንድ ተጋብዞ ይሄዳል።

በወቅቱ አንድ መቶ ሺ ህዝብ ታድሞ በቀረበው ንግግር ተደስቶ ፕሮግራሙ ይጠናቀቃል። ከዚያ በዃላ ሁኔታው ያልተዋጠላቸው በሃገሪቱ መንግስታዊ ስርአት ውስጥ ያሉ ግለሰቦች ዛኪርን አሸባሪ፣ የጥላቻ ንግግር ሰባኪ በሚል መውቀስና መስደብ ጀመሩ። ዛኪር ስለጉዳዩ ሲያብራራ እንዲህ ይላል

«አምስት ናቸው። ሳጣራ ሁሉም ፖለቲከኞች ሲሆኑ የህንድ ዝርያ ያላቸው ናቸው። ይህንን ጉዳይ ዝም ማለት ስላልፈለኩ ወደ ፍርድ ቤት ሄጄ ከሰስኩኝ። ከአምስቱ አራቱ በነገሩ በመደናገጣቸው ይቀርታ በመጠየቅ ጉዳዩ እንዲዘጋ አናገሩኝ። እኔም ይቅርታ አደረኩላቸው። አንደኛው ግን የወቅቱ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስቴር አቶ ራማሳይ ጥላቻቸው ጥግ የደረሰ በመሆኑ የክስ ሂደቱ እንዲቀጥል አደረኩኝ።»

ዶክተር ዛኪር አሁን የሚገኘው ናይጀሪያ ነው። ሰሞኑን ከሶስት ወር በፊት በተደረገለት ግብዣ ወደ ናይጀሪያ ተጉዞ በየአካባቢው ንግግር በማድረግ ላይ ይገኛል። በርካታ ሰዎችም እስልምናን በመቀበል ላይ ናቸው።

ታዲያ ያኔ ግብዣ ሲደረግለት ጠበቃው ክስ እንዳለበትና ኖቬምበር 2 ፍርድ እንዳለውና እንዳይንቀሳቀስ ይነግረዋል። ዛኪር ግን ግብዣ ተቀብያለሁና መቅረት አልችልም የሚወሰነውን እቀበላለሁ ብሎ ነበር ወደናይጀሪያ ያመራው።

ዶክተር ዛኪር ኖቬምበር 2 የነበረውን ግብዣ ተከትሎ በናይጀሪያ ንግግር ሲያደረግ የመረጠው ርእሰ ጉዳይ የፍልስጤምን ሰቆቃና የሙስሊሙን ሃላፊነት ነበር። ይህንን ንግግር እያደረገ ስለነበረው የክስ ሂደት ካብራራ በዃላ ዛሬ የፍርድ ሂደቱ ከሁለት አመት በዃላ ተጠናቀቀ፣ ዳኛውም ስሜን በማጥፋት በደል ለፈፀመብኝና ጥላቻውን ለገለፀው የቀድም ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ጥፋተኛ ብሎታል ሲል ገለፀ።

የፍርድ ሂደቱን ተከትሎም በ30 ቀናት ውስጥ 1ሚሊዮን 4መቶ 20ሺ የማሌዥያ ገንዘብ ወይንም 320ሺ ዶላር ለዶክተር ዛኪር ናይክ ካሳ እንኪፍል ውሳኔ ተሰጠ። 320ሺ የአሜሪካን ዶላር በኛ ሃገር በባንክ ምንዛሬ ከ16ሚሊዮን ብር በላይ ነው።

ዶክተር ዛኪር ናይክም በመድረኩ ባደረገው ንግግር ይህንን የቅጣት ገንዘብ ሙሉ በሙሉ ለፍልስጤም እርዳታ እንዲውል መወሰኑን አሳውቋል።

ይህ ትንሹ ለወንድምና እህቶቼ የማደርገው ነው ሲል ገልፁዋል።

ዶክተር ዛኪር ከህንድ በስደት ማሌዥያ የሚኖር ሲሆን በተለያየ መንገድ ዛሬም ዳዕዋውን አስቀጥሏል። በርካታ የኢስላም ጥላቻ የተጠናወታቸው አካላት ዛሬም እሱን መክሰሳቸውና ማሳደዳቸውን አላቆሙም። እሱም ከጥሪውና የአላህን መንገድ ከማስተዋወቅ አልተወገደም።

አቡሐኒፋ - ሙሀመድ ሰዒድ

image
image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

ይህን ሰምና ወርቅ ያዘለ ጹሁፍ አምብቡልኝማ

እንደ ሰማሁት በጹሁፍ ቀይሄ አመጣሁላችሁ

አንድ ታላቅ የአረቡ አለም አሊም በዳአዋ መድረካቸው ላይ ያጋሩት ኮመዲ አዘል ቁም ነገር ያለው ንግግር ነው ።

።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

አንድ መንድር ላይ የሚኖር እጅግ በጣም አጭበርባሪ

ሰው ነበር ይህ ሰው ህይወቱ የሚመራው አጭበርብሮ በሚያገኘው ገንዘብ ነው

አንድ አህያ ነበረችው አንድ ቀን አህያው አፍዋን ከፍቶ ወርቅ ሞላባት እና ገቢያ ሊሸጣት አወጣት

አህያይቱ ገቢያው ላይ አስጮሀት ስትጮህ ከአፍዋ ወርቆቹ ወዳደቁ ገበያተኞቹ ተገመው ያዩዋት ሊገዙዋት ቋመጡ ስንት ናት ስንት እቺ ወርቅ ምትተፋ አህያ እያሉ ገቢያው አደሩለት እሱም ውድ ነው ውድ ነው እያለ አጓራ አንዱ ቱጃር በውድ ዋጋ ገዝቶት ቤቱ ወሰዳት ቤት አስገብቶ ቢያጮሀት ከአፍዋ ምንም ጠብ አላለም

በቃ ተሸወድኩ አለና የሰፈሩን ሰው ይዞ አጭበርባሪውን ሰው ፍለጋ ሄዱ እና ቤቱ ደረሱ እሱ ከሩቅ አይቶዋቸው ስለ ነበር ተደበቀ ቤቱ ሲገቡ ሚስቱ ነው ያለችው ባልሽ ሸውዶናል የት አለ አሉዋት እስዋም አሁን ወጣ ቆዩ ይሄ ውሻ ልላክበት አለችና አንድ ውሻ ፈትታ ለቀቀች እናተ እዚህ አረፍ በሉ ውሻይ ይዞት ይመጣል አለቻቸው

ትንሽ እንደ ቆዩ ሰውየው ውሻውን ይዞ መጣ

ሰዎቹ ተገረሙ የመጡበት ጉዳይ ረስተው ይሄ ለማዳ ውሻህ እንግዛህ እያሉ ቤቱን ገቢያ አደረጉት እሱም በውድ ዋጋ ለአንዱ ሸጠለት ገዢው ቤት ወስዶ ውሻው ለአደን አሰማራው በዛው ጠፍቶ ቀረ አሁምን ተመልሰው ሸወደን ያ ሰው እንሂድ ብለው ቤቱ ገቡ ሲገቡ የለም ሚስቱ ናት ያለችው የት አለ ባልሽ ሸውዶናል አሉዋት ቆዩ ልጥራው ብላ ጠርታው መጣች

ልክ ሲገባ ቡና አላፈላሽላቸውም አላት እስዋም አው አለች

ለምን አለና ሚስቱን በአቴፊሻል ጩቤ ወጋት እስዋም ነገሩን ስለ ምታቅ ቀድማ በልብስዋ ውስጥ ደም መሳይ ነገር ይዛ ነበርና እሱን አፍሳ ወደቀች ሰዎቹ ግራ ገባቸው

አጭበርባሪው ሰውዬ ቆዩ ቆዩ አንዴ አለና ከኪሲ የሆነ ዋሽት መሳይ ነገር አውጥቶ በዋሽንት አጠገብዋ ሄዶ አዜመለት እስዋም ተነስታ ቆመች ከዛ ቡና አፈላች እየጠጡ ሳላ ይሄ ጉደኛ ዋሽትህ ሽጥልን አሉት እሱም ይሄማ ውድ ነው አላቸው ቢሆንም ሽጥልን የኛ እዳ አለብህ አሉት እሱም እሺ ብሎ ለአንዱ ሸጠለት ።

ገዢው ቤት ገባና ለሚስቱ ውዴ ገራሚ ዋሽት ገዛሁ አለና ሚስቱን በጩቤ ወጋት ዋሽቱ ቢነፋ ቢነፋ ሚስቱ ሆዬ አሸልባለች ለጎረቤቱ ሞክርልኝ ብሎ ሰጠው እስም ሚስቱን ወግቶ ዋሽቱ ሚለው ቢለው አሸልባች በዚህ መልኩ መላው የመደሬው ሰዎች ሚስቶቻቸገ ገደሉ

አባ ወራዎቹ ተናደው ገንፍለው ያን አጭቤ ሰው በቁም አገለውም ባህር ውስጥ ነው ምንጨምረው ብለው ዝተው አጭቤው ጋር መጡ

አፍነው ያዙት መዳበሪያ ውስጭ ጨምረው ተሸከመው

ባህር ወደ አለበት እሩቅ መንገድ ጉዞ ጀመሩ

በጉዞ መሀል አረፍ አሉ ደካም አለና እንቅልፍ ሸለባቸው

አጭቤው ሰው ከመዳበሪያው ውስጥ በንቃት አለ

አንድ ምስኪን ገበሬ በዛጋ አለፈ እከሌ ብሎ ጠራው ፍታኝ አለው ማን ነው ያሰረህ አለው እነዛ ሰዎች በግድ አግባ ትዳር ያዝ አሉኝ እና አንዲት የሀብታም ልጅ ሊድሩኝ ነው እኔ እንቢ ስለ አሉኩ ነው አለው ገበሬው ሰው ፈታው

አጭቤው ሰው ለምን አንተ አታገባትም እቺን ሀብታብ እንስት አለው እሺ አገባታለሁ አለ ገበሬው በቃ ና በኔ ቦታ ብሎ ገበሬው በመዳበሪያ አስሮ ወደ ቤቱ አቀና

ሰዎቹ ከእቅልፍ እንደ ነቁ ማዳበሪያው ተሸክነው ባህር ውስጥ ጣሉት ገበሬው በማያቀው ነገር ተሰዋ ሰዎቹ ሰፈራቸው ሲመለሱ አጭቤው ሰው አለ ተገረሙ እንዴት መጣህ አሉት እናንተ ከባህሩ እንደ ጣላቹኝ አንዲት ልእት ልጅ አገኘችን ማዳበሪያው ፈታ ብርም ሰጥታ ከባሽሩ አወጣችኝ እንዳምው አለችኝ አለ አጭቤው ምን አለችህ አሉት የባህሩ ዳር ላይ ስለ ጣሉህ እኔ አገኘሁህ መሀል ላይ ቢጥሉህ ኖሮ ታላቅ እህቴ አግታህ ብዙ ብር ትሰጥህ ነበር አለችኝ አላቸው እና ታላቅ እህትዋ ከባህሩ መሀል ላይ አለች አሉት አው አላቸው በቃ እኛም ሄደን ብር አናምጣ ብለው ከባህሩ መሀል ላይ ሰምጠው ቀሩ

አጭበርባሪው ሰውዬ ብቻውን ከሚስቱ ጋር መንደሩን እንደ ፈለገ ይኖርበት ጀመር ።

ታሪክ አበቃ ቁም ነገሩ ወዲህ ነው

ያ አጭበርባሪው ሰው እስራኤል ነው

ሚስቱ አሜሪካ ናት

ህዝቦቹ አረቦች ናቸው ።

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

በጦር ሜዳ በተሰዋው የቀሳም ሙጃሂድ ኪስ ውስጥ የተገኘ ደብዳቤ። የወራሪዋ ጦር መሪ ለወታደሮቹ እያሳየ ደብዳቤው እንዲህ ይላል:-

"በኸይበር ጌታ በአላህ ስም እንጀምራለን

በዙልፊቀርም ሰይፍ ሰንዝረን እንመታለን።

ወራሪዋ ጠላትህ ናት። ልክ እንደ በሽታ። ግንባር ደረቱን ልብና ጉበቱ ላይ አነጣጥረህ ከመምታት በቀር ምንም ዓይነት መድኃኒት የሌለው በሽታ መሆኑን እወቅ። አጥፋቸው የአቡ ሱለይማንን የኻሊድን ሰይፍ ተጠቅመህ ሰንዝርባቸው"

በኸይበር ጌታ በአላህ ስም እንጀምራለን

በዙልፊቀርም ሰይፍ ሰንዝረን እንመታለን

Mahi Mahisho

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

አሰላም ዋአለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱ

እንዴት ናቹህ የኡማ ላይፍ ቤተሰቦች ።

ኧረ ፎሎ እንደራረግ የኛን ነገር ከፍ ከፍ ማረግ ለምድነው ግን ሚከብደን ሀይይይይይ ዳይ ፎሎ ተደራረጉ

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

እናትና ልጅ በጠባቧ ክፍላቸው ውስጥ ተቀምጠዋል።

"እማ ርቦኛል" አለ ዩሱፍ ሆዱን እያሻሸ።

"ሀቢቢ ትንሽ ጠብቀኝ ቲማቲም ስልስ እሰራልሃለሁ" አለች እናት ፀጉሩን እያሻሸች።

ቤት ውስጥ የሚላስ የሚቀመስ ባለመኖሩ የዩሱፍን ርሐብ ለማስታገስ ሁለት የቲማቲም ዘለላዎችን ፍለጋ ከቤት ወጣሁ። በበር በኩል አጮለቅኩና እስክመለስ በሩን እንዲዘጋ ነገርኩትና ወደ ጎረቤታችን ቤት አቀናሁ። ደጋግሜ አንኳኳሁ። መልስ የሚሰጠኝ አላገኘሁም። ከመንገዱ ማዶ ወደሚገኘው ወደ ኡሙ ሚቅዳድ ቤት አመራሁ።

አንኳኩቼ ገባሁ። እንዴት ነሽ ልጆችሽስ ብዬ ሰላምታን አቀረብኩላት።

"አልሀምዱሊላህ ደህና ነን አላህ ይጠብቀን" ብላ መለሰችልኝ።

እያንዳንዱ ሰከንድ የመጨረሻ ሊሆን ይችላልና እኛ ፍልስጤማዊያን ጦርነት ውስጥ ስንሆን እንዲህ ነን ብዙ አንናገርም።

"ባለቤቴ ውሎ አዳሩ ሆስፒታል ሆኗል። ጦርነቱ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ ወደ ቤት አልተመለሰም። አልሐምዱሊላህ" አልኩና ቲማቲም ካላት እንድትሰጠኝ ጠየቅኳት። በፌስታል ቋጥራ ያቀበለችኝን ቲማቲም ይዤ ልወጣ ስል "ሁኔታዎች ከባድ ሆነዋል በዱዓ እንተዋወስ" አለችኝ።

"በአላህ እርዳታ ይህ ሁሉ ያልፋል ኢንሻ አላህ..." እያልኳት ገና ንግግሬን ሳልጨርስ ከባድ ፍንዳታ ተሰማ። በጥቁር ደመና አየሩን ተሸፈነ። አካባቢው በአቧራ ተሞላ። አእምሮዬ የዩሱፍን ስም አቃጨለ። ከራሴ ጋር እየታገልኩ ወደ ጎዳናው ሮጥኩ። ሁሉም ይጮኻል።

ዩሱፍን አይታችዋል..? እዚህ አካባቢ አንድ ትንሽ ፍሪዝ የሆነ ልጅ አጊኝታችኋል? እያልኩ ጮኽኩ። መልስ የሰጠኝ ማንም አልነበረም። በአንቡላንስ ተጭኜ ሄድኩ። የመኪናው በር ሲዘጋ በዩሱፍ ላይ የዘጋሁት በር ታወሰኝ።

እየተብሰለሰልኩ አሽ-ሺፋእ ሆስፒታል ደረስኩ። ዩሱፍ....የሱፍ.... ብዬ ተጣራሁ። ለአላፊ አግዳሚው የ7 አመት ቆንጅዬ ልጄን አይታቹታልን? እያልኩ ጠየቅኩ።

የዓይኔ ማረፍያ ባለጥቅልል ፀጉሩ ጥቃቱ ፊቱን ከማበላሸቱ በፊት ቆንጆ ምስሉን በአእምሮዬ ሳልኩ። ፍርስራሽ አቧራ ከሰውነቱ ጋር ተጣብቆ በደም ተጨማልቆ አልጋ ላይ ተንጋሎ አገኘሁት። ዩሱፍ በባዶ ሆዱ ጌታውን ተገናኘ።

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group