ترجمہ ممکن نہیں

ይህን ሰምና ወርቅ ያዘለ ጹሁፍ አምብቡልኝማ

እንደ ሰማሁት በጹሁፍ ቀይሄ አመጣሁላችሁ

አንድ ታላቅ የአረቡ አለም አሊም በዳአዋ መድረካቸው ላይ ያጋሩት ኮመዲ አዘል ቁም ነገር ያለው ንግግር ነው ።

።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

አንድ መንድር ላይ የሚኖር እጅግ በጣም አጭበርባሪ

ሰው ነበር ይህ ሰው ህይወቱ የሚመራው አጭበርብሮ በሚያገኘው ገንዘብ ነው

አንድ አህያ ነበረችው አንድ ቀን አህያው አፍዋን ከፍቶ ወርቅ ሞላባት እና ገቢያ ሊሸጣት አወጣት

አህያይቱ ገቢያው ላይ አስጮሀት ስትጮህ ከአፍዋ ወርቆቹ ወዳደቁ ገበያተኞቹ ተገመው ያዩዋት ሊገዙዋት ቋመጡ ስንት ናት ስንት እቺ ወርቅ ምትተፋ አህያ እያሉ ገቢያው አደሩለት እሱም ውድ ነው ውድ ነው እያለ አጓራ አንዱ ቱጃር በውድ ዋጋ ገዝቶት ቤቱ ወሰዳት ቤት አስገብቶ ቢያጮሀት ከአፍዋ ምንም ጠብ አላለም

በቃ ተሸወድኩ አለና የሰፈሩን ሰው ይዞ አጭበርባሪውን ሰው ፍለጋ ሄዱ እና ቤቱ ደረሱ እሱ ከሩቅ አይቶዋቸው ስለ ነበር ተደበቀ ቤቱ ሲገቡ ሚስቱ ነው ያለችው ባልሽ ሸውዶናል የት አለ አሉዋት እስዋም አሁን ወጣ ቆዩ ይሄ ውሻ ልላክበት አለችና አንድ ውሻ ፈትታ ለቀቀች እናተ እዚህ አረፍ በሉ ውሻይ ይዞት ይመጣል አለቻቸው

ትንሽ እንደ ቆዩ ሰውየው ውሻውን ይዞ መጣ

ሰዎቹ ተገረሙ የመጡበት ጉዳይ ረስተው ይሄ ለማዳ ውሻህ እንግዛህ እያሉ ቤቱን ገቢያ አደረጉት እሱም በውድ ዋጋ ለአንዱ ሸጠለት ገዢው ቤት ወስዶ ውሻው ለአደን አሰማራው በዛው ጠፍቶ ቀረ አሁምን ተመልሰው ሸወደን ያ ሰው እንሂድ ብለው ቤቱ ገቡ ሲገቡ የለም ሚስቱ ናት ያለችው የት አለ ባልሽ ሸውዶናል አሉዋት ቆዩ ልጥራው ብላ ጠርታው መጣች

ልክ ሲገባ ቡና አላፈላሽላቸውም አላት እስዋም አው አለች

ለምን አለና ሚስቱን በአቴፊሻል ጩቤ ወጋት እስዋም ነገሩን ስለ ምታቅ ቀድማ በልብስዋ ውስጥ ደም መሳይ ነገር ይዛ ነበርና እሱን አፍሳ ወደቀች ሰዎቹ ግራ ገባቸው

አጭበርባሪው ሰውዬ ቆዩ ቆዩ አንዴ አለና ከኪሲ የሆነ ዋሽት መሳይ ነገር አውጥቶ በዋሽንት አጠገብዋ ሄዶ አዜመለት እስዋም ተነስታ ቆመች ከዛ ቡና አፈላች እየጠጡ ሳላ ይሄ ጉደኛ ዋሽትህ ሽጥልን አሉት እሱም ይሄማ ውድ ነው አላቸው ቢሆንም ሽጥልን የኛ እዳ አለብህ አሉት እሱም እሺ ብሎ ለአንዱ ሸጠለት ።

ገዢው ቤት ገባና ለሚስቱ ውዴ ገራሚ ዋሽት ገዛሁ አለና ሚስቱን በጩቤ ወጋት ዋሽቱ ቢነፋ ቢነፋ ሚስቱ ሆዬ አሸልባለች ለጎረቤቱ ሞክርልኝ ብሎ ሰጠው እስም ሚስቱን ወግቶ ዋሽቱ ሚለው ቢለው አሸልባች በዚህ መልኩ መላው የመደሬው ሰዎች ሚስቶቻቸገ ገደሉ

አባ ወራዎቹ ተናደው ገንፍለው ያን አጭቤ ሰው በቁም አገለውም ባህር ውስጥ ነው ምንጨምረው ብለው ዝተው አጭቤው ጋር መጡ

አፍነው ያዙት መዳበሪያ ውስጭ ጨምረው ተሸከመው

ባህር ወደ አለበት እሩቅ መንገድ ጉዞ ጀመሩ

በጉዞ መሀል አረፍ አሉ ደካም አለና እንቅልፍ ሸለባቸው

አጭቤው ሰው ከመዳበሪያው ውስጥ በንቃት አለ

አንድ ምስኪን ገበሬ በዛጋ አለፈ እከሌ ብሎ ጠራው ፍታኝ አለው ማን ነው ያሰረህ አለው እነዛ ሰዎች በግድ አግባ ትዳር ያዝ አሉኝ እና አንዲት የሀብታም ልጅ ሊድሩኝ ነው እኔ እንቢ ስለ አሉኩ ነው አለው ገበሬው ሰው ፈታው

አጭቤው ሰው ለምን አንተ አታገባትም እቺን ሀብታብ እንስት አለው እሺ አገባታለሁ አለ ገበሬው በቃ ና በኔ ቦታ ብሎ ገበሬው በመዳበሪያ አስሮ ወደ ቤቱ አቀና

ሰዎቹ ከእቅልፍ እንደ ነቁ ማዳበሪያው ተሸክነው ባህር ውስጥ ጣሉት ገበሬው በማያቀው ነገር ተሰዋ ሰዎቹ ሰፈራቸው ሲመለሱ አጭቤው ሰው አለ ተገረሙ እንዴት መጣህ አሉት እናንተ ከባህሩ እንደ ጣላቹኝ አንዲት ልእት ልጅ አገኘችን ማዳበሪያው ፈታ ብርም ሰጥታ ከባሽሩ አወጣችኝ እንዳምው አለችኝ አለ አጭቤው ምን አለችህ አሉት የባህሩ ዳር ላይ ስለ ጣሉህ እኔ አገኘሁህ መሀል ላይ ቢጥሉህ ኖሮ ታላቅ እህቴ አግታህ ብዙ ብር ትሰጥህ ነበር አለችኝ አላቸው እና ታላቅ እህትዋ ከባህሩ መሀል ላይ አለች አሉት አው አላቸው በቃ እኛም ሄደን ብር አናምጣ ብለው ከባህሩ መሀል ላይ ሰምጠው ቀሩ

አጭበርባሪው ሰውዬ ብቻውን ከሚስቱ ጋር መንደሩን እንደ ፈለገ ይኖርበት ጀመር ።

ታሪክ አበቃ ቁም ነገሩ ወዲህ ነው

ያ አጭበርባሪው ሰው እስራኤል ነው

ሚስቱ አሜሪካ ናት

ህዝቦቹ አረቦች ናቸው ።

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group