Rabia abdellah Profile Picture
UMMA TOKEN INVESTOR

Translation is not possible.
ኢየሱስ ሲመጣ "የእስራኤል/አይሁድ ንጉስ" ተብሎ ነው የሚመጣውና እስራኤላውያን ያሻውን ያክል ግፈኛ ቢሆኑም በግፋቸው ሳቢያ እንዲጠፉ አንመኝም፥ ምክንያቱም እነሱ ከጠፉ ኢየሱስ "ንጉስ" ተብሎ በትንቢቱ መሠረት የሚጠራበት ህዝብ አይኖርም ማለት ነው 🤦‍♂️ አንዳንድ ክርስቲያን ወገኖቼ ሎጂክን አስገድዳችሁ የምትደፍሩበት መንገድ ያሳዝነኛል።
1/ ኢየሱስ እንደ እናንተ እሳቤ አምላክ እንደመሆኑ መጠን ንጉስነቱ ለአለም እንጅ ለእስራኤላውያን ብቻ አይደለም። ሲመጣ አሁንም እስራኤላውያን ጋ የሚነግሴ አህዛብ የማይመለከቱት ሰው ነው ብላችሁ ነው የምታምኑት?
2/ ይህ ማለትኮ የምበላበት ሳህን የፈለገ ቆሻሻ ቢያርፍበት በሱ ለመብላት ስለወሰንኩ ሳላጸዳው ከነቆሻሻው እበላበታለሁ እንደማለት ነው። ለኢየሱስ ያላችሁ አመለካከት በዚህ ግፍ የታጠረ ነው?
3/ ኢየሱስ ለንግስና ስያሜው ብቻ ተጨንቆ ያንን ሁሉ ግፍ የሚፈጽሙ ህዝቦችን /እሱን መስቀል ጨምሮ/ እንዲሁ በፍርደ ገምድልነት ችላ ይላቸዋል ብላችሁ ታምናላችሁ?
4/ ኢየሱስ እንደ እናንተ እሳቤ የዚህ ግፍና በደል አጽዳቂ ነው ብላችሁ ታምናላችሁ? ጽዮናውያን የሚሰሩትን ግፍ እናንተ ስትደግፉ አምላካችሁ ጋ ተመሳሳይ አፕሩቫል እንዳለ ታምናላችሁ ማለት ነው? ታዲያ እንዲያ ከሆነ ኢየሱስንም መግደላቸውም ልክ ነበር ማለት ነው?
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.
ሽማግሌ__ነው
.
በህይወቱ ያሳለፋቸውን ምኞቶቹን ሲያወጋ እንዲህ ይላል:— "አላህ መልካም
ትዳር እንዲሰጠኝ ተመኘሁ። ሆኖልኝ መልካም ሴት አገባሁ።
.
…ነገርግን ትዳር ያለ ልጅ አይሞቅምና አላህ ልጆች እንዲሰጠኝ ተመኘሁ።
ህልሜም እውን ሆነ። ልጆች ተወለዱልኝ።
.
…ነገርግን ብዙም ሳልቆይ የቤቴ ጥበት ሰለቸኝ። ጋርደን ያለው ሰፊ ቤት
እንዲኖረኝ ተመኘሁ። ከብዙ ውጣ ውረድ በኋላ ተሳካልኝ። የተመኘሁትን ቤት
ገነባሁ።
.
…ነገርግን አሁን ደግሞ ልጆቼ ደርሰዋል። ስለዚህ ወግ መዕረጋቸውን ለማየት
ተመኘሁ። ውጥኔ ተሳካና አገቡ።
.
…ነገርግን ሥራ ሰልችቶኛል። የህይወትን ግብግብን መወጣት አልቻልኩም።
ስለዚህ ጡረተኛ በመሆን እረፍት ማግኘት ተመኘሁ። ተሳካልኝ።
.
…ነገርግን አሁን ቀድሞ እንደነበርኩት ብቸኛ ሆኛለሁ። እንደውም ከቀድሞው
የሚከፋው ድሮ ወደ ህይወት እየቀረብኩ፣ ኑሮ እየመሰረትኩ ነበር። አሁንስ?!
ለጉዞ እየተሰናዳው ሞቴን እየጠበኩኝ። ወደፊት ይመጣል ብዬ የምጠብቀው
ምንም ዓለማዊ ነገር የለም።
.
…ነገርግን አሁንም መመኘት አላቆምኩም።…ቁርኣን መሐፈዝ ተመኘሁ። ነገርግን
የማስታወስ ችሎታዬ ተዳክሟል። መጾም ተመኘሁ። ነገርግን ጤናዬ ተቃውሷል።
አልቻልኩም። ለሊት መስገድ ተመኘሁ። ነገርግን እግሬ ሊሸከመኝ
አልተቻለውም።…"
.
#ነቢዩ (ሰዐወ) እንዲህ ብለዋል:— "አምስት ነገሮችን ከአምስት ነገሮች በፊት
ተጠቀምባቸው:
— ወጣትነትህን ከእርጅና በፊት
— ከህመምህ በፊት ጤናህን
— ኃብትህን ከድህነትህ በፊት
— በሥራ ከመጠመድህ በፊት ትርፍ ጊዜህን
—ከመሞትህ በፊት ሕይወትህን"
.
የቀን ፕሮግራምህ ላይ:—
/ በጧት ከሥራ በፊት ሁለት ረከዐ አዱሐ ከሌለ…
/ ምንም ያህል ቢያንስም የምትችለውን ያህል የቁርኣን ዊርድ ከሌለ…
/ ከዒሻእ በኋላ ከፈጅር ሶላት በፊት ዊትር ከሌለ…
/ መልካም ነግግር ከሌለ…
/ የጌታን ቁጣ የሚያበርድ ሶደቃ ከሌለ…
/ ከአላህ በቀር ማንም የማያውቀው ድብቅ ስራ ከሌለ…
.
… ሕይወት ምን ጣዕም አለው!?
.
ኢላሂ ጀነትህን ስጠን ከእሳት ጠብቀን። ያማረ ህይወትና የደጋጎቹን ሞት ለግሰን!
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.
ነብዩ صلى الله عليه وسلم አዘውትረው ከሚያደርጉት ዱዓእ ዉስጥ:
#ጌታዬ_ሆይ፦
➭ከጸጋዎችህ መወገድ (አግኝቶ ከማጣት)
➭ካሟላህልኝ ደህንነትና ጤንነት መታወክ
➭ከድንገተኛ ቅጣትህ
➭ከየትኛውም አይነት ቁጣህ በአንተው እጠበቃለሁ።
image
Send as a message
Share on my page
Share in the group