UMMA TOKEN INVESTOR

About me

Writ good or remain silent

Translation is not possible.

Follow & Share → Umma ሚዲያ

↓↓↓↓↓

Umma ሚዲያ

ከነቢ ሰዐወ ህልፈት በኋላ ሰሃባዎች ወደ ተለያዩ የአለማችን

ክፍሎች ተበትነው ዘመቻ ላይ ናቸው።

ሳዕድ ኢብኑ አቢ ወቃስ ረዐ በታዘዘው መሰረት ሰራዊቱን ይዞ

ከፐርሺያ ምድር ተከስቷል። ያ በዐረብያ ምድር ያለ ስልጣኔ የኖረ

ማህበረሰብ ትልቁን የስልጣኔ መገለጫ የሆነውን ፐርሺያን በጦር

ሊገጥም አኮብኩቧል።

የፐርሺያው ስረወ መንግስት እልፍ አዕላፍ የሆነ የሰራዊት ማዐት

አሰልፎ ቁጥራቸው እና ትጥቃቸው እዚህ ግባ ከማይባሉ

ሰሓባዎች ጋር ሊፋለም ድንኳናቸውን ተክለው ማዶ ለማዶ

ይተያያሉ።

በዚህ መሃል የሰሓባዎቹ የጦር አዛዥ የሆነው ሳዕድ ከሰራዊቱ 7

ወጣቶችን መልምሎ የፐርሺያ ሰራዊቶችን ሁኔታ እንዲያጣሩ እና

ከቻሉም አንድ የፐርሺያ ወታደር ጠልፈው እንዲመጡ ላካቸው።

7 ሁነው ጉዞ ጀመሩ። ትንሽ እንደተጓዙም በርከት ያለ ቁጥር

ያላቸው የፐርሺያ ወታደሮችን ከርቀት ሲመጡ ተመለከቱ'ና

መቋቋም ስለማይችሉ ለመመለስ ወሰኑ።

ግና ከመካከላቸው በሀሳባቸው ሳይስማማ ቀርቶ አንደኛው

«የታዘዝኩትን ሳልፈፅም አልመለስም» በማለት ተልዕኮውን

ለማሳካት ጎዞውን ቀጠለ። 6ቱ ትተው ተመለሱ።

ጉዞውን በእርጋታ እና በመጠንቀቅ ቀጠለ። ሰራዊቱን በውሃ

ድልድዮች ተደብቆ ከተሻገረ በኋላ ማንም በማያውቀው ሁኔታ

ከ40,000 ሰራዊት እንብርት ላይ ተከሰተ።

ከሰራዊቱ መሀል ላይ ቁሞ ሩቅ እያማተረ ሲመለከት ከርቀት ነጭ

ድንኳን እና ከደጁ የቆመ የንጉሳን ፈረሰ ከአይኑ ገባ።

«ይህ የጦር አዛዣቸው የሩስቱም ድንኳን መሆን አለበት» ብሎ ወደ

ድንኳኑ ተጠግቶ ሌሊቱ ፅልመቱን ለምድር እስኪያልብስ እዝያው

ቁጭ አለ።

ፀሀይ ጠልቃ ምድር በፅልመት ስትወረር፣ ሰራዊቱ ከብርዱ

ጭጋግ ሽሽት ከየድንኳኖቻቸው ሲወሸቁ፤ ወጣቱ ሰይፉን

ከማንገቻው መዝዞ ወደ አዛዡ ድንኳን አመራ።

ከድንኳኑ ደጅ ሲደርስም የድንኳኑን ማዋቀርያ ገመዶች በሰይፉ

ቆራርጦ ሙሉ ድንኳኑ በአዳሪያኑ ላይ ሲወድቅ እሱ ደጅ ላይ

የታሰረውን ፈረስ ፈትቶ ጎዞውን ቀጠለ።

ፈጣን ፈረሰኞች ኮቴውን ተከትለው ያሯርጡት ጀመር፤ ከፈረስ

ጀርባ ያደገው የዐረብያ ብላቴናውም አሸዋውን እያቦነነ ከፊታቸው

ይከንፋል።

በመጨረሻም ከሁሉም ርቆ ሶስት ፈረሰኞች ብቻ ሲያሯርጡ

ደረሱበት። ከሶስቱ ፈረሰኞች የግድ አንዱን ይዞ ወደ አሚሩ መሄድ

ስለሚጠበቅበት ሊያጃጅላቸው ፈልጎ ሲደርሱበት እያመለጣቸው፤

በጣም ሲራራቁ እየጠበቃቸው ከክልላቸው አስወጣቸው።

ከዝያም ዞሮ ሰይፍ ተማዘዛቸው፤ ብዙም ሳይቆይ ሁለቱን ገድሎ

አንዱን አስሮ ይዞት ከፊት ከፊት እየነዳው ጉዞ ወደ አሚሩ ጀመረ።

ልክ የሙስሊሞችን ሰራዊት ደርሶ ምርኮኛውን ከአሚሩ ፊት

ሲያቆመው ምርኮኛው ለአሚሩ፦ «ከለላህን ስጠኝ እኔም

ዕውነታውን ላውራ» አለው።

«እኛ የዕውነት ህዝቦች ነን፤ ከላላችንን የምንሰጥህ እማትዋሸን

እንደሆን ነው» አለው አሚሩ።

ንግግሩን ቀጠለ፦ «እስቲ ስለ ፐርሺያ ሰራዊቶች ንገረኝ»

ምርኮኛው፦ «ስለ ፐርሺያ ሰራዊት ስብጥር ከመናገሬ በፊት ስለ

ጀግናው ጓድህ ላውጋህ።

ከልጅነቴ አንስቶ የጦርነት ሜዳ ላይ ነው ያደግኩት እንዲህ አይነት

ሰው አይቼም አላውቅም። ሁለት ጠንካራ የሰራዊት ቡድኖችን

አልፎ በመግባት የአዛዣችንን ድንኳን ቆራርጦ ጣለ'ና ፈረሱን ይዞ

ጋለበ።

ለ3 ሁነን እስከ መጨረሻ ተከታተልነው። ከፈረሱ ወርዶ

ተፋለመን'ና የ1000 ፈረሰኛ ግምት የምንሰጠውን ጀግናችንን

ገደለው።

ሁለተኛውንም የጦር መኳንንት በ1000 የምንገምተው ሲሆን

እሱንም እያየሁ ገደለው። ሁለቱም ያጎቶቼ ልጆች ነበሩ።

ይህ ድርጊቱ እልህ በልቤ ቋጥሬ ልገድለው ባለ በሌለ ጉልበቴ

እንዳሯሩጠው አስገደደኝ። የኔ አይነት ጉልበታም ከወታደሩ ይኖራል

ብዬ ባልገምትም ባላሰብኩት መልኩ የዚህ ልጅ ምርኮኛ ሆኜ

መጣሁ።

የዚህ አይነት ጀግና አንድ ካላችሁ መቼም አትሸነፉም» አላቸው።

በመጨረሻም እስልምናን ተቀበለ።

የሙስሊሞቹ ወታደሮችም ምድር አንቀጥቃጭ የሆነ ጦርነት

አድርገው ፐርሺያን ሙሉ በሙሉ ደምስሰው ድልን ተቀዳጁ።

ያ ጀግናው ሰሓቢይም ስሙ ጡለይሃ ቢን ኩወይሊድ ዱንያ

እስካለች ድረስ ሲወሳ ይኖራል።

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

boycot abbysinia bank

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

Follow & Share → Umma ሚዲያ

↓↓↓↓↓

Umma ሚዲያ

አዲስ ቤት ገዛህ? ዝም በል አታውራ

አዲስ መኪና ገዛ? አትናገር

ትዳር መሰረትክ? ብዙ አታውራለት

ለመዝናናት ከከተማ/ሀገር ወጣ ብለህ ነበር? ዝም በል

ንግድ ልትጀምር ነው? ድምፅህን አጥፋ

ኑሮ እየሰመረልህ ነው? ብዙ አታውራ

አብዛኛውን ጊዜ

ያሰብናቸው ህልሞች እና የወጠንናቸው ራእዮች የማይሳኩበት

ዋነኛው ምክንያት ከመከናወናቸው በፊት ብዙ ስለምናወራ ነው -

ገና እንቁላሉን ስንታቀፍ ማውራት እንጀምርና ብዙ

ሸለምጥማጦችን እንጠራለን::

ወዳጅ እና የቅርብ ሰዎች የምንላቸው ሰዎች "ሰዋዊ ቅናት" እና

"የጥሎ ማለፍ ውስጣዊ ትንቅንቅ" በጣም የሚጠበቅ ተፈጥሯዊ

ሁነት ነው:: ስለዚህ ህልሞችህ መስመር ይዘው ፍሬ እስኪያፈራ

ድረስ ዝም ብለህ መስራትን ምረጥ::

አብዛኛው ሰው

ቢያልፍልህ እና ህልምህ ቢሰምርልህ ደስ ይለዋል ሆኖም ግን

ጥለኸው እንድትሄድ እና አንጋጦ ሊያይህ ይተናነቀዋል::

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

Follow & Share → Umma ሚዲያ

↓↓↓↓↓

Umma ሚዲያ

ከነቢ ሰዐወ ህልፈት በኋላ ሰሃባዎች ወደ ተለያዩ የአለማችን

ክፍሎች ተበትነው ዘመቻ ላይ ናቸው።

ሳዕድ ኢብኑ አቢ ወቃስ ረዐ በታዘዘው መሰረት ሰራዊቱን ይዞ

ከፐርሺያ ምድር ተከስቷል። ያ በዐረብያ ምድር ያለ ስልጣኔ የኖረ

ማህበረሰብ ትልቁን የስልጣኔ መገለጫ የሆነውን ፐርሺያን በጦር

ሊገጥም አኮብኩቧል።

የፐርሺያው ስረወ መንግስት እልፍ አዕላፍ የሆነ የሰራዊት ማዐት

አሰልፎ ቁጥራቸው እና ትጥቃቸው እዚህ ግባ ከማይባሉ

ሰሓባዎች ጋር ሊፋለም ድንኳናቸውን ተክለው ማዶ ለማዶ

ይተያያሉ።

በዚህ መሃል የሰሓባዎቹ የጦር አዛዥ የሆነው ሳዕድ ከሰራዊቱ 7

ወጣቶችን መልምሎ የፐርሺያ ሰራዊቶችን ሁኔታ እንዲያጣሩ እና

ከቻሉም አንድ የፐርሺያ ወታደር ጠልፈው እንዲመጡ ላካቸው።

7 ሁነው ጉዞ ጀመሩ። ትንሽ እንደተጓዙም በርከት ያለ ቁጥር

ያላቸው የፐርሺያ ወታደሮችን ከርቀት ሲመጡ ተመለከቱ'ና

መቋቋም ስለማይችሉ ለመመለስ ወሰኑ።

ግና ከመካከላቸው በሀሳባቸው ሳይስማማ ቀርቶ አንደኛው

«የታዘዝኩትን ሳልፈፅም አልመለስም» በማለት ተልዕኮውን

ለማሳካት ጎዞውን ቀጠለ። 6ቱ ትተው ተመለሱ።

ጉዞውን በእርጋታ እና በመጠንቀቅ ቀጠለ። ሰራዊቱን በውሃ

ድልድዮች ተደብቆ ከተሻገረ በኋላ ማንም በማያውቀው ሁኔታ

ከ40,000 ሰራዊት እንብርት ላይ ተከሰተ።

ከሰራዊቱ መሀል ላይ ቁሞ ሩቅ እያማተረ ሲመለከት ከርቀት ነጭ

ድንኳን እና ከደጁ የቆመ የንጉሳን ፈረሰ ከአይኑ ገባ።

«ይህ የጦር አዛዣቸው የሩስቱም ድንኳን መሆን አለበት» ብሎ ወደ

ድንኳኑ ተጠግቶ ሌሊቱ ፅልመቱን ለምድር እስኪያልብስ እዝያው

ቁጭ አለ።

ፀሀይ ጠልቃ ምድር በፅልመት ስትወረር፣ ሰራዊቱ ከብርዱ

ጭጋግ ሽሽት ከየድንኳኖቻቸው ሲወሸቁ፤ ወጣቱ ሰይፉን

ከማንገቻው መዝዞ ወደ አዛዡ ድንኳን አመራ።

ከድንኳኑ ደጅ ሲደርስም የድንኳኑን ማዋቀርያ ገመዶች በሰይፉ

ቆራርጦ ሙሉ ድንኳኑ በአዳሪያኑ ላይ ሲወድቅ እሱ ደጅ ላይ

የታሰረውን ፈረስ ፈትቶ ጎዞውን ቀጠለ።

ፈጣን ፈረሰኞች ኮቴውን ተከትለው ያሯርጡት ጀመር፤ ከፈረስ

ጀርባ ያደገው የዐረብያ ብላቴናውም አሸዋውን እያቦነነ ከፊታቸው

ይከንፋል።

በመጨረሻም ከሁሉም ርቆ ሶስት ፈረሰኞች ብቻ ሲያሯርጡ

ደረሱበት። ከሶስቱ ፈረሰኞች የግድ አንዱን ይዞ ወደ አሚሩ መሄድ

ስለሚጠበቅበት ሊያጃጅላቸው ፈልጎ ሲደርሱበት እያመለጣቸው፤

በጣም ሲራራቁ እየጠበቃቸው ከክልላቸው አስወጣቸው።

ከዝያም ዞሮ ሰይፍ ተማዘዛቸው፤ ብዙም ሳይቆይ ሁለቱን ገድሎ

አንዱን አስሮ ይዞት ከፊት ከፊት እየነዳው ጉዞ ወደ አሚሩ ጀመረ።

ልክ የሙስሊሞችን ሰራዊት ደርሶ ምርኮኛውን ከአሚሩ ፊት

ሲያቆመው ምርኮኛው ለአሚሩ፦ «ከለላህን ስጠኝ እኔም

ዕውነታውን ላውራ» አለው።

«እኛ የዕውነት ህዝቦች ነን፤ ከላላችንን የምንሰጥህ እማትዋሸን

እንደሆን ነው» አለው አሚሩ።

ንግግሩን ቀጠለ፦ «እስቲ ስለ ፐርሺያ ሰራዊቶች ንገረኝ»

ምርኮኛው፦ «ስለ ፐርሺያ ሰራዊት ስብጥር ከመናገሬ በፊት ስለ

ጀግናው ጓድህ ላውጋህ።

ከልጅነቴ አንስቶ የጦርነት ሜዳ ላይ ነው ያደግኩት እንዲህ አይነት

ሰው አይቼም አላውቅም። ሁለት ጠንካራ የሰራዊት ቡድኖችን

አልፎ በመግባት የአዛዣችንን ድንኳን ቆራርጦ ጣለ'ና ፈረሱን ይዞ

ጋለበ።

ለ3 ሁነን እስከ መጨረሻ ተከታተልነው። ከፈረሱ ወርዶ

ተፋለመን'ና የ1000 ፈረሰኛ ግምት የምንሰጠውን ጀግናችንን

ገደለው።

ሁለተኛውንም የጦር መኳንንት በ1000 የምንገምተው ሲሆን

እሱንም እያየሁ ገደለው። ሁለቱም ያጎቶቼ ልጆች ነበሩ።

ይህ ድርጊቱ እልህ በልቤ ቋጥሬ ልገድለው ባለ በሌለ ጉልበቴ

እንዳሯሩጠው አስገደደኝ። የኔ አይነት ጉልበታም ከወታደሩ ይኖራል

ብዬ ባልገምትም ባላሰብኩት መልኩ የዚህ ልጅ ምርኮኛ ሆኜ

መጣሁ።

የዚህ አይነት ጀግና አንድ ካላችሁ መቼም አትሸነፉም» አላቸው።

በመጨረሻም እስልምናን ተቀበለ።

የሙስሊሞቹ ወታደሮችም ምድር አንቀጥቃጭ የሆነ ጦርነት

አድርገው ፐርሺያን ሙሉ በሙሉ ደምስሰው ድልን ተቀዳጁ።

ያ ጀግናው ሰሓቢይም ስሙ ጡለይሃ ቢን ኩወይሊድ ዱንያ

እስካለች ድረስ ሲወሳ ይኖራል።

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

የኛ ሃገር ባንኮች‼

=============

(ደሃን በጣም ደሃ አድራጊዎች፣ ባለ ሃብትን በጣም ባለ ሃብት አድራጊዎች!)

||

✍ ሚስኪኑ ወገኔ ሆይ! ዛሬ ባንኮች እንደት እንደሚቀፍሉህ ልጠቁምህ ወደድኩ።

ይህን የባንኮች አሠራር ምናልባት ከፊሎች ከናካቴው አያውቁትም፣ ከፊሎች አስተውለውት አያውቁም፣ ከፊሎች ቢያውቁትም አማራጭ ስለሌላቸው ውስጣቸው እየጨሰ ተላምደውት እየኖሩ ነው።

ባንኮች በየመንገዱ አስቁመውህ በ10 ብርም ቢሆን አካውንት ክፈት የሚሉህ ለአንተ አስበው ይመስልሃል? «ፎቶ አልያዝኩም!» ስትላቸው እንኳ «ችግር የለውም፣ ሌላ ጊዜ ታመጣለህ!» ይሉሃል። ሽል ለማለት ብለህ «አካውንት አለኝ!» ስትላቸው ሊያስምሉህ ይደርሳሉ።

✔ ባንኮች እንደት መሰለህ የሚሠሩት። ከአንተ በትንሹ 10 ብር ወሰዱ። እንዳንተ ያሉ 20 ሚሊዮን ሚስኪኖች አሉ። ስለዚህ ከእናንተ ስንት ሸቀሉ? 200 ሚሊዮን ብር! አስበው ከአንዳችሁ ኪስ የወጣው 10 ብር ስለሆነች ምንም ላትመስላችሁ ትችላለች።

ከፊሎቹ በየወሩ ከሚያገኟት ደመወዛቸው ላይ ቀንሰው ያገኟትን ያጠራቅማሉ። ባለ 10 ሺህ ብር ደመወዝተኛ ለቤት ኪራይ 5 ሺህ ብር፣ ለምግብና ተያያዥ ወጪዎች 3 ሺህ ብር አወጣና ቀሪዋን 2000 ብር ባንክ አስቀመጠ። ከ124+ ሚሊዮን ዜጎች መካከል እንደዚህ አይነት 10 ሚሊዮን ዜጎች ቢኖሩ፤ ከነዚህ ብቻ 20 ቢሊዮን ብር ይቀፈላል። አስበው! ከፊሎች በ10 ሺዎች፣ በመቶ ሺዎች፣ በሚሊዮን የሚያጠራቅሙ አሉ። የነርሱን ስንጨምረው አስበው።

የሚገርመው ይሄ ከሁላችንም የተሰባሰበ ገንዘብ የሚውልበት አላማ ነው።

ይሄ ከየሚስኪኑ የተጠራቀመ ገንዘብ ለባለሃብቶች በብድር መልክ ይሰጥና ቢዝነስ ይሠሩበታል። አንተ ሚስኪኑም ከአንተና መሰሎችህ በተሰባሰበው ከተከፈተወረ ቢዝነስ ከፍለህ ትጠቀማለህ። አስበው! በአንተው ብር ትርፍ ሲሠራብህ! አያምም?

*

√ የሚገርምህ አንተ መኪና ወይም ቤት ለመግዛት አስበህ በወቅቱ ያለው አንተ የምትፈልገው መኪና ዋጋ 1 ሚሊዮን ብር ቢሆንና የምትፈልገው ቤት ግምቱ 10 ሚሊዮን ብር ቢሆን፤ አንተ ለጊዜው ያለህ ለመኪና 800 ሺህ ብር ቢሆንና ለቤቱ 8 ሚሊዮን ብር ቢሆን፤ በቃ የአመት ገቢዬን አጠራቅሜ ቀጣይ አመት እገዛዋለሁ ስትል፤ አንተ እያጠራቀምከው ያለውን ገንዘብ ተጠቅመው እየነገዱበት ያሉት ከባንኩ ጀርባ ያሉ ባለሃብቶች ኑሮን አስወድደውት ያ ቀጣይ አመት ልታገኘው የተመኘኸው መኪና 1.5 ሚሊዮን ብር ሆኗል፣ ቤቱ 20 ሚሊዮን ብር ገብቷል። አሁንም ቀጣይ አመት ስትል በየጊዜው እየጨመረ እነርሱ ወደፊት እየሸሹህ፣ አንተ ከኋላ እየተከተልክ አባራሪና ተባራሪ ሆናችሁ እድሜህ ይገፋና አንድ ቀን ሞት ይመጣል።

ግን ራስህን እየጎዳህ ያለኸው አንተ ነህ። ኑሮን ለሚያስወድዱብህ ባለሃብቶች ከየትም ተሯሩጠህ ገንዘብ ፈልገህ በባንክ በኩል ታቀብላቸዋለህ።

አንዳንድ የግል ባንኮችማ አክሲዮን ብለው በጣት የሚቆጠሩ ሰዎች ይሰባሰቡና ከየቦታው አጠራቅመው ለራሳቸው ተከፋፍለው ይነግዱበታል። ይሄ ህዝብ ብዙ ያልገባው ነገር አለ።

እነዚያ ባለሃብት ተብዬዎች ግን ያላለቀ ህንፃቸውንና አሮጌ መኪናቸውን መያዣ አድርገው ያንተን ብር ተበድረው ይሠሩበታል። አንተ እንደነርሱ ተበድረህ እንዳትሠራ ቤትና መኪና የለህም። በቃ እንዲህ ሆነህ ውለታህ እንኳ ሳይቆጠር ማንንም ጠቃሚ ትሆናለህ።

በአጭሩ የኛ ሃገር ባንኮች ባለሃብቱን በተጠራቀመ የሚስኪኑ ገንዘብ ስለሚነግድ ይበልጥ ባለሃብት የሚያደርጉት፣ ድሃው ግሽበት ያለበት ገንዘብ እያጠራቀመ በየጊዜው ዋጋው በመቀነስ ከፍላጎቱ ጋር እንዳይገናኝ በማድረግ ይበልጥ ድሃ የሚያደርጉ፣ በድሃና በሃብታም መካከል ከፍተኛ የኑሮ ልዩነት እንዲኖር የሚያደርጉ ናቸው።

*

√ ይሄ ይገርምሃል እንደ! ጭራሽ የወለድ ባንኮች ላይ ከወለድ አልባ በሚባለው መስኮት የሚያጠራቅም ሙስሊም አለ። እኔ'ምልህ ሐቢቢ! በዛ መስኮት የሰጡህ ብር ወለድ ካለበት መስኮት ላለመምጣቱ ምን ዋስትና አለህ? ሲጀመር እነርሱስ እንደት ብለው መቆጣጠር ይችላሉ?

ወይንስ የአንተ ከወለድ ነፃ ብሮች የተለዬ መልክ ስላላቸው እነዛን ለይተው ይስጡህ?

አትሞኝ! ንግድ ባንክ ከወለድ አልባ ያገኘውን ገቢ ዘምዘምና ሒጅራ ተደምረው አላገኙትም።

ቢያንስ ለሙስሊሞቹ ባንኮች ብትሰጣቸው ይበልጣል። ወንድሞችህ ይጠቀሙበት።

√ ምን ይሻል? ባንኮች አነስተኛ ገቢ ያለውንም ማኅበረሰብ ያማከለ ጥቅም እስኪዘረጉ ድረስ መታገል ግድ ነው። ሲጀመር የባለ ወለዶቹ እንደዛ ቢዘረጉም መጠቀም የለብንም። ከነርሱ ከናካቴው ውጡና ወደ ኢስላማዊ ባንኮች ዙሩ። ግን እነርሱም ጋ ገንዘባችሁን በአግባቡ ተጠቀሙበት።

እስኪ ሃሳብ አንሱና እንወያይበት። በተለይም መፍትሄው ላይ!

||

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group