UMMA TOKEN INVESTOR

About me

በአላህ ሀቅ ሰዎችን አትፍራ በሰዎች ሀቅ አላህን ፍራ

Translation is not possible.

መላ ዐረቢያን የሚያስተዳድረው የኢስላማዊ ስረወ መንግስቱ መሪ ዑመር ረዐ የመስጂደል ሀራምን ግቢ ለማስፋፋት የዐባስ ቤት እንዲፈርስ እና ለዐባስም በምትኩ ቆንጆ ቤት ሌላ ቦታ እንዲገነባለት ትዕዛዝ አስተላለፈ።

አባስም፦‹‹ቤቴ እንዲፈርስ እልፈቅድም›› አሉ።

(መብት)

ዑመርም፦‹‹ዐባስ! የአላህን ቤት ቤት ለማስፋፋት እኮ ነው›› አለው።

(ማባበል)

ዐባስም፦‹‹አልፈቅድም አልኩኝ እኮ ዑመር!›› ብሎ መለሰ።

(መሪ ፊት መብትን ማስከበር)

ዑመርም፦‹‹እንግዲያውስ ወደ ሸንጎ ሂደን እንዳኝ፤ ሚዳኘንን ዳኛም አንተው ምረጥ›› አለው።

(ፍትህ እና መተናነስ)

ዐባስም፦‹‹ዳኛ ሹረይሕ ይዳኘን›› አለ።

(ጥሩ ስም ሲኖር)

ዑመርም፦‹‹ተስማምቻለሁ››አለ።

(መተናነስ)

ዐባስም፦‹‹የምእመናን መሪ ሆይ! በል ዳኛ ሹረይሕን ጥራው'ና ይዳኘን›› አለ።

ዑመርም፦‹‹ዳኛ ወደሚዳኛቸው ሰዎች አይሄድም፤ እነሱ ናቸው ወደ እሱ መሄድ ያለባቸው። ተነስ እኛ እንሂድ›› አለው።

(መርህ)

ሁለቱም ተያይዘው ወደ ሸንጎው ዳኛ አመሩ። ሸንጎው ፊት ሲቆሙም ዳኛው፦‹‹የምእመናን መሪ...›› ብሎ ዑመርን ሲጠራ ዑመርም፦‹‹ዑመር ብለህ ጥራኝ፤ ሸንጎ ላይ እስካለሁ ድረስ›› አለው።

(የሸንጎ እና የዳኛ ክብር)

ሸንጎው ተጀመረ። ሁለቱም ስሞታቸውን ለዳኛው ካሳሰቡ በኋላ ዳኛው እንዲህ ስል ውሳኔ አስተላለፈ፦‹‹ከሀራም የፀዳ ቦታ ማለት መስጅድ ነው።መስጂድን ለማስፋፋት ያለ በጎ ፈቃዱ የዐባስን ቤትም ማፍረስ ደግሞ ሀራም ነው››

(ፍትህ ፣ ሀላፊነት፣ ድፍረት)

ዑመርም ክሱ ውድቅ ሲሆንበት፦‹‹ምንኛ ፍትሀዊ ዳኛ ነህ! ሸንጎህ ያማረ›› አለው።

(ዕውነታን መቀበል)

ዑመር እዝያው ሽንጎ ላይ ሁኖ ይህንን ዳኛ የዳኞች ሁሉ የበላይ አድርጎትም ሾመው።

(ዕምነት)

ይህን የተመለከተው ዐባስም፦‹‹እንግዲያ ነገሩ እንዲህ ተሆነማ ፤ እኔም ቤቴን በገዛ ፈቃዴ ለአላህ ብዬ ለቅቄያለሁ›› አለ

(ከድል በኋላ ያለ ለጋስነት)

ምንጭ፦

البدايه والنهايه

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

መላ ዐረቢያን የሚያስተዳድረው የኢስላማዊ ስረወ መንግስቱ መሪ ዑመር ረዐ የመስጂደል ሀራምን ግቢ ለማስፋፋት የዐባስ ቤት እንዲፈርስ እና ለዐባስም በምትኩ ቆንጆ ቤት ሌላ ቦታ እንዲገነባለት ትዕዛዝ አስተላለፈ።

አባስም፦‹‹ቤቴ እንዲፈርስ እልፈቅድም›› አሉ።

(መብት)

ዑመርም፦‹‹ዐባስ! የአላህን ቤት ቤት ለማስፋፋት እኮ ነው›› አለው።

(ማባበል)

ዐባስም፦‹‹አልፈቅድም አልኩኝ እኮ ዑመር!›› ብሎ መለሰ።

(መሪ ፊት መብትን ማስከበር)

ዑመርም፦‹‹እንግዲያውስ ወደ ሸንጎ ሂደን እንዳኝ፤ ሚዳኘንን ዳኛም አንተው ምረጥ›› አለው።

(ፍትህ እና መተናነስ)

ዐባስም፦‹‹ዳኛ ሹረይሕ ይዳኘን›› አለ።

(ጥሩ ስም ሲኖር)

ዑመርም፦‹‹ተስማምቻለሁ››አለ።

(መተናነስ)

ዐባስም፦‹‹የምእመናን መሪ ሆይ! በል ዳኛ ሹረይሕን ጥራው'ና ይዳኘን›› አለ።

ዑመርም፦‹‹ዳኛ ወደሚዳኛቸው ሰዎች አይሄድም፤ እነሱ ናቸው ወደ እሱ መሄድ ያለባቸው። ተነስ እኛ እንሂድ›› አለው።

(መርህ)

ሁለቱም ተያይዘው ወደ ሸንጎው ዳኛ አመሩ። ሸንጎው ፊት ሲቆሙም ዳኛው፦‹‹የምእመናን መሪ...›› ብሎ ዑመርን ሲጠራ ዑመርም፦‹‹ዑመር ብለህ ጥራኝ፤ ሸንጎ ላይ እስካለሁ ድረስ›› አለው።

(የሸንጎ እና የዳኛ ክብር)

ሸንጎው ተጀመረ። ሁለቱም ስሞታቸውን ለዳኛው ካሳሰቡ በኋላ ዳኛው እንዲህ ስል ውሳኔ አስተላለፈ፦‹‹ከሀራም የፀዳ ቦታ ማለት መስጅድ ነው።መስጂድን ለማስፋፋት ያለ በጎ ፈቃዱ የዐባስን ቤትም ማፍረስ ደግሞ ሀራም ነው››

(ፍትህ ፣ ሀላፊነት፣ ድፍረት)

ዑመርም ክሱ ውድቅ ሲሆንበት፦‹‹ምንኛ ፍትሀዊ ዳኛ ነህ! ሸንጎህ ያማረ›› አለው።

(ዕውነታን መቀበል)

ዑመር እዝያው ሽንጎ ላይ ሁኖ ይህንን ዳኛ የዳኞች ሁሉ የበላይ አድርጎትም ሾመው።

(ዕምነት)

ይህን የተመለከተው ዐባስም፦‹‹እንግዲያ ነገሩ እንዲህ ተሆነማ ፤ እኔም ቤቴን በገዛ ፈቃዴ ለአላህ ብዬ ለቅቄያለሁ›› አለ

(ከድል በኋላ ያለ ለጋስነት)

ምንጭ፦

البدايه والنهايه

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

የእስራኤል ሚዲያ እንደዘገበው፡ በጋዛ ሰርጥ ዙሪያ የሚገኙ በደርዘን የሚቆጠሩ የእስራኤል ወታደሮች በአሸዋ ዝንብ ንክሻ በሚተላለፈው በሊሽማንያ በተሰኘው ጥገኛ በሽታ ተይዘዋል። በሽታው የሚያሠቃይ እና ለረጅም ጊዜ የሚቆይ የቆዳ ቁስሎችን ያመጣል, እና ካልታከመ, ዘላቂ ጠባሳ ሊያስከትል ይችላል.

በሙስሊሙ ዓለም የተፈጠሩ ሁሉንም አዳዲስ መረጃዎች በተለይም በወቅታዊ የፍልስጤም ጉዳይ እውነተኛ እና ሚዛናዊ መረጃ ለማግኘት የሙሐመድ ትውልድ ገፅን ፎሎው ያድርጉ

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

አል-ቃሳም ብርጌድ፡ የአልቃሳም ብርጌድ የሞርታር ቡድን በጋዛ ሰርጥ በወራሪ የጠላት ስብስብን ደብግቧል።

አል-ቃሳም ብርጌድ፡ በማዕከላዊ ጋዛ ሰርጥ ከአል-ቡሬጅ ካምፕ በስተሰሜን የሚገኘውን የጽዮናውያን ጦር ተሸካሚ ተሽከርካሪ በ"አል-ያሲን 105" መሳሪያ ሙሉ በሙሉ ማውደም ችለናል።

በሙስሊሙ ዓለም የተፈጠሩ ሁሉንም አዳዲስ መረጃዎች በተለይም በወቅታዊ የፍልስጤም ጉዳይ እውነተኛ እና ሚዛናዊ መረጃ ለማግኘት የሙሐመድ ትውልድ ገፅን ፎሎው ያድርጉ

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group

ሰባቱ(7) የ‹‹ላ ኢላሀ ኢለላህ›› መስፈርቶች (ሸርጦች)

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩኅ ናበጣም አዛኝ በኾነዉ፦

1.✍ዕውቀት፡- ይህም ማለት የዚህ ቃል መልዕክት እና ቃሉ ዉድቅ

የሚያደርጋቸዉንና እና የሚያፀድቃቸውን ነገሮች ጠንቅቆ ማወቅ ማለት ነው፡፡

ለዚህም ማስረጃው ቀጣዩ የአላህ ቃል ነው፡፡

ﻭَﻟَﺎ ﻳَﻤْﻠِﻚُ ﺍﻟَّﺬِﻳﻦَ ﻳَﺪْﻋُﻮﻥَ ﻣِﻦْ ﺩُﻭﻧِﻪِ ﺍﻟﺸَّﻔَﺎﻋَﺔَ ﺇِﻟَّﺎ ﻣَﻦْ ﺷَﻬِﺪَ ﺑِﺎﻟْﺤَﻖِّ ﻭَﻫُﻢْ ﻳَﻌْﻠَﻤُﻮﻥَ

ﺍﻟﺰﺧﺮﻑ : ٨٦

(እነዚያም ከአላህ ሌላ የሚያመልኳቸዉ እነሱ የሚያውቁ ሆነው በእውነት

ከመሰከሩት በስተቀር ምልጃን አይችሉም) አል-ዙኸሩፍ 86

2✍.እርግጠኛነት፡- በአላህ ብቸኛ አምላክነት ላይ ሙሉ በሙሉ እርግጠኛ መሆን

ነው፡፡አላህ (ሱ.ወ)እንዲህ ይላል፡-

ﺇِﻧَّﻤَﺎ ﺍﻟْﻤُﺆْﻣِﻨُﻮﻥَ ﺍﻟَّﺬِﻳﻦَ ﺁﻣَﻨُﻮﺍ ﺑِﺎﻟﻠَّﻪِ ﻭَﺭَﺳُﻮﻟِﻪِ ﺛُﻢَّ ﻟَﻢْ ﻳَﺮْﺗَﺎﺑُﻮﺍ ﻭَﺟَﺎﻫَﺪُﻭﺍ ﺑِﺄَﻣْﻮَﺍﻟِﻬِﻢْ ﻭَﺃَﻧْﻔُﺴِﻬِﻢْ

ﻓِﻲ ﺳَﺒِﻴﻞِ ﺍﻟﻠَّﻪِ ﺃُﻭﻟَﺌِﻚَ ﻫُﻢُ ﺍﻟﺼَّﺎﺩِﻗُﻮﻥَ

ﺍﻟﺤﺠﺮﺍﺕ: ١٥

({እዉነተኞቹ} ምእመናን እነዚያ በአላህና በመልእክተኛዉ ያመኑት ከዚያም

ያልተጠረጠሩት ናቸው) አል-ሑጁራት 15

የአላህ መልእክተኛም (ሰ.ዐ.ወ) ለአቡ ሑረይራ (ረዲየ አላሁ አንሁ) እንዲህ

ብለውታል፡- ‹‹ ከዚህ አጥር በስተጀርባ የአላህን ብቸኛ አምላክነት ከልቡ

በእርግጠኝነት የሚመሰክር ሰው ብታገኝ በጀነት አበስረው፡፡›› ሙስሊም

ዘግበዉታል

3.✍መቀበል፡- የላኢላሀ ኢለላህን መልእክት (አላህን በብቸኝነት ማምለክን)

ከልብ መቀበልና ለሌላ አካል የሚከናወኑ አምልኮቶችን መተው ነው፡፡ ይህንን

ያልተቀበለ ግን አላህ ኩራተኛነታቸውን እና አለመቀበላቸው እንዲህ በማለት

ከገለፃቸው ሙሽሪኮች መደዳ ይሰለፋል፡፡

ﺇِﻧَّﻬُﻢْ ﻛَﺎﻧُﻮﺍ ﺇِﺫَﺍ ﻗِﻴﻞَ ﻟَﻬُﻢْ ﻟَﺎ ﺇِﻟَﻪَ ﺇِﻟَّﺎ ﺍﻟﻠَّﻪُ ﻳَﺴْﺘَﻜْﺒِﺮُﻭﻥَ

ﺍﻟﺼﺎﻓﺎﺕ: ٣٥ – ٣٦

(እነርሱ፤ ‹ከአላህ ሌላ አምልኮት የሚገባው ሆኖ የሚመለክ አምላክ የለም›

በተባሉ ጊዜ ይኮሩ ነበር፡፡ እኛ ለእብድ ባለቅኔ ብለን አማልክቶቻችንን የምንተው

ነን ይሉም ነበር፡፡) አልሷፋት 35-36

4.✍መታዘዝ፡- ይህ ማለት ‹‹ላ ኢላሀ ኢለላህ›› የሚለው የምስክርነት ቃል

ለሚያመላክታቸው ትዕዛዛትና ክልከላዎች ሙሉ ታዛዥ ተከታይና ተናናሽ መሆን

ነው፡፡ አላህ (ሱ.ወ) እንዲህ ይላል፡-

ﻭَﻣَﻦْ ﻳُﺴْﻠِﻢْ ﻭَﺟْﻬَﻪُ ﺇِﻟَﻰ ﺍﻟﻠَّﻪِ ﻭَﻫُﻮَ ﻣُﺤْﺴِﻦٌ ﻓَﻘَﺪِ ﺍﺳْﺘَﻤْﺴَﻚَ ﺑِﺎﻟْﻌُﺮْﻭَﺓِ ﺍﻟْﻮُﺛْﻘَﻰ ﻭَﺇِﻟَﻰ ﺍﻟﻠَّﻪِ

ﻋَﺎﻗِﺒَﺔُ ﺍﻟْﺄُﻣُﻮﺭِ

ﻟﻘﻤﺎﻥ : ٢٢

(እርሱ መልካም ሰሪ ሆኖ ፊቱን (በመታዘዝና በመተናነስ) ወደ አላህ የሚሰጥ

ሰው ጠንካራን ገመድ በእርግጥ ጨበጠ…)

ሉቅማን 22

5.✍ እውነተኝነት፡- የላኢላሀ ኢለላህን የምስክርነት ቃል በሚሰጥበት ጊዜ

እውነተኛ መሆን ማለት ነው፡፡ የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ይላሉ

‹‹ማንኛውም ከልቡ በእውነተኛነት በአላህ ብቸኛ አምላክነትና በሙሐመድ

(ሰ.ዐ.ወ) መልዕክተኝነት የሚመሰክር ሰው አላህ ከእሳት እርም ይለዋል ››

ቡኻሪ ዘግበዉታል

6.✍መውደድ፡- ይህ ማለት ላኢላሀ ኢለላህ የሚለውን የምስክርነት ቃል ፣ አላህን

እንዲሁም አላህን በብቸኝነት የሚያመልኩትን የተውሂድ ሰዎችን መውደድ ነው፡፡

አላህ (ሱ.ወ) እንዲህ ይላል ፡-

( ﻭَﻣِﻦَ ﺍﻟﻨَّﺎﺱِ ﻣَﻦْ ﻳَﺘَّﺨِﺬُ ﻣِﻦْ ﺩُﻭﻥِ ﺍﻟﻠَّﻪِ ﺃَﻧْﺪَﺍﺩًﺍ ﻳُﺤِﺒُّﻮﻧَﻬُﻢْ ﻛَﺤُﺐِّ ﺍﻟﻠَّﻪِ ﻭَﺍﻟَّﺬِﻳﻦَ ﺁﻣَﻨُﻮﺍ ﺃَﺷَﺪُّ

ﺣُﺒًّﺎ ﻟِﻠَّﻪِ

ﺍﻟﺒﻘﺮﺓ: ١٦٥

(ከሰዎችም አላህን እንደሚወዱ የሚወዷቸው ኾነው ከአላህ ሌላ ባለንጣዎችን

(ጣዖታትን) የሚይዙ አሉ፡፡ እነዚያ ያመኑትም አላህን በመውደድ (ከነርሱ)

ይበልጥ የበረቱ ናቸው) አል በቀራህ 165

7✍ማጥራት፡- ይህም ማለት የላኢላሀ ኢለላህን የምስክርነት ቃል የሰጠ ሰው

ስራውን ከሽርክ ማጥራት አለበት፡፡ እንዲሁም በዚህ የምስክርነት ቃል የዱንያ

ጥቅማጥቅሞችን ከመከጀል፣ ከይዩልኝ እና ይስሙልኝ መጥራት አለበት፡፡

የአላህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል ‹‹የቂያማ ዕለት የኔን ምልጃ

በማግኘት ዕድለኛ የሚሆነው ላ ኢላሀ ኢለላህን ከልቡ ያለ ሰው ነው፡፡››

🎀ቡኻሪ ዘግበውታል🎀

Send as a message
Share on my page
Share in the group