Abu Ayub Profile Picture
UMMA TOKEN INVESTOR

Abu Ayub shared a
Translation is not possible.

ትኩረት የነፈግናቸው የሃሜት ሰበቦች

~

ሃሜት ፀያፍ እንደሆነ የምናምንበት ግን በተግባር መራቁ የሚያቅተን ክፉ ባህሪ ነው። ለሃሜት የሚዳርጉን ሰበቦች ብዙ ናቸው። ዋና ዋናዎቹ የሚከተሉት ናቸው:-

1- የተቅዋ ማነስ፦

አንድ ሰው በልቡ ውስጥ አላህ መፍራት ሲቀንስ የሚናገረውን መመዘን ይቀራል። በንግግሩ ሳቢያ የሚመጣበትን ጣጣ ከማሰብ ይልቅ የሚሰማውን ሁሉ መናገር ደስታ ይሰጠዋል። ስለዚህ በዚህ በሽታ የተጠቃ ሰው (ያልተጠቃ አለ ግን?) ህክምና የሚፈልግ ከሆነ ልቡን ከማከም ይጀምር። ተቅዋውን ይፈትሽ።

2- ምቀኝነት፦

ሌላኛው የሃሜት ሰበብ በሌሎች ላይ የሚኖረን የምቀኝነት ስሜት ነው። "እኔ ከዚህ በሽታ ንፁህ ነኝ" እያልክ ራስህን አትሸንግል። ምቀኞች ምቀኝነታቸውን አያምኑም። የራስ እንትን አይገማም ይባላል። ስለዚህ ሃሜተኝነት የሌላ በሽታ ማለትም በምቀኝነት የመጠቃት ምልክት ሊሆን ስለሚችል ደጋግመህ ልብህን አዳምጥ። ከዚያም በተቅዋ ታከመው።

3- ውሎ:-

ሌላኛው የሃሜት ሰበብ ጓደኛ ነው። ሰው ብቻውን በሃሜት አይለፈልፍም። ሃሜት ላይ አድማጭ፣ አጃቢ፣ አጋዥ፣ ... ትልቅ ሚና አላቸው። ሃሜት ላይ የምትወድቀው ከማን ጋር ስትሆን እንደሆነ አንዴ በአይነ ህሊናህ ተመልከት። ከማን ጋር ሆነው ሰው የምታማው? ከዚያም ችግሩን ለመፍታት ከልብህ አስብበት። ተነጋግሮ ችግሩን ለመፍታት መፍትሄው ከራቀ ለሰበቡ ያለህን ቅርበት ቀንስ። ያን ካላደረግክ ከነ ህመምህ ልትኖር ወስነሃል።

4- ራስን ማጉላት:-

ሌላኛው የሃሜት መንስኤ ሌሎችን በማሳነስ ወይም በማጠልሸት ራስን የማጉላት ድብቅ ፍላጎት ነው። ይሄ ከሃሜቱ ልክፍት በፊት ልንታከመው የሚገባ ሌላ በሽታ ነው። አዎ ብዙ የሃሜት ገፊ ምክንያቶች ውስጥ ከጀርባ ያደፈጡ ራስን በሆነ ነገር ልዩ የማድረግ ወይም የመስቀል አባዜ ስለሚኖር ነፍሲያችንን ምን ፈልጋ ከሃሜት ሰፈር እየተልከሰከሰች እንደሆነ ቀስ ብለን እንከታተላት። ምናልባት እጅ ከፍንጅ ልንይዛት እንችላለን።

5- ቀልድና ቧልት:-

ብዙ ጨዋታዎች የሞቁ የደመቁ የሃሜት ድግሶች ናቸው። በቀልድ እያዋዛን የምንዘለዝለው የሃሜት ቁርጥ ለጊዜው ጣእሙ ልዩ ሊሆን ይችላል። ሰው ሳያውቅ የሰውን ስጋ አጣጥሞ ቢበላ ላይደንቅ ይችላል። የሚገርመው እያወቅን ደጋግመን መቀጠላችን ነው። ሃሜት የሰው ስጋ መብላት ነው። ያውም የሞተን ሰው አካል! ምን ስሜት ይሰጣል?

{وَلَا یَغۡتَب بَّعۡضُكُم بَعۡضًاۚ أَیُحِبُّ أَحَدُكُمۡ أَن یَأۡكُلَ لَحۡمَ أَخِیهِ مَیۡتࣰا فَكَرِهۡتُمُوهُۚ وَٱتَّقُوا۟ ٱللَّهَۚ}

"ከፊላችሁም ከፊሉን አይማ። አንደኛችሁ የወንድሙን ስጋ የሞተ ሆኖ ሊበላው ይወዳልን? (መብላቱን) ጠላችሁትም፤ (ሐሜቱንም ጥሉት)። አላህንም ፍሩ።" [አልሁጁራት፡ 12]

Ibnu Munewor

=

የቴሌግራም ቻናል፡-

https://t.me/IbnuMunewor

Telegram: Contact @IbnuMunewor

Telegram: Contact @IbnuMunewor

كناشة ابن منور
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Abu Ayub shared a
Translation is not possible.

አንድ ትንሽዬ ልጅ ለወላጆቹ፦"3 ጥያቄዎቼን የሚመልስልኝ

ጠንካራ ዑለማ አምጡልኝ" አላቸው።

ወላጆቹም በአከባቢያቸው ያለ አንድ ኡስታዝ አመጡለትና

አገናኙት።

💧ልጁ፦"ማን ነህ አንተ? እኔ ስለምጠይቀውስ ጥያቄ መልስ

እንዳለህ ምን ያህል እርግጠኛ ነህ?"

➣ኡስታዙ፦"ስሜ ዐብዱላህ ይባላል ከአላህ ባሪያዎችም አንዱ

ነኝ።ለምትጠይቀኝ ጥያቄዎችም በአላህ ፍቃድ መልስ

እሰጥሀለሁ።"

💧ልጁ፦"አንተ ግን ብዙ ዑለማኦች ሊያብራሩልኝ ያልቻሉትን

ጥያቄዬን እንደምትመልስልኝ ሙሉ በሙሉ እርግጠኛ ነህ?

➣ኡስታዙ፦"ልመልስልህ እሞክራለሁ በአላህ እገዛ።"

💧ልጁ፦" 3 ጥያቄዎች አሉኝ።

❶ ➛ እውነት ፈጣሪ አለ? አዎ አለ የምትል ከሆነ አሳየኝ የት ነው

ያለው?

❷ ➛ ቀዷ እና ቀደር ምንድነው?

❸ ➛ እውነት ሸይጣን ከእሳት የተፈጠረ ከሆነ እንዴት በእሳት

ይቀጣል? ከእሳት ተፈጥሮ እሳት አያቃጥለውም።

"ይሄን ግዜ ኡስታዙ እሳት በሆነች ጥፊ ልጁን አጮለው።

💧ልጁ፦"እንዴ!!! ለምን ትመታኛለህ? ምን ሚያስመታ ነገር

ተናገርኩ?

➢ኡስታዙ፦"አረ!!! እኔ አልተቆጣሁም ግን ያሁኗ ጥፊ ለሶስቱም

ጥያቄዎችህ መልስ ናት።

💧ልጁ፦"እንዴት? አልገባኝም...

➢ኡስታዙ፦"በጥፊ ስመታህ ምን ተሰማህ?

ልጁ፦"በጣም ህመም ተሰማኝ።

➢ኡስታዙ፦"ህመም እንዳለ ታምናለህ?"

💧ልጁ፦"አዎ አምናለሁ።"

➢ኡስታዙ፦"አሳየኝ የት ነው ያለው?"

ልጁ፦"አይ አለ ግን ማየት እንኳን አይቻልማ"

➢ኡስታዙ፦"ይህ ለመጀመሪያ ጥያቄህ መልስ ነው።ሁላችንም

አላህ እንዳለ እናምናለን ነገር ግን ማየት አንችልም።

እሺ ዛሬ እንደምመታህ ትናንት ማታ ገምተህ ነበር?"

ልጁ፦"አልገመትኩም።"

➢ኡስታዙ፦"እሺ እኔስ አንተን ዛሬ እንደምመታህ ትናንት ማታ አስቤ

ነበር?

💧ልጁ፦"አላሰብክም።"

➢ኡስታዙ፦"ለ2ኛ ጥያቄህ መልስ ይህ ነው ቀዷ ቀደር

የሚባለው።

እሺ እኔ አንተን የመታሁበት እጄ 💧ከምንድነው የተፈጠረው?"

ልጁ፦"ከአፈር"

➢ኡስታዙ፦"እሺ በእጄ የመታሁት ያንተ ፊትስ ከምንድነው

የተፈጠረው?"

ልጁ፦"ከአፈር"

➢ኡስታዙ፦"ስመታህ ምን ተሰማህ?"

💧ልጁ፦"አመመኝ"

➢ኡስታዙ፦"ከአፈር የተሰራ አፈርን ሲመታው

እንደሚያሳምመው ሁላ ከእሳት የተሰራውም ሸይጣን በእሳት

ሲቀጣ በጣም ያመዋል።"

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Abu Ayub shared a
Translation is not possible.

➯3ቱ ሐዲሶች

፡፡፡።፡፡፡፡።።።።።።።።።።።።

❶) «ከሱረተል ካህፍ መጀመሪያ አስር አንቀፆችን የሸመደደ ሰው ከደጃል ተጠበቀ»።

ረሱል (ሶለሏሁ ዓለይሂ ወሰለም)

ﻣﻦ ﺣﻔِﻆ ﻋﺸﺮَ ﺁﻳﺎﺕٍ ﻣﻦ ﺃﻭﻝِ ﺳﻮﺭﺓِ ﺍﻟﻜﻬﻒ، ﻋُﺼِﻢَ ﻣﻦ ﺍﻟﺪَّﺟَّﺎﻝِ.

ምንጭ:-📒ሶሒሁል ሙስሊም (809)

❷) «ሱረተል ካህፍን ያነበበ ሰው እስከ ቂያማ እለት ድረስ ብርሀን ትሆንለታለች ካለበት ቦታ እስከ መካ ድረስ የሚደርስ ከመጨረሻዋ አስር አንቀፆችን ያነበበ ሰው ከዛም ደጃል ቢወጣ አይጎዳውም»።

ረሱል (ሶለሏሁ ዓለይሂ ወሰለም)

ﻣﻦ ﻗﺮﺃ ﺳﻮﺭﺓَ ﺍﻟﻜﻬﻒِ ﻛﺎﻧﺖ ﻟﻪ ﻧﻮﺭًﺍ ﺇﻟﻰ ﻳﻮﻡِ ﺍﻟﻘﻴﺎﻣﺔِ ، ﻣﻦ ﻣﻘﺎﻣِﻪ ﺇﻟﻰ ﻣﻜﺔَ، ﻭﻣﻦ ﻗﺮﺃ ﻋﺸﺮَ ﺁﻳﺎﺕٍ ﻣﻦ ﺁﺧﺮِﻫﺎ ﺛﻢ ﺧﺮﺝ ﺍﻟﺪﺟﺎﻝُ ﻟﻢ ﻳﻀﺮُّﻩ،

ምንጭ:-📒ሶሒህ አት-ተርጊብ (225)

➌) «ጁምአ ቀን ላይ ሱረተል ካህፍን ያነበበ ሰው በሁለቱ ጁምአዎች መሀከል ብርሀን ያበራለታል»።

ረሱል (ሶለሏሁ ዓለይሂ ወሰለም)

ምንጭ:-📒ሶሒሁል ጃሚዕ (6470)

ﻣﻦ ﻗﺮﺃ ﺳﻮﺭﺓَ ﺍﻟﻜﻬﻒِ ﻓﻲ ﻳﻮﻡِ ﺍﻟﺠﻤﻌﺔِ ﺃﺿﺎﺀ ﻟﻪ ﻣﻦ ﺍﻟﻨﻮﺭِ ﻣﺎ ﺑﻴﻦ ﺍﻟﺠﻤُﻌَﺘَﻴﻦ

ﺻﺤﻴﺢ ﺍﻟﺠﺎﻣﻊ: (6470

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Abu Ayub shared a
Translation is not possible.

{{ሶብር صَّبْرِ}}

👉ትግስት የዚህ አለም ሀብት የመጭው አለም ስኬት ናት። አላህ ለታጋሾች ትልቅ ስጦታን ሰጣቸዋ በጀነትም አበሰራቸው።

وَلَنَبْلُوَنَّكُم بِشَيْءٍ مِّنَ الْخَوْفِ وَالْجُوعِ وَنَقْصٍ مِّنَ الْأَمْوَالِ وَالْأَنفُسِ وَالثَّمَرَاتِ ۗ وَبَشِّرِ الصَّابِرِينَ

ከፍርሃትና ከረኃብም በጥቂት ነገር፣ ከገንዘቦችና ከነፍሶችም፣ ከፍራፍሬዎችም በመቀነስ በእርግጥ እንሞክራችኋለን፡፡ ታጋሾችንም (በጀነት) አብስር፡፡

'👉'ትግስት ከኢባዳዎች አንዱና ምንዳውም የላቀ ነው። አላህ ትእግስትን ከሶላት ጋር አብሮ በማቆራኘት ጠቅሶታል።

يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا اسْتَعِينُوا بِالصَّبْرِ وَالصَّلَاةِ ۚ إِنَّ اللَّهَ مَعَ الصَّابِرِينَ

እናንተ ያመናችሁ ሆይ! በመታገስና በሶላት ተረዱ፡፡ አላህ (በእርዳታው) ከታጋሾች ጋር ነውና፡፡

الَّذِينَ إِذَا ذُكِرَ اللَّهُ وَجِلَتْ قُلُوبُهُمْ وَالصَّابِرِينَ عَلَىٰ مَا أَصَابَهُمْ وَالْمُقِيمِي الصَّلَاةِ وَمِمَّا رَزَقْنَاهُمْ يُنفِقُونَ

እነዚያን አላህ በተወሳ ጊዜ ልቦቻቸው የሚጨነቁትን፣ በደረሰባቸውም (መከራ) ላይ ታጋሾችን፣ ሶላትንም አስተካክለው ሰጋጆችን፣ ከሰጠናቸውም ሲሳይ የሚለግሱትን (አብስር)፡፡

'👉'ሳትፈተንና መከራን ሳትቀምስ ጀነትን የምታገኝ መሰለህን? አስታውስ! ጀነት ለነዚያ መከራና ችግር ባጋጠማቸው ጊዜ እንዲህ ለሚሉት ናት፦

👉''ብልህ ሰው ከችግርና መከራ ትምህርት ይወስዳል፣ ነገሮች ቢከብዱም ጌታውን  ያመሰግናል።

👉ታላቁ የትዕግስት መምህር ነብያችን ሱለላሁ አለይሂ ወሰለም ከፍ ባለ ድምፅ እዲህ ነበር ያሉት፦ "አዋጅ! የአላህ ሸቀጥ እጅግ ውድ ናት፣ የአላህ ሸቀጥ እርሷ ጀነት ናት። "

👉*እናም ችግርና መከራ ቢደራረብብህ አትዘን ተስፋ አትቁረጥም.... አላህ ምን እዳዘጋጀልህ አታውቅምና ታጋሽና አመስጋኝም ሁን

🌹وَلَسَوْفَ يُعْطِيكَ رَبُّكَ فَتَرْضَىٰ 🌹

👉ጌታህም ወደ ፊት (ብዙን ስጦታ) በእርግጥ ይሰጥሃል፡፡ ትደሰታለህም፡፡

'' አላህ ከታጋሾች ጋር መሆኑን አትርሳ።

إِنَّ اللَّهَ مَعَ الصَّابِرِينَ

👉 አላህ (በእርዳታው) ከታጋሾች ጋር ነው።

✍️አብ ኒሃል አዩብ

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Abu Ayub shared a
Translation is not possible.

🚫:::::::::ሰኸረተል መዉት:::::::::🚫

አንድ ሰዉ ለ#ሶስት /3 ቀናት በሰኸረተል መዉት ተሰቃየ ባለቤቱ ረሱል ( ﷺ ) ዘንድ አቀናች፡፡

ወይ ሞቶ አያሳርፈን እሱም አያርፍ ወይ ምላሱ ሸሐዳ አትል ግራ ገባን እኮ ያ ረሱለላህ ( ﷺ ) አለቻቸዉ፡፡

ረሱል ( ﷺ ) እናቱን አምጡልኝ አሉ፡፡ እናቱም ተጠርታ መጣች፡፡ ልጅሽ ምን አይነት ሰዉ ነዉ? ብለዉ ጠየቋት፡፡ እናትየዉም እንዲህ በማለት መለሱላቸዉ:– ከሰጋጆቹ ከዛኪሮቹ መሀል ነዉ አለቻቸዉ፡፡

ረሱልም ( ﷺ ) እሱን አደለም የምልሽ ካንቺ ጋራ እንዴት ነዉ? አሏት፡፡ እሷም ልቤ አዝኖበታል ያ! ረሱለላህ ( ﷺ ) ዋሽቼዎት በዋሕይ መጋለጥን አልፈልግም፡፡ ፈገግተኛ ፊቱን ለሚስቱ ኮስታራዉን ለኔ፣ መልካም ንግግርን ለእሷ ለዛ ቢሱን ለኔ፣ ከምግብ ጥሩዉን ከልብስ ቆንጆዉን ለእሷ እሷ ከመረጠችዉ የተረፈዉን ለኔ ስትል ብሶቷን ገለፀች፡፡

ይህኔ ረሱልም ( ﷺ ) እሳት አምጡልኛና ላቃጥለዉ አሉ፡፡ እናቲቱ ጮኸች ያ! ረሱለላህ ( ﷺ ) ልጄ የአካሌ ክፋይ እኮ ነዉ፡፡ ነብሴን ፊዳ አደርግለታለሁ አትንኩት አለች፡፡

ረሱልም ( ﷺ ) ይህን እኮ ነዉ የምልሽ አንቺ ይቅርታሽን ካልሰጠሽዉ የጀነትን ሽታ አያገኝም አሏት፡፡ ይኸዉ ጌታዬ መልዕክቶቹም ከልቤ ይቅር እንዳልኩት ምስክሮቼ ናቸዉ አለች፡፡ ሰዎችን ወደ ሰዉዬዉ ቤት ላኩ፡፡ ሰዉየዉም ሸሐዳ ከምላሱ እንደወጣ ነብስያዉ ወጣች።

✍ወዳጄ ሆይ!

ባልዋን በጀነት ማግኘት የምትፈልግ ሴት በእናቱ ሐቅ ላይ ታበረታዋለች ጀነትን የሚመኝ ሰዉ በወላጆቹ ሐቅ አይደራደርም፡፡ ከአላህ ሐቅ ቀጥሎ ከባዱ የነሱ መሆኑን አይዘነጋም እነሱ ማለት አጥፍተህም የሚወዱህ ዉብ ልቦች ናቸዉና ሁሌም ብታጠፋ ሁሌም ሁሌም ይቅርታን ጠይቅ። አደራ አደራ.።#ሼር በማድረግ ያስተላልፉ

Send as a message
Share on my page
Share in the group