UMMA TOKEN INVESTOR

BAHRU AKMEL shared a
Translation is not possible.

የሰዉ ልጅ ግን በምኑ ነዉ ሊኮራ የሚችለዉ?

ገንዘብ ፣ ዉበት፣ እዉቀት ፣ጤና፣ልጅ ሁሉም ከአሏህ ናቸዉ የሆነ ቀን ሁሉም ወደ አሏህ ይሄዳሉ ።

1,ለዘመናት ባካበተዉ ሀብታም ሁኖ ሲኩራራ በ1 ቀን ስህተት ስበብ ድሀ ይሆናል።

2,ከአሏህ በሆነ ዉበት ሲኩራራ እርጅና መጥቶ ወይም በድንገተኛ አደጋ ያጣዋል።

አረብ ሀገር ያሉ በጋዝ ፍንዳታ ምክኒያት ዉበታቸዉን ያጡ እህቶች የበፊት ፎቶአቸዉን ከአሁኑ ጋር ሲለቁት ሳይ 😓 ያ አሏህ ዉበትም በድንገት ይታጣል ።

3, እዉቀት አለኝ ብሎ መኩራራትም አደጋ አለዉ ። ብዙ በእዉቀታቸዉ ያስገረሙን ሰዎች የሰዉ ልጅ ለህመማቸዉ ስበብ ቢሆንም አዕምሯቸዉን አጥተዉ አይተናል።

4,ጤናም አያኮራ ። ድንገት በተቀመጥንበት ላንነሳ እንችላለን ። በብዙዎችም አይተናል።

5,ልጅ ልጅም ከአሏህ ነዉ ድንገት ሊታጣ ይችላል።

ሁሉም ከአሏህ ነዉ ። የአላህን ፀጋ ልናመሰግንበት እንጅ ልንኮራበት የተገባ አይደለም ።

ምን የሚያስተማምን ነገር አለና ይኮራል?

መልካም ዉሎ 💝

Send as a message
Share on my page
Share in the group
BAHRU AKMEL shared a
Translation is not possible.

ህፃናትና ስልክ‼

============

✍ አንዳንድ ወላጆች ገና ጥቅምና ጉዳትን፣ ሐላልና ሐራምን ላልለዩ ለጋ ህፃናት ይጫዎቱበት ዘንድ ስልካቸውን ይሰጣሉ። ያውም ኢንተርኔት ከፍተው፣ ያውም ቲክቶክና መሰል ሚዲያዎች ላይ ቪድዮዎችን እንዲያዩ!

ይህ ተገቢ አይደለም። ከጥቅሙ ጉዳቱ ያመዝናል። ልጆች እናንተ ተመልከቱ ብላችሁ የከፈታችሁላቸውን ብቻ ሳይሆን ሌላም ነገር መጎርጎራቸው አይቀርም።

«ይሄ አያውቁም፣ ወደ ሌላ አይገቡም!…» የሚለውን ሽንገላችሁን ተውት። የዛሬ ልጆች ሳታስቡት ቀድመዋችሁ ሄደዋል። ት/ቤት አድርሳችኋቸው መጣችሁ እንጂ ጓደኞቻቸው እነማን እንደሆኑና ማን ጋር እንደሚውሉ አታውቁም።

ስልክ አትስጧቸው። በሐላሉ ዘና እንዲሉ ብላችሁ መስጠታችሁ አስፈላጊ መስሎ በታያችሁ ጊዜ ደግሞ ገደብ፣ ህግና ደንብ አብጁላቸው። ወይ በእናንተው ቁጥጥር ሆነው ወይም በሆነ ዘዴ ይመልከቱ።

አለበለዚያ ገና ከለጋነታቸው እናንተው ራሳችሁ በራሳችሁ ገንዘብ አበላሽታችኋቸው፤ ኋላ ሲጎለምሱ ልመልሳቸው ብትሉ እንኳ ከአቅማችሁ በላይ በሚሆንበት ደረጃ ላይ ሊደርሱ ይችላሉ።

ትልቅ ኃላፊነት አለባችሁ። በዚህ እድሚያቸው ቂርኣታቸውን መቅራት፣ ትምህርታቸውን ማጎበዝና በሌሎች በሚጠቅሟቸው ነገሮች እንዲጫዎቱ ማድረግ እንጂ ጧት ማታ የስልክ ሱሰኛ እንዲሆኑ ማድረግ የለባችሁም።

ውዱ ነቢይ ይህን ብለዋል፦

( كلُّكم راعٍ وكلُّكم مسؤولٌ عن رعيتِهِ…

والرجلُ راعٍ على أهلِ بيتِهِ…)

«ሁላችሁም ጠባቂዎች ናችሁ። ሁላችሁም ስለምትጠብቁት ነገር ትጠየቃላችሁ። … ወንድ (ባል) በቤተሰቡ ጉዳይ ጠባቂ ነው።»

[አል-ቡኻሪይ: 2554፥ 2409፣ ሙስሊም: 1829፣ አቡ ዳውድ: 2928፣ አ-ት'ቲርሚዚይ: 1705፣ አ-ን'ነሳኢይ: 9173፣ አሕመድ: 5167]

√ ሳይንሱ የሚለውንም ልጨምርላችሁ። አንድ ከ13–17 እድሜ ባላቸው ታዳጊዎች ላይ የተደረገ የ Pew Research Centre ሰርቬይ እንደሚጠቁመው ከሆነ፤ 44% ታዳጊዎች ከእንቅልፋቸው ወዲያው እንደነቁ ስልካቸውን ያያሉ።

ስልክ ማብዛታቸው ከሚያስከትልባቸው የጤና ችግሮች መካከል፤ የአንገትና የወገብ (ስፓይናል ኮርድ) ህመም፣ Teen Tendonitis (TTT)፣ የስልክ ሱሰኛ ስለሚሆኑ ያለ ስልክ ሲሆኑ ከፍተኛ የድብርት ስሜት ውስጥ መግባት፣ መጨናነቅ/ ስጋት (Anxiety) ፣ ውፍረት፣ ለካንሰር በሽታም ይዳርጋል የሚል አለ። ማለትም ለ acoustic neuroma ይዳርጋል። በርግጥ እስካሁን ኮንፊርም ባይደረግም ከስልኮች የሚመነጨው ጨረር (radiation) ከስልኩ ጋር የተነካካውን የሰውነታችን ክፍል (በተለይም እጅ፣ በተለይም ኢንተርኔት ሲከፈትና እጅ ላይ ስልኩ ሲሞቅ) DNAን የመጉዳት አቅም ሊኖረው ይችላል።

ሌላው ከባዱ ችግር የእይታ (የዓይን) ችግር ይፈጥራል። በተለይም ህፃናት ለጊዜው ተፅዕኖው ጎልቶ ባይታይባቸውም እድሚያቸው ሲጨምር ገና በጊዜ ዓይነ ስውር እንዳታደርጓቸው። የcell phone vision ምልክቶቹ stress, redness, burning sensation, blurred vision, and dry eyes ናቸው።

ተጨማሪ ፔፐሮችንና ጆርናሎችን ከፈለጋችሁ እነዚህን አንብቡ።

1) Cell Phones and Cancer Risk; National Cancer Institute

2) Aswitha Priya Sadagopan, et al.; Prevalence of Smartphone Users at Risk for Developing Cell Phone Vision Syndrome among College Students; Journal of Psychology & Psychotherapy (2017).

3) Sehar Shoukat; Cell phone addiction and psychological and physiological health in adolescents; EXCLI Journal (2019).

4) Amanda Lenhart, et al.; Teens and Mobile Phones; Pew Research Center (2010).

በአጭሩ ተጠንቀቁ። የጠቀማችኋቸው መስሏችሁ እንዳትጎዷቸው። ጭራሽ አንዳንዱ ወላጅማ ለራሳቸውም ስልክ ገዝቶ የሚሰጥ አለ። ልጁም «የኔ ጓደኞች ስልክ ይዘው እኔ ብቻ…» እያለ ያለቃቅሳል። ወላጅም የኔ ልጅ ከማን ያንሳል ብሎ ይገዛል። ተወው! አሁን ያልቅስ! ኋላ ዓይኑን አጥቶ ከሚያለቅስ! አሁን የጎዳኸው መስሎት ቢጠላህም ኋላ ሲገባህ ይወድሃል። በትህትና ለነርሱ ጥቅም ብላችሁ እንደሆነ የምትከለክሏቸው አብራሩላቸው። ግን እንዳልኳችሁ ከቴክ ነክ ነገር የራቁ በደዊይ እንዳይሆኑም ለትምህርት በሚሆን መልኩ በእናንተ ክትትል አሳዯቸው።

አላህ ያግዘን! ያግዛችሁ! በዲኑም በትምህርቱም ጠንካራ ልጅ እናፍራ።

||

ወንድማችሁ፦ ሙራድ ታደሰ

=========

ኖቬምበር 28, 2023 G.C.

||

t.me/MuradTadesse

https://ummalife.com/MuradTadesse

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
BAHRU AKMEL shared a
Translation is not possible.

ሳዑዲ ግን…‼

===========

✍ አንዳንዶች በፈተና ጊዜ ይፈተናሉ‼

ምን አይነት አስተሳሰብ እንዳላቸው ባላውቅም ግራ ቀኝ ሳይመለከቱ ዝም ብለው ስሜታቸው ያመጣላቸውን እያወሩ ለአጉል ድምዳሜና ፍረጃ ይዳረጋሉ።

የሆነ ነገር በተፈጠረ ቁጥር ሳዑዲ ዓረቢያን፣ መሪዎቿንና ዑለማዎቿን ሲኮንኑ ይስተዋላል። በተቃራኒው እንደ ኢራን ያሉ በአፍ የሚያወሩ ሃገራትን ይደግፋሉ።

በሰሞነኛው የጋዛ ጦርነት ሳዑዲ ላይ የተለመደውን መርዛማ አፋቸውን የሚከፍቱ እያየሁ ነው።

እስኪ አንድ ነጥብ ብቻ ላንሳ።

ሳዑዲ ለጋዛ በጦር መሳሪያ አግዛ ጦርነቱን በይፋ ብትቀላቀል ምንድን ነው የሚፈጠረው?

የሁለቱ ሐረሞች መቀመጫ መሆኗን አታስተውሉም? ጦርነት ትግጠም የምትሉት ደግሞ ሙስሊም ጠል ከሆነች ሃገር ጋር ነው። ከሑቲ ታጣቂዎችና መሰል ሙስሊም ነን ከሚሉ ቡድኖች ጋር ቢሆን ኖሮ፤ እንደ አርማኮ ያሉ ኢኮኖሚዋን ነክ የሆኑ ነገሮችንና የመንግስት ተቋማትን ለማጥቃት ይሞክራሉ እንጂ ደፍረው ሁለቱን ሐረሞች ኢላማ አያደርጉም።

እንደ እስራኤል አይነቱ መርዛማ ግን በተለይም ሊሸነፍ መሆኑን ካወቀና ተስፋ ከቆረጠ፤ ሁለቱ ሐረሞች የዓለም ሙስሊሞች የዓይን ብሌን መሆናቸውን አውቆ ኢላማ ሊያደርጋቸው ይችላል። ወይ ተፈትኖ የተዋጣለት የሚሳኤል መቃወሚያ የላቸው።

ባይሆን ሳዑዲ አሁንም ከሞላ ጎደል እያደረገች እንዳለው ፈለስጢማውያንንና ጂሃዲስቶቹን በስውር በገንዘብ መደገፍ፣ የዲፕሎማሲ ሥራ መሥራት፣ በድብቅ የመሳሪያ ድጋፍ ማድረግ፣ ለተጎዱት ሕክምናና መሰል የእርዳታ ድጋፍ ማድረግ፣ በወራሪዋ ላይ ማዕቀብ መጣልና ሌሎችም እንዲቀላቀሉ ማድረግ፣ ሪያድ አካባቢ የሚታዩ አንዳንድ ፈሳዶችን ማስቆም… አለባት።

ከርሷ ይልቅ እንደ ግብፅ፣ ኳታር፣ ቱርክ፣ ኢራን፣ ሊባኖስ፣ የመን፣ ሶሪያ፣ ኩዌት፣ ጆርዳን… ያሉ ሃገራት ግን በቀጥታ ጦርነቱን ቢሳተፉ ችግር አልነበረውም።

በነገራችን ላይ ሳዑዲ በሃገር አቀፍ ደረጃ ለፈለስጢናዊያን ድጋፍ እያሰባሰበች ነው። 300 ሚሊዮን ሪያል ደርሳለች።

ንጉስ ሰልማንና ልጃቸው ደግሞ ከግል ገንዘባቸው 13 ቢሊዮም ዶላር ድጋፍ ሰጥተዋል። በኛ ከ1.3 ትሪሊዮን ብር በላይ ነው። እስከዛሬም በየአመቱ ዘካ ታሰባስባለች። ሃገራትን ሞቢላይዝ ማድረግ፣ ጫና መፍጠር፣ ጥቃቶችን በጥብቅ ማውገዝ፣ ማስፈራራት… አይነት ሥራዎች በደንብ ቢገፋባቸው ይሻላል። ከሳዑዲ ከዚህ የበለጠ መጠበቅ ሞኝነት ነው የሚመስለኝ።

ባይሆን የዐረብ ሃገራት የሚያናድዱኝ፤ አሁን አሁን እየከዷት መጡ እንጂ የአሜሪካ አሽከር ሆነው ገንዘብ ሳያጡ ኒዩክሌር አለመታጠቃቸው። ሌሎች ለራሳቸው እየታጠቁ ሌላውን በስምምነት ሽፋን እየከለከሉ ያንን አምነው ከመቀበል ይልቅ ቢታጠቁ ማንም በቀላሉ አይደፍራቸውም ነበር። ያለብን የኢማን ድክመት እንዳለ ሆኖ!

ያም ሆነ ይህ ለፈለስጢናውያን ከመግለጫ ውጭ ምንም የፈየዳቸው ነገር የለም። እንዳውም አንዳንድ ሃገራት በሽምግልና ሽፋን የራሳቸውን ፖለቲካና ቅቡልነት እየሠሩባቸው እንጂ አልጠቀሟቸውም። ፈለስጢን አሁን ላይ የምትሻው የ"እናዝለን!" መግለጫ ሳይሆን ያለውን መሳሪያ ይዞ አብሯቸው የሚታገል ነው። ለእናዝናለንማ ኮሎምቢያና ቺሊ ይበቁናል።

ለማንኛውም አሁንም ቢሆን የእኛ ትችትና ሙገሳ በየሰዓቱ ለሚገደሉት የጋዛ ህፃናትና ሴቶች ስለማይጠቅም፤ ሁላችንም ከልብ ዱዓእ እናድርግላቸው። አላህ ዲሉን ያቀዳጃቸው።

||

t.me/MuradTadesse

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
BAHRU AKMEL shared a
Translation is not possible.

አንድ ትንሽዬ ልጅ ለወላጆቹ፦"3 ጥያቄዎቼን የሚመልስልኝ

ጠንካራ ዑለማ አምጡልኝ" አላቸው።

ወላጆቹም በአከባቢያቸው ያለ አንድ ኡስታዝ አመጡለትና

አገናኙት።

💧ልጁ፦"ማን ነህ አንተ? እኔ ስለምጠይቀውስ ጥያቄ መልስ

እንዳለህ ምን ያህል እርግጠኛ ነህ?"

➣ኡስታዙ፦"ስሜ ዐብዱላህ ይባላል ከአላህ ባሪያዎችም አንዱ

ነኝ።ለምትጠይቀኝ ጥያቄዎችም በአላህ ፍቃድ መልስ

እሰጥሀለሁ።"

💧ልጁ፦"አንተ ግን ብዙ ዑለማኦች ሊያብራሩልኝ ያልቻሉትን

ጥያቄዬን እንደምትመልስልኝ ሙሉ በሙሉ እርግጠኛ ነህ?

➣ኡስታዙ፦"ልመልስልህ እሞክራለሁ በአላህ እገዛ።"

💧ልጁ፦" 3 ጥያቄዎች አሉኝ።

❶ ➛ እውነት ፈጣሪ አለ? አዎ አለ የምትል ከሆነ አሳየኝ የት ነው

ያለው?

❷ ➛ ቀዷ እና ቀደር ምንድነው?

❸ ➛ እውነት ሸይጣን ከእሳት የተፈጠረ ከሆነ እንዴት በእሳት

ይቀጣል? ከእሳት ተፈጥሮ እሳት አያቃጥለውም።

"ይሄን ግዜ ኡስታዙ እሳት በሆነች ጥፊ ልጁን አጮለው።

💧ልጁ፦"እንዴ!!! ለምን ትመታኛለህ? ምን ሚያስመታ ነገር

ተናገርኩ?

➢ኡስታዙ፦"አረ!!! እኔ አልተቆጣሁም ግን ያሁኗ ጥፊ ለሶስቱም

ጥያቄዎችህ መልስ ናት።

💧ልጁ፦"እንዴት? አልገባኝም...

➢ኡስታዙ፦"በጥፊ ስመታህ ምን ተሰማህ?

ልጁ፦"በጣም ህመም ተሰማኝ።

➢ኡስታዙ፦"ህመም እንዳለ ታምናለህ?"

💧ልጁ፦"አዎ አምናለሁ።"

➢ኡስታዙ፦"አሳየኝ የት ነው ያለው?"

ልጁ፦"አይ አለ ግን ማየት እንኳን አይቻልማ"

➢ኡስታዙ፦"ይህ ለመጀመሪያ ጥያቄህ መልስ ነው።ሁላችንም

አላህ እንዳለ እናምናለን ነገር ግን ማየት አንችልም።

እሺ ዛሬ እንደምመታህ ትናንት ማታ ገምተህ ነበር?"

ልጁ፦"አልገመትኩም።"

➢ኡስታዙ፦"እሺ እኔስ አንተን ዛሬ እንደምመታህ ትናንት ማታ አስቤ

ነበር?

💧ልጁ፦"አላሰብክም።"

➢ኡስታዙ፦"ለ2ኛ ጥያቄህ መልስ ይህ ነው ቀዷ ቀደር

የሚባለው።

እሺ እኔ አንተን የመታሁበት እጄ 💧ከምንድነው የተፈጠረው?"

ልጁ፦"ከአፈር"

➢ኡስታዙ፦"እሺ በእጄ የመታሁት ያንተ ፊትስ ከምንድነው

የተፈጠረው?"

ልጁ፦"ከአፈር"

➢ኡስታዙ፦"ስመታህ ምን ተሰማህ?"

💧ልጁ፦"አመመኝ"

➢ኡስታዙ፦"ከአፈር የተሰራ አፈርን ሲመታው

እንደሚያሳምመው ሁላ ከእሳት የተሰራውም ሸይጣን በእሳት

ሲቀጣ በጣም ያመዋል።"

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
BAHRU AKMEL shared a
Translation is not possible.

የአሜሪካ ሴኔት ዛሬ ከባድ መብረቅ ወርዶበታል !

ዛሬ አንቶኒ ብሊንከን የአሜሪካን በጀት አስመልክቶ ለሴኔቱ ማብራሪያ እየሰጠ ሳለ የፍልስጤም ድምፆች ከጀርባ ማስተጋባት ጀመሩ !

ከዚያ የሆነውን ቪዲዮው ላይ እዩት !

ፍልስጤሞች የአለምን ልብ እያሸነፉና የምእራቡ አለም ህዝብ ሳይቀር ወደፍልስጤም እየተከረበተ ነው !

ከዚህ በላይ ለአሜሪካም ሆነ ለእስራኤላውያን ዉርደት የለም።

4 views
Send as a message
Share on my page
Share in the group