UMMA TOKEN INVESTOR

About me

አድናቆትን ዝናን ስምን ፈልጌ ሳይሆን አሏህ በሰጠኝ እዉቅና ወንድም እና እህቶቼን ለማገልገል አንድ ጊዜ ተፈጥሪያለዉ እናም ዱኒያ አኼራሄን እንዲያሳምርልኝ በዱዓ አግዙኝ ለማንኛዉም ጥያቄ ============ 💌👇 👇 💌 @Ummamediabot 👳👳👳👳👳👳 ነብያት እና ህዝባቸዉ ነብዩም ሶሀቦ

Translation is not possible.

ሙዓዊያ እና ዐሊይ ረዲየላሁ ዐንሁማ በተጋጩ ግዜ ሁለት

ኢስላማዊ ስረወ መንግስት ተመሰረተ የሮሙ ንጉስ ይህን ሰምቶ

እንዲህ ሲል ደብዳቤ ፃፈ።

<<ከሮም ንጉሰ ነገስት ለ ሙስሊሞች መሪ ሙዐዊያ አቡ ሱፍያን!!

ባንተ እና በዐሊይ መካከል የተከሰተውን ግጭት

ሰምተናል።ስለዚህም ለሙስሊሞች መሪ አንተ መሆን

እንዳለብህም ስለምናምን አንተ ፍቃድህ ከሆነ የዐሊይን ጭንቅላት

ቀንጥሶ የሚያመጣልህን ወታደር ልላክልህ>>

ይህ ደብዳቤ ሙዐዊያ ጋር እንደደረሰም ሙዓዊያም

<<ከሙዓዊያ ለሮም መሪ!!! ሁለት ወንድማማቾች ስለተጣሉ

አንተ ምን አገባህ? አፍህን የማትዘጋ ከሆነ ጅማሬው እኔ ጋ የሆነ

እና ፍፃሜው አንተ ጋ የሆነ ሰራዊት ልኬ አንገትህን በማስቀንጠስ

ለዐሊይ በስጦታ መልኩ አበረክትለታለሁ>>

#ይህ_ትክክለኛ_ሙስሊሞች_ሳለን_ነው

_____

___

ካሊድ ኢብን ወሊድ ለፐርሺያው ንጉሰ ነገስት እንዲህ ሲል

ደብዳቤ ፃፈለት

<<ስለም ትድናለህ። እንቢ ያልክ እንደሆን ግን፤ እናንተ ህይወትን

የምትወዱትን ያህል ሞትን የሚወዱ ሰራዊቶችን ይዤልህ

እመጣለሁ።>>

ንጉሱ ይህን ደብዳቤ ካነበበ በኋላ የቻይናውን ንጉስ የጦር እርዳታ

ሊለምነው ደብዳቤ ፃፈለት።

የቻይናውም ንጉስ እንዲህ ሲል ደብዳቤ መልሶ ላከለት።

<<ንጉስ ሆይ! ተራራን እንኳን ለመናድ ካሰቡ ምንም

ከማያግዳቸው ወታደሮች ጋር ለመጋፈጥ አቅሙ ስለሌለኝ

ጥያቄህን መፈፀም አልችልም።>>

# ምን_ያህል_ሀያላን_እንደነበርን_ተመልከቱ

_____

____

በደውለቱል ዑስማኒያ የአገዛዝ ዘመን የሙስሊም ወታደሮች የጦር

መርከቦቻቸውን ይዘው በአውሮፓ ደሴቶች ሲያልፉ በአከባቢው ያሉ

አብያተ ክርስትያናት በሙሉ ሙስሊሞች መጥተው ፈትህ

እንዳያደርጉ በመፍራት ከበሮ ከመምታት እና ምንም አይነት ድምፅ

ከማሰማት ይቆጠቡ ነበር።

#ያኔ_ጀግና_ሳለን

_____

____

በደውለቱል ኡስማኒያ የአገዛዝ ዘመን በያንዳንዴ ቤት ደጅ ላይ

ሁለት የበር ማንኳኩያዎች ይኖራሉ። አንዱ ትልቅ ሲሆን አንዱ ትንሽ

ነው። በትልቀኛው ከተንኳኳ አንኳኪው ወንድ ነው'ና በሩን ሊከፍት

ሚመጣው ወንድ ይሆናል። ነገር ግን በትንሸኛዋ ከተንኳኳ

አንኳኪዋ ሴት መሆኗ ስለሚታወቅ ሴት ትከፍትላታለች።

በዚያ ምርጥ ዘመን አንድ ቤት ውስጥ ሰው ከታመመ ደጅ ላይ

ቀይ አበባ ይንጠለጠል ነበር። ያን አበባ የተመለከቱ ሰዎች ሁሉ

እዝያ ቤት በሽተኛ መኖሩን ስለሚያውቁ በበሩ ሲያልፉ ድምፃቸውን

ዝቅ ያደርጉ ነበር።

#ሹፍ_ምን_እንመስል_እንደነበር !!!

_____

_

ግዜው ሰላሁዱን አል አዩቢ በይተል መቅዲስን ባስመለሰበት ግዜ

ነበር። እና ጦርነቱ ነገውን ሊጀመር ማታ ላይ የጦር መሪው

ሰላሁዲን የወታደሮቹን ድንኳን እየዞረ ሲያዳምጥ፤ ግማሹ ለይል

ይሰግዳል፣ ሌላው ቁርአን ይቀራል፣ የተቀሩት ደግሞ ይዘክራሉ።

ግን ድንገት በሆነ ድንኳን አጠገብ ሲያልፍ በድንኳኑ ውስጥ ያሉት

ሁሉም ተኝተው ነበር። ይህን ግዜ፦"በዚህች ድንኳን አዳሪዎች

ምክንያት ልንሸነፍ እንችላለን" ብሎ አለፈ።

#ማንተኛበት_ዘመን

_____

___

ቀደምት ዑለማኦች በሶስት ነገራት አደራ ይባባሉ ነበር።

1፦ሰውዬው በሱ እና በአላህ መካከል ያለውን ግንኙነት ካሳመረ፤

በሱ እና በሌሎች መካከል ያለው ግንኙነት ያምርለታል።

2፦ሰውዬው ሚስጥራዊ ተግባሩን ካሳመረ አላህ ይፋዊ ተግባሩን

ያሳምርለታል።

3፦ሰውዬው የአኪራው ጉዳይ ካስጨነቀው አላህ የዱንያውንም

የአኪራውንም ጉዳይ ያግራራለታል።

_____

_

#ትልቁ_ኪሳራ_ማለት_ይህ_ነው

ጀነት ስፋቷ የምድርን እና የሰማያትን ያህል ሁና ላንተ በሷ ቦታ

ሳይኖርህ ሲቀር...ትልቅ ኪሳራ ነው።

በእለታዊ ፕሮግራምህ ውስጥ ቁርአንን መቅራት ካልተካተተ ትልቅ

ኪሳራ ነው።

ይህን ፅሁፍ በማሰራጨት ጓደኛህን እንድታነቃው ይከጀላል!

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

Follow & Share → Umma ሚዲያ

↓↓↓↓↓

Umma ሚዲያ

ከነቢ ሰዐወ ህልፈት በኋላ ሰሃባዎች ወደ ተለያዩ የአለማችን

ክፍሎች ተበትነው ዘመቻ ላይ ናቸው።

ሳዕድ ኢብኑ አቢ ወቃስ ረዐ በታዘዘው መሰረት ሰራዊቱን ይዞ

ከፐርሺያ ምድር ተከስቷል። ያ በዐረብያ ምድር ያለ ስልጣኔ የኖረ

ማህበረሰብ ትልቁን የስልጣኔ መገለጫ የሆነውን ፐርሺያን በጦር

ሊገጥም አኮብኩቧል።

የፐርሺያው ስረወ መንግስት እልፍ አዕላፍ የሆነ የሰራዊት ማዐት

አሰልፎ ቁጥራቸው እና ትጥቃቸው እዚህ ግባ ከማይባሉ

ሰሓባዎች ጋር ሊፋለም ድንኳናቸውን ተክለው ማዶ ለማዶ

ይተያያሉ።

በዚህ መሃል የሰሓባዎቹ የጦር አዛዥ የሆነው ሳዕድ ከሰራዊቱ 7

ወጣቶችን መልምሎ የፐርሺያ ሰራዊቶችን ሁኔታ እንዲያጣሩ እና

ከቻሉም አንድ የፐርሺያ ወታደር ጠልፈው እንዲመጡ ላካቸው።

7 ሁነው ጉዞ ጀመሩ። ትንሽ እንደተጓዙም በርከት ያለ ቁጥር

ያላቸው የፐርሺያ ወታደሮችን ከርቀት ሲመጡ ተመለከቱ'ና

መቋቋም ስለማይችሉ ለመመለስ ወሰኑ።

ግና ከመካከላቸው በሀሳባቸው ሳይስማማ ቀርቶ አንደኛው

«የታዘዝኩትን ሳልፈፅም አልመለስም» በማለት ተልዕኮውን

ለማሳካት ጎዞውን ቀጠለ። 6ቱ ትተው ተመለሱ።

ጉዞውን በእርጋታ እና በመጠንቀቅ ቀጠለ። ሰራዊቱን በውሃ

ድልድዮች ተደብቆ ከተሻገረ በኋላ ማንም በማያውቀው ሁኔታ

ከ40,000 ሰራዊት እንብርት ላይ ተከሰተ።

ከሰራዊቱ መሀል ላይ ቁሞ ሩቅ እያማተረ ሲመለከት ከርቀት ነጭ

ድንኳን እና ከደጁ የቆመ የንጉሳን ፈረሰ ከአይኑ ገባ።

«ይህ የጦር አዛዣቸው የሩስቱም ድንኳን መሆን አለበት» ብሎ ወደ

ድንኳኑ ተጠግቶ ሌሊቱ ፅልመቱን ለምድር እስኪያልብስ እዝያው

ቁጭ አለ።

ፀሀይ ጠልቃ ምድር በፅልመት ስትወረር፣ ሰራዊቱ ከብርዱ

ጭጋግ ሽሽት ከየድንኳኖቻቸው ሲወሸቁ፤ ወጣቱ ሰይፉን

ከማንገቻው መዝዞ ወደ አዛዡ ድንኳን አመራ።

ከድንኳኑ ደጅ ሲደርስም የድንኳኑን ማዋቀርያ ገመዶች በሰይፉ

ቆራርጦ ሙሉ ድንኳኑ በአዳሪያኑ ላይ ሲወድቅ እሱ ደጅ ላይ

የታሰረውን ፈረስ ፈትቶ ጎዞውን ቀጠለ።

ፈጣን ፈረሰኞች ኮቴውን ተከትለው ያሯርጡት ጀመር፤ ከፈረስ

ጀርባ ያደገው የዐረብያ ብላቴናውም አሸዋውን እያቦነነ ከፊታቸው

ይከንፋል።

በመጨረሻም ከሁሉም ርቆ ሶስት ፈረሰኞች ብቻ ሲያሯርጡ

ደረሱበት። ከሶስቱ ፈረሰኞች የግድ አንዱን ይዞ ወደ አሚሩ መሄድ

ስለሚጠበቅበት ሊያጃጅላቸው ፈልጎ ሲደርሱበት እያመለጣቸው፤

በጣም ሲራራቁ እየጠበቃቸው ከክልላቸው አስወጣቸው።

ከዝያም ዞሮ ሰይፍ ተማዘዛቸው፤ ብዙም ሳይቆይ ሁለቱን ገድሎ

አንዱን አስሮ ይዞት ከፊት ከፊት እየነዳው ጉዞ ወደ አሚሩ ጀመረ።

ልክ የሙስሊሞችን ሰራዊት ደርሶ ምርኮኛውን ከአሚሩ ፊት

ሲያቆመው ምርኮኛው ለአሚሩ፦ «ከለላህን ስጠኝ እኔም

ዕውነታውን ላውራ» አለው።

«እኛ የዕውነት ህዝቦች ነን፤ ከላላችንን የምንሰጥህ እማትዋሸን

እንደሆን ነው» አለው አሚሩ።

ንግግሩን ቀጠለ፦ «እስቲ ስለ ፐርሺያ ሰራዊቶች ንገረኝ»

ምርኮኛው፦ «ስለ ፐርሺያ ሰራዊት ስብጥር ከመናገሬ በፊት ስለ

ጀግናው ጓድህ ላውጋህ።

ከልጅነቴ አንስቶ የጦርነት ሜዳ ላይ ነው ያደግኩት እንዲህ አይነት

ሰው አይቼም አላውቅም። ሁለት ጠንካራ የሰራዊት ቡድኖችን

አልፎ በመግባት የአዛዣችንን ድንኳን ቆራርጦ ጣለ'ና ፈረሱን ይዞ

ጋለበ።

ለ3 ሁነን እስከ መጨረሻ ተከታተልነው። ከፈረሱ ወርዶ

ተፋለመን'ና የ1000 ፈረሰኛ ግምት የምንሰጠውን ጀግናችንን

ገደለው።

ሁለተኛውንም የጦር መኳንንት በ1000 የምንገምተው ሲሆን

እሱንም እያየሁ ገደለው። ሁለቱም ያጎቶቼ ልጆች ነበሩ።

ይህ ድርጊቱ እልህ በልቤ ቋጥሬ ልገድለው ባለ በሌለ ጉልበቴ

እንዳሯሩጠው አስገደደኝ። የኔ አይነት ጉልበታም ከወታደሩ ይኖራል

ብዬ ባልገምትም ባላሰብኩት መልኩ የዚህ ልጅ ምርኮኛ ሆኜ

መጣሁ።

የዚህ አይነት ጀግና አንድ ካላችሁ መቼም አትሸነፉም» አላቸው።

በመጨረሻም እስልምናን ተቀበለ።

የሙስሊሞቹ ወታደሮችም ምድር አንቀጥቃጭ የሆነ ጦርነት

አድርገው ፐርሺያን ሙሉ በሙሉ ደምስሰው ድልን ተቀዳጁ።

ያ ጀግናው ሰሓቢይም ስሙ ጡለይሃ ቢን ኩወይሊድ ዱንያ

እስካለች ድረስ ሲወሳ ይኖራል።

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

Follow & Share → Umma ሚዲያ

↓↓↓↓↓

Umma ሚዲያ

አዲስ ቤት ገዛህ? ዝም በል አታውራ

አዲስ መኪና ገዛ? አትናገር

ትዳር መሰረትክ? ብዙ አታውራለት

ለመዝናናት ከከተማ/ሀገር ወጣ ብለህ ነበር? ዝም በል

ንግድ ልትጀምር ነው? ድምፅህን አጥፋ

ኑሮ እየሰመረልህ ነው? ብዙ አታውራ

አብዛኛውን ጊዜ

ያሰብናቸው ህልሞች እና የወጠንናቸው ራእዮች የማይሳኩበት

ዋነኛው ምክንያት ከመከናወናቸው በፊት ብዙ ስለምናወራ ነው -

ገና እንቁላሉን ስንታቀፍ ማውራት እንጀምርና ብዙ

ሸለምጥማጦችን እንጠራለን::

ወዳጅ እና የቅርብ ሰዎች የምንላቸው ሰዎች "ሰዋዊ ቅናት" እና

"የጥሎ ማለፍ ውስጣዊ ትንቅንቅ" በጣም የሚጠበቅ ተፈጥሯዊ

ሁነት ነው:: ስለዚህ ህልሞችህ መስመር ይዘው ፍሬ እስኪያፈራ

ድረስ ዝም ብለህ መስራትን ምረጥ::

አብዛኛው ሰው

ቢያልፍልህ እና ህልምህ ቢሰምርልህ ደስ ይለዋል ሆኖም ግን

ጥለኸው እንድትሄድ እና አንጋጦ ሊያይህ ይተናነቀዋል::

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

Follow Share → Umma ሚዲያ

↓↓↓↓↓

Umma ሚዲያ

#ሐብታም ብትሆን፣ የምትጠራው ሐብታም #ሰው ተብለህ ነው።

#የተማርክም ከሆንክ፣ የምትጠራው የተማረ #ሰው ተብለህ ነው።

#ቀይም ብትሆን፣ ቀዩ #ሰው ነው ምትባለው።

#ቆንጆም ብትሆን፣ ቀንጆ #ሰው ነው ተብለህ ምትጠራው። ከነዚህ አይነት ሰዎች አንዱም ብትሆን በየትኛውም መልኩ ከሰውነት አትወጣም።

#ልብ በል! እነዚህ ከላይ #ሰው ከሚለው ቃል በፊት የተቀመጡት ስሞች ሰው ከሆንክ በሗላ የተቸሩህ እንጅ ሰው ከመሆንህ በፊት የተሰጡህ ፀጋዎች አይደሉም።

ከጊዜ በኃላ የተሰጡህን ነገሮች ደግሞ በጊዜ ምክንያት ልታጣቸው ትችል ይሆናል። በየትኛውም መልኩ ግን ሰውነትህን ሊነጥቅህ የሚችል ማንም የለም።

#ሁሉም ሰው ሲማር ሙሁር ሳይማር ሲቀር መሃይም ነው።

#ሁሉም ሰው ከሰራ ሐብታም ካልሰራ ደሃ ነው።

#ሁሉም ሰው ሲደላው ያምርበታል ሲቸግረው ያስጠላበታል።

#ሁሉም ሰው ፀሐይ ሲበዛበት ይጦቅራል። አየሩ ሲመቸው ይቀላል። ስለሆነም፥

#ሁሉም ሰው ከአደም ነው።

#ሁሉም ሰው እኩል እናቱ መሃፀን ውስጥ ለዘጠኝ ወር ነው የተረገዘው።

#ሁሉም ሰው ከአንድ ፈጣሪ ነው።

#ሁሉም ሰው የሚበላው ምግብ፣ የሚጠጣው መጠጥ የሚያስፈልገው ከመሆኑ ጋ የበላውንና የጠጣውንም ነገር የማስወገድ ግዴታ አለበት።

#ሁሉም ሰው ታማሚም ሟችም ነው። ወዘተ...

#ሰው ምንም ወደላይ ቢንጠራራ ከሰውነት ተራ ወጥቶ መላዕክ ሊሆን አይችልም።

#ምንም ቢቸገርና ቢጎሳቆል ወደ እንሰሳነት ሊወርድ አይችልም።

#ሰው በየትኛውም መልኩ ሰው ነው!

አላህ የሰውን ልጅ ከሁሉ አልቆታልና፤ ሰውም ሰውን እኩል ሊያይና ሊያከብር ግድ ይለዋል! በመጨረሻም ይህችን ግጥም ተጋበዙልኝ!

👇

#የሰው_ዛፍ

ምነው የሰው ልጆች፣ ልዩነት መረጡ፣

ከአንድ ዛፍ በቅለው፣ መበላለጥ ሻቱ፣

ያ'ንድ ዛፍ ቅርንጫፍ፣ ስሩ አንድ መሆኑን፣

ማየት ተስኗቸው፣ ዘንግተውት ይሆን?

ያ'ንድ ዛፍ ፍሬዎች፣ ሁሉም አንድ አይነት ነው።

ማንጎ ሎሚን ማፍራት፣ የማይታሰብ ነው።

ዛፉ ማንጎ ከሆን፣ ፍሬውም ማንጎ ነው፣

ዛፉ ሰው ከሆነም፣ ፍሬውም ያው ሰው ነው።

ምናልባት አንዱ ሰው፣ ካ'ንዱ የሚበልጠው፣

አላህን በመፍራት፣ ብቻና ብቻ ነው።

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

Follow & Share → Umma ሚዲያ

↓↓↓↓↓

Umma ሚዲያ

ሒጅራ 15ኛው አመት ላይ ሰሓባዎች የዐረብያን ምድር በአንድ

ስረወ መንግስት የሚተደደር ግዛት አድርገውት በአቡ በክር

አማካይነት ተቆጣጥረውታል።

ሰሀባዎቹ በነቢ ሰዐወ መሞት ያነቡት እንባ ባይነጥፍም

ስሜታቸውን ዋጥ አድርገው ዘመቻዎችን እየተሳተፉ ይገኛሉ።

በሳዕድ ኢብኑ አቢ ወቃስ የሚመራው ክፍለ ጦር 30,000 የነቢ

ሙሪዶችን ይዞ ከዒራቅ መግብያ ከሚገኘው ሜዳ ላይ ተሰልፏል።

ያኔ ዒራቅ በፐርሺያን ስረወ መንግስት ውስጥ የምትገኝ ግዛት

ስትሆን የነቢ ሙሪዶችን ለመጋፈጥ 200,000 ሰራዊቶችን እና

33 የጦር ዝሆኖችን በጦር መሪያቸው ሩስቱም አማካይነት

አሰልፈዋል።

የምድራችን ሁለቱ ተፅዕኖ ፈጣሪ ስረወ መንግስቶች

ሰራዊቶቻቸውን አሰልፈው ውግያ ሳይጀምሩ ለተወሰኑ ቀናት ማዶ

ለ ማዶ ሲፈጠጡ ከረሙ።

«መልዕክተኞቻችሁን ላኩልን'ና እንግባባ» የሚል መልዕክት

ከፐርሺያው ጦር አዛዥ ወደ ሰሀባው ሳዕድ ተላከለት።

ሳዕድ'ም ከጀግኖቹ መሀል ሪብዒይ የተሰኘውን ሙሒብ መርጦ

ወደ ፐርሺያውያኑ የጦር ካምፕ ላከው።

ሪብዒይ መልከ መልካም እና የወንድነት ወኔ ከፊቱ የሚነበብ

ብርቱ ሙጃሂድ ነው። ከፈረሱ ጀርባ እየከነፈ ከካምፑ ደረሰ።

ስፍር ቁጥር የሌላቸው ሰራዊቶች ተሰልፈዋል፣ በርካታ የጦር

መገልገያዎቻቸው ዝግጁ ሆነው በየቦታዎቻቸው ተቀምጠዋል።

ዐረቦቹ የማያውቋቸውን የጦር መገልገያዎች በየቦታው

ቢመለከተውም ግድ ያልሰጠው ሪብዒው የፈረሱን ልጓም

ወደተላከበት ለጎመው።

የጦር አዛዡ ከሚገኝበት ድንኳን ደረሰ። በአንፀባራቂ መጋረጃዎች

የተሽሞነሙነው ድንኳን በውስጡ ባለ ጌጥ ትራሶች እና

ምንጣፎች ተነጥፈውበት አይቶት የማያውቀውን የቤት ውስጥ

ጌጦችን ተመለከተ።

የነቢ ሙሪድ ዱንያ ምን ገዶት! ከአፈር ተቆፍረው ለሚወጡ

የማዕድናት ጌጥ መማረክን ነቢም አላስተማሯቸውማ!

ሪብዒይ ከፈረሱ ጀርባ ከነግርማ ሞገሱ ተሰይሞ የድንኳኑን

መግብያ ዘልቆ ገባ። የጦር አዛዡ የወርቅ ዘውዱን ከራሱ ላይ

ደፍቶ በዙፋኑ ላይ ሁኖ በአግራሞት ይመለከተዋል።

ሪብዒይ የተንኳሰሰች ልብሱን ለብሶ፣ ሰይፉን ከወገቡ ታጥቆ፣

ከድንኳኑ ስር በተነጠፈው ምንጣፍ የተወሰነ ርቀት በፈረሱ ከሄደ

በኋላ ፈረሱን ከወርቃማው ትራስ ላይ ሸብ አድርጎ ወደ ዙፋኑ ሄደ።

ከዙፋኑ ዙርያ ከተሰለፉት ጠባቂዎች አንዱ አስቆመው'ና፦

«ትጥቅህን እዚህ ጋር ፍታ» አለው።

ፍርሀትን መች ያውቅና! ፈሪ አላሰለጠነው'ማ!፦ «ስማ እኔ ትጥቄን

ስታዙኝ ልፈታ አይደለም እዚህ የመጣሁት። ጠርታችሁኝ

መጥቻለሁ ከነ ትጥቄ መግባት ከከለከላችሁኝ መመለስ

እችላለሁ» ብሎ መለሰለት።

«ተዉት ይምጣ ከነ ትጥቁ» አለ የጦር አዛዡ ሩስቱም ከዙፋኑ ላይ

ተደላድሎ ቁልቁል እየተመለለታቸው።

ሪብዒይ ከቆመበት ጀምሮ እስከ ዙፋኑ ድረስ የተደረደሩትን የጌጥ

ትራሶች እና የንጉሳን ምንጣፎችን በአሸዋማ ጫማው እየረገጠ

ከዙፈኑ ፊት ቆመ።

«ለምንድነው እዚህ ድረስ የመጣችሁት?» ብሎ ጠየቀው የጦር

አዛዡ። የዐረቢያ ነገዶች ለልመና እንጂ ለጦር የፐርሺያን ምድር

ሲረግጡ ተስተውለው ስለማያውቁ።

የቀድሞው ታሪኩ ምንም አላሸማቀቀውም። ገጠሬነቱ ባጎናፀፈው

የወኔ ገፅታ ቀና ብሎ፦ «አላህ ልኮን ነው። አላህ ፍጡራንን

ከፍጡራን አምልኮ ነፃ አውጥተን ወደ ፈጣሪ አምልኮ እንድናስገባ፣

ከዱንያ ጥበት ወደ ሰፊው ኢስላም፣ ከሀይማኖቶች አድሎ ወደ

ፍትሀዊው ኢስላም እንድናሸጋግር ልኮን ነው።

ይህን ይዘን መልዕክቱን ለሰው ልጅ በሙሉ እናስተጋባለን። ይህን

የተስማማ ተስማምተነው ትተን እንመለሳለን፤ አሻፈረኝ የሚል ካለ

ተጋድለነው ከጌታው ፊት ይዘነው ለፍርድ እንቆማለን።»

በመጨረሻም ቃል ከገቡ የማያፈገፍጉ የኑረል ካኢናቱ ሙሒቦች

በቃል ኪዳናቸው መሰረት ለክፍለ ዘመናት አለምን የገዛውን ስረወ

መንግስት በጣት በሚቆጠሩ ቀናት እንደ ወደመ አውድማ

አድርገው ፈጇቸው። ሀገራቸውንም ተቆጣጥረው ከግዛታቸው

አካለሉ።

"የደረሳውን ማንነት ልታውቅ ኡስታዙን ተመልከት" እንደሚሉት ሁላ

የሰሀባዎቹን ማንነት ለማወቅ ነቢን ሰዐወ መመልከት በቂ ነው።

_________

ምንጭ፦

ﺍﻟﺒﺪﺍﻳﺔ ﻭﺍﻟﻨﻬﺎﻳﺔ ﻻﺑﻦ ﻛﺜﻴﺮ

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

Follow & Share → Umma ሚዲያ

↓↓↓↓↓

Umma ሚዲያ

ሁለቱም ማዶ ለማዶ ተፋጠዋል፤ የግመሎቹ ባለቤት ለሚወስደው

ማንኛውም እርምጃ ሰውዬአችን አፀፋውን ለመመለስ ቀስቶቹን

ወጥሯል።

ከርቀት የቆመው መልከ-መልካም ወጣት፦«እስቲ ከጎንህ ያለውን

ልጓም አንጠልጥልልኝ» አለው።

ሰውዬው ልጓሙን አንስቶ ሲያንጠለጥለው ሶስት ቋጠሮዎች

ከገመዱ ላይ ይታያሉ።

ወጣቱም በራስ መተማመን እፊቱ ላይ እየተስተዋለ፦«በየትኛው

ቋጠሮ ላይ ቀስቴን እንድሰካ ትፈልጋለህ...?»

ሰውዬው ግራ በመጋባት ገመዱ ላይ ተቋጥረው ከሚታዩት

የመሀከለኛዋን አመላከተው። ወጣቱም ከርቀት የቀስቱን

ማስወንጨፍያ ስቦ ፍላፃዋን ከመሀልኛው ቋጠሮ ላይ ሰካት።

እንዲህ እንዲህ እያለ በሶስቱም ቋጠሮዎች ያለምንም መሳት

ቀስቶቹን ከርቀት ሰክቶ በፍልምያም ሆነ በውግያ አቅሙን

አሳየው።

ሰውዬአችን ማመን የማይችለውን በአይኑ ሲመለከት የታጠቀውን

ሰይፍ እና ቀስቶች ወደ መሬት ጥሎ ፈዞ ማየት ጀመረ።

ወጣቱም ወደ ሰውዬው በመምጣት ሰይፉን እና ቀስቱን

ተቀብሎት ፈረስ ላይ ጭኖ ይዞት ሄደ።

«አሁን በቁጥጥሬ ስር ውለሀል። ምን ማደርግህ ይመስልሀል?»

ወጣቱ ጠየቀው።

«ትበቀለኛለሃ!» አለው ሰውዬአችን።

«ለምን?» ወጣቱ ጠየቀ።

«ያው ለሰራሁት ዝርፍያ እና በደል ነዋ፤ አሁን ፈጣሪ

አመቻችቶልሀል ትበቀለኛለህ» አለው።

ወጣቱም፦«እንደው ከሙሀልሂል ዘንድ ማዕድ ተጋርተህ፣ አብረህ

አድረህ የምበቀልህ ይመስልሀል?»

ሰውዬው በዝና የሚያውቀውን ስም ሲሰማ ድንግጥ አለ፦«አንተ

ዘይዱል ከይል ነህ?»

«አዎን» ወጣቱ መለሰለት።

«እባክህ መጥፎ አጋች አትሁነኝ» ሰውየው ይማፀን ጀመር።

«ስጋት አይግባህ!» አለ ወጣቱ።

ረጅሙን ጉዞ ከተጓዙ በኋላ ሽማግሌው ከሚገኙበት ስፍራ

ደረሱ።ከኋላቸው በርካታ ግመሎችን አስከትለዋል።

ወጣቱ ወደ ሰውዬአችን ዞር አለ ና፦«እምልልሀለሁ፤ እነዚህ

ግመሎች የኔ ቢሆኑ ሁሉንም እሰጥህ ነበር። ግና የእህቴ ነው።

ባይሆን ጥቂት ቀናት እኔ ዘንድ ትቆያለህ፤ እንዲያው ሰሞኑን አንድ

የምዘምተው ወረራ አለኝና ያን ምርኮ በሙሉ ላንተ እሰጥሀለሁ።»

ተስማሙ። በእንግድነት ልክ 3 ቀናትን እንዳሳለፈም ወጣቱ

ትጥቁን ታጥቆ አንድ ሙሉ መንደር ላይ በመዝመት ከ 100 በላይ

ግመሎችን ማርኮ እየነዳ መጣ።

ያመጣቸውን የምርኮ ግመሎችም አንዳች ሳይቀንስ ለሰውዬአችን

አስረክቦ ሰውዬውንም እስከ ቀዬው ድረስ የሚያደርሱትን

አገልጋዮች ጨምሮ ሸኘው።

ወራትን የሚወልዱት ቀናት እየተፈራረቁ በርካታ አመታትን ወልደው

አስቆጠሩ፤ አመታት እየነጎዱ በአመታት ተተኩ።

ወጣቱ ዘይድ የወጣትነትን እድሜ ተሻግሮ ግርማ ሞገስ ያለው

ጎልማሳ ሁኗል። ከእለታት አንድ ቀን ሙሀመድ ስለተባለ ነብይ

ይሰማው የነበረውን መረጃ በአካል ሄዶ ለማረጋገጥ የቀዬውን

መሳፍንት አማከራቸው። አብረው መዲና ለመሄድም ተስማሙ።

ዘይዱል ከይር ከቀዬው መሳፍንቶች ጋ ሁኖ ልክ መዲና እንደገባ

የጉዞ አዋራውን ከጀርባው ሳያራግፍ ወደ ነቢ ሰዐወ መስጅድ

አቀና።

ከመስጅዱ ቅጥር ግቢ እንደገቡም ፈረሶቻቸውን ከደጃፍ አስረው

ወደ መስጅዱ ዘልቀው ሲገቡ ቀና ብሎ ለማየት የሚያጓጓው

ነብይ ከሚንበር ላይ ቁመው ኩጥባ እያደረጉ ተመለከቱ።

ነቢ ሰዐወ ኩጥባቸውን ቀጥለዋል፦«ህዝቦቼ ሆይ! እኔ

ከአማልክቱ ዑዛ እሻላችኋለሁ። እኔ ከምታመልኳቸው ጥቋቁር

ግመሎች ለናንተ የተሻልኩ ነኝ»

ውዴ ንግግራቸውን ቀጥለዋል። ዘይድ በትኩረት አይኑንም

ጆሮውንም ሰጥቶ እያዳመጠ ነው፤ ግና የኢማን ስፍር መለክያዋ

ለከፊሉ ኢማንን ወፍቃ ለተቀሩት ክህደት ላይ ክህደትን

በመጨመር ዘይድንም ከኢማን ሰዎች መደበችው።

ከመሀከላቸው አንደኛው መሳፍንት ወደ ጓደኞቹ ጠጋ ብሎ፦«እኔ

ይህ ሰው መላ ዐረብን እንደሚቆጣጠር ምንም ጥርጥር የለኝም፤

እኔ ደሞ በአረቢያ ምድር ተቀምጬ በዚህ ።ሰው ቁጥጥር ስር

መዋልን ስለማልፈልግ ፀጉሬን ተልጬ ከደማስቆ ገዳም

እከትማለሁ » ብሎ ከተወሰኑ ጓደኞቹ ጋ ትቶ ሄደ።

ዘይድ እና የተወሰኑ ጓደኞቹ እዝያ ኩጥባው እስኪጠናቀቅ ረግተው

ተቀመጡ። ልክ ነቢ ሰዐወ ከሚንበራቸው ሲወርዱ ዘይድ ብድግ

ብሎ ድምፁን ከፍ በማድረግ፦« ሙሀመድ ሆይ! በአላህ ጌትነት

ያመንኩ ስሆን ባንተ መልዕክተኝነትም አምኛለሁ» አለ።

ነቢ ሰዐወ ሰልፉን እያቆራረጡ ወደ ዘይድ መጡ ና፦«ማን ነህ?»

አሉት።

«እኔ ዘይዱል-ከይል የሙሀልሂል ልጅ ነኝ»

«አይ አንተ ዘይዱል ከይል ሳትሆን ዘይዱል ከይር ነህ። ጋራ

ሸንተረሩን አቆራርጦ ሊኢስላም ቀልብህን ከፍቶ ያመጣህ አላህ

ምስጋና ይገባው» አሉ።

ነቢ ሰዐወ እንግዳ አክባሪ ናቸው። እንግዳቸውን እና የተወሰኑ

ሰሀባዎችን ይዘው ወደ ቤታቸው ሄዱ። ዘይድ ልክ ነቢ ሰዐወ ቤት

ገብቶ ከመደቡ ላይ አረፍ ሲል ነቢ ሰዐወ ትራስ አቀበሉት።

ከሳቸው ፊት ሁኖ ትራስ ላይ መንተራስ የከበደው ዘይድም ትራሱን

መልሶ ሰጣቸው፣ መልሰው ሰጡት፣ መልሶ ሰጣቸው፣ መልሰው

ሰጡት።

ከዝያ ተረጋግተው ማውጋር ጀመሩ።

«ዘይድ! እኔ ብዙ ሰው ባህሪው ከሩቅ ተነግሮኝ በአካልም

ተመልክቼዋለሁ። ግን ዝናውን ሰምቼ በአካልም ሳገኘው ከዝናው

ጋር እንዳንተ የተመሳሰለብኝ ሰው የለም። እና እንዴት ነህ?...»

ነቢ ጫወታ ያውቃሉ እኮ።

«ያው መልካምን እና ሰሪዎቹን እወዳለሁ። መልካም ነገር ሰርቼ

ስጨርስ እረካለሁ፤ ሲያመልጠኝም እቆጫለሁ» አላቸው።

«ይኼማ! አላህ በመረጣቸው ባሮች ላይ የሚያደርገው መለያ

ምልክት ነው» አሉት።

ወደሳቸው ዞር ብሎ፦«አላህ እና መልዕክተኛው በሚሹት ነገር ላይ

ላዋለኝ አላህ ምስጋና ይገባው።

ባይሆን እስቲ 3 መቶ ፈረሰኞችን ይስጡኝና የሮም ስረወ

መንግስትን ደምስሼ ምርኮውን ላምጣ።» አላቸው።

ነቢ ሰዐወ ነገሩ ገነነባቸው ና፦« አይ!!! ዘይድ እንዴት ያለህ ደፋር

ሰው ነህሳ!?» አሉት።

ዘይድ ለተወሰኑ ቀናት መዲና የነቢን ሰዐወ ኮቴ እየተከታተለ

ካሳለፈ በኋላ የቀዬውን ሰው ከዲኑ ሊያቀላቅል መዲናን ትቶ

ወጣ።

እሱን ሊሸኙ የወጡት ነብይም የአሸዋው አዋራ ከአይናቸው

እስኪሰውረው ድረስ እየተመለከቱት፦«ወይ ዘይድ! የመዲናን

ወረርሽኝ ባልፈራለት ኖሮ እዚህ ተቀምጦ ስንት እና ስንት ጀብድ

ይፈፅምልኝ ነበር» አሉ።

ዘይድ ከጓደኞቹ ጋር ሁኖ የመዲናን ግዛት ትቶ ወጣ። መዲና ላይ

በተከሰተው ወረርሽኝ ዘይድ መለከፉን ሳያውቅ ከአሸዋማው ሜዳ

ላይ ህመሙ ያጥወለውለው ጀመር።

ሞትን ተሽቀዳድሞ የዲኑን ብርሀን ለቀዬተኛው ሊያደርስ ከሞት

ጋር ቢፎካከርም ከተወሰነለት ሰአት ቅፅበትን የማይዛነፈው ሞት

ዘይድን የመጨረሻዋን ትንፋሽ አስተነፈሰው።

በኢስላም ጥላ ስር ከመግባቱ በፊት የፈፀማቸውን አያሌ

መልካም ስራዎች አላህ ሊመነዳው መዲና አምጥቶ ከነቢ

ካገናኘው በኋላ ምንዳውን ሊያስረክበው ከራሱ አገናኘው።

____

ምንጭ፦

ﺍﻹﺻﺎﺑﺔ

ﺍﻻﺳﺘﻌﻴﺎﺏ

ﺗﻬﺬﻳﺐ ﺍﺑﻦ ﻋﺴﺎﻛﺮ

ﺛﻤﺎﺭ ﺍﻟﻘﻠﻮﺏ

ﺣﻠﻴﺔ ﺍﻷﻭﻟﻴﺎﺀ

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group