UMMA TOKEN INVESTOR

ummu Fatima shared a
ترجمہ ممکن نہیں

ግን እስከ መቼ⁉️

============

(እስከ መቼ የንጹሐን ደም በጽንፈኞች እየፈሰሰ ይቀጥላል? እስከ መቼ ሰው በሰፈሩ በስጋት ይኖራል?)

||

✍ ሎሚ ሜዳ አካባቢ የሚገኘውን የዓሊ መስጅድ ጉዳይ መጅሊስ ይዞታል ስለተባለና ጉዳዩን ወደ ሚዲያ በማውጣት የበለጠ ልዩነት እንዳይሰፋና የጠላት መሳለቂያ እንዳንሆን በሚል በተደጋጋሚ ዝምታን መርጨ ነበር።

ግና የሰዎች እነዚህ ንጹሐን ሙስሊሞችን «ውሃብያ» የሚል ታፔላ ለጥፈው የሚያከፍሩና ደማቸውን ሐላል ያደረጉ የአሕባሽና በነርሱ የተጠለፉ የጥመት አንጃዎች፤ ከሙስሊሙ አንድነት ይልቅ ክፍፍሉን፣ ከከፍታው ይልቅ ዝቅታውን፣ ከጥንካሬው ይልቅ ድክመቱን፣ ከስልጣኔው ይልቅ ኋላ ቀርነቱን… የሚሹ ናቸውና ዛሬም እንደተለመደው ከጠሮ፣ በኒ፣ ከአንዋርና መሰል ከሚታወቁባቸው ሰፈሮች ተጠራርተው በየቦታው በመሄድ የተለመደውን የንጹሐን ደም ማፍሰስ አጠናክረው ቀጥለዋል።

ከአሁን በፊት በጠሮ፣ በፉል ውሃ ተውፊቅ፣ በፈላሕ መስጅድና በሌሎች መስጅዶች በሚያስነሷቸው ሁከቶች የሚታወቁት እነዚህ ስብስቦች፤ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የሁከት አቅጣጫው ወደ ሎሚ ሜዳው ዓሊ መስጅድ ላይ ሆኗል።

በዚህ መስጅድ ውስጥ ከበፊት ጀምሮ መስጅዱን የቆረቆሩና ሰፈሩን ያቋቋሙ የአካባቢው ሙስሊሞች ሳይቀሩ፤ የመስጂዱን ኮሚቴዎች፣ ሴቶቻቸውን ሳይቀር ከመስጅድ ባሻገር ጨለማን ተገን አድርገው መንገድ ላይ በመጠበቅና መኖሪያ ቤታቸው ድረስ በመሄድ ደማቸውን አፍሰዋል። በዛሬው ዕለትም ከጠዋት የመስጂዱን ምንጣፍ እየቀየሩ የነበሩ ሙስሊሞችን ከየቦታው ተጠራርተው መጥተው ደማቸውን አፍሰዋል፤ መስጂዱም በጸጥታ አካላት ተከቧል።

ነገር ግን ዛቻና ሁከታቸው አሁንም በአካባቢው ካለ የጸጥታ አካል በላይ ስለሆነ ተጨማሪ ኃይል ያስፈልጋል። በነዚህ አካላት ላይ ተገቢ የሆነ ተመጣጣኝ እርምጃ አለመወሰዱ፤ ሰፈሩ በየቀኑ የስጋትና የሁከት ማዕከል እንዲሆን አድርጎታል። የሚመለከተው የመንግስትና የመጅሊስ አካል ይህን ቡድን ለአንደና ለመጨረሻ ጊዜ እርምጃ እንዲወሰድበት በማድረግ የአካባቢውን ሰላም ወደነበረበት ሊመልስ ይገባል።

በየአካባቢው ካሉ ተላላኪዎቻቸው ጋር በመሆን ሁከት በተነሳበት ቦታ ሁሉ አዝማች በመያዝ ነገሩን የሚያጋግሉት በጣት የሚቆጠሩና የሚታወቁ ወጣቶች ናቸው። እነዚህ ወጣቶች ሰንሰለታቸው ከማኅበሩ ሰዎችና ከታላላቅ የሃገሪቱ ጽንፈኛ ቡድኖች ጋር ነው። የዚህን ቡድን ሰንሰለት ከነ አጋሮቹ አፈላልጎ እርምጃ በመውሰድ የአካባቢውንና አጠቃላይ የህዝበ ሙስሊሙን ሰላም ማስጠበቅ የመንግስት ኃላፊነት ነው።

በሆነ ባልሆነው የሙስሊሞችን ደም ማፍሰስ ይቁም። በፊት ከነበረው ስርዓት ጋር አብረው ያፈሰሱት ደምና ያሰደዱት ሙስሊም አንሷቸው፤ ዛሬም በሌላ መልክ ተመሳሳይ በደል ሲፈፅሙብን ዝም ልንል አይገባም።

በቃን‼

ፍትሕ ለሎሚ ሜዳ ሙስሊሞች‼

Cc:

===

Addis Ababa Police

Ethiopian Federal Police

Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council

Mayor Office of Addis Ababa

Adanech Abiebie- አዳነች አቤቤ

||

t.me/MuradTadesse

x.com/MuradTadesse

ummalife.com/MuradTadesse

image
image
image
image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
ummu Fatima shared a
ترجمہ ممکن نہیں

ጥቂት ስለዚህ ዲዛይን‼

=================

✍ ይህ ከታች በምስሉ ላይ የምትመለከቱት ዲዛይን አፍሪካ ህብረት አካባቢ የተሰጠው የነጃሺ መስጅድና ኢስላማዊ ማዕከል ዲዛይን ነው። ከትናንት በፊት በወጣው የተወዳዳሪዎች ውጤት አሸናፊ የሆነው ዲዛይን ነው።

ብዙዎች «ኢስላማዊ ምልክት» የሌለው ነው፤ ከላይ ሲታይ ምንም ኢስላማዊ የሚመስል ምልክት የለውም ስትሉ ነበር፤ በውስጥም ያናገራችሁኝ ነበራችሁ።

የእኔ ሃሳብ፤ ለመሆኑ «ኢስላማዊ ምልክት» ማለት ምን ማለት ነው?

ሳንወሻሽ «ጨረቃና ኮከብ ምልክት» የለውመረ ለማለት ነው ኣ? በተጨማሪም የህንፃው ዲዛይን በወትሮው የምናውቀውን የመስጅድ ቅርፅ አይመስልም ለማለት ነው ኣ?

እንደዛ ከሆነ፤ በመስጅዶች ላይ ጨረቃና ኮከብን እንደ ምልክት መጠቀም በሸሪዓችን መሠረት የለውም። እንዳውም አንዳንዶች አላማውን አይተው ቢድዓህ ነው እስከማለት ደርሰዋል። ነገር ግን ከታለመለት በጎ አላማ አንፃር በዛ ደረጃ ላይደርስ ይችላል።

የተጀመረውና ኦፊሲያሊ ኢስላማዊ ምልክት የተደረገው ያኔ ኦቶማን ቱርኮች መለያቸውን መስቀል ካደረጉት የመስቀል ጦረኞች ለመለየት ብለው ነው። ሰንሰለቱም የAlexander the Great አባት Byzantiumን (ቆስጠንጣኒያን) ሲያጠቃ የተሸነፈበትን ምሽት ታሳቢ አድርገው ነው።

  (ዝርዝር ነገሮችን ከዚህ ኪታብ አንብቡ፦

"التراتيب الإدارية" للشيخ عبد الحي الكتاني رحمه الله (1 / 320) .

ኢብኑ ዑሠይሚንም አላህ ይዘንላቸውና፤ ይህን ጉዳይ ሙስሊሞች የሚያደርጉት እነርሱ "ቀይ መስቀል" ሲሉ እኛ "ቀይ ጨረቃ" ብለን ለመመሳሰል እና በተለያዩ ነገሮች ላይ ምልክቱን ስለሚጠቀሙት እኛም በራሳችን ለመጠቀም ከሆነ አይፈቀድም ብለዋል።

وقال الشيخ ابن عثيمين رحمه الله :

" وضع الأهلة على المنائر قيل : إن بعض المسلمين الذين قلدوا غيرهم فيما يصنعونه على معابدهم ، وضعوا الهلال بإزاء وضع النصارى الصليب على معابدهم ، كما سموا دور الإسعافات للمرضى ( الهلال الأحمر ) بإزاء تسمية النصارى لها بـ ( الصليب الأحمر ) وعلى هذا فلا ينبغي وضع الأهلة على رؤوس المنارات من أجل هذه الشبهة ، ومن أجل ما فيها من إضاعة المال والوقت " انتهى .

"مجموع فتاوى ورسائل ابن عثيمين" (13 / 941)

√ በአጭሩ፦ ጨረቃና ኮከብን የምንጠቀመው የአላህን ታዕምር ገላጭ ከሆኑ ፍጡሮቹ መካከል ስለሆኑ ከምልክት አንፃር እንጂ የሚመለኩ ስለሆኑ ወይንም የተለዬ ነገር ስላላቸው አይደለም።

ከዚያ ወዲህ በብዙው ሙስሊም ዘንድ ስለተለመዱ ብቻ ጨረቃና ኮከብ ምልክት ሲቀር፤ ኢስላማዊ ምልክት የለውም ወደማለት ደረጃ መሄድ የለብንም።

ነገር ግን ይህ ዲዛይን የተመረጠው የእውነት እነዚህ ምልክቶች በሸሪዓው መሠረት የላቸው ተብሎ ነው ወይንስ አፍሪካ ህብረት አካባቢ ስለሆነ በኢስላማዊ ምልክትነት የተለመደ ነገር እንዳይቀመጥ ጫና ተደርጎ የሚለውን አላህ ይወቅ።

ያ ካልሆነ ግን አሁን ያለው ዲዛይን የሌላ እምነት ወይም ፈሳድ ነገር መታወቂያ የሆነ ነገር እስካልታየበት ድረስ፤ በአጠቃላይ ከሸሪዓው ጋር የሚጋጭ ምልክት እስከሌለው ድረስ፤ የተለመደው ጨረቃና ኮከብ ስለሌለው ብቻ ዲዛይኑን ኢስላማዊ ፋና የለውም ብሎ ማጣጣልና መተቸት ተገቢ አይደለም።

አላህ የበለጠውን ያውቃል።

||

t.me/MuradTadesse

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
ummu Fatima shared a
ترجمہ ممکن نہیں

❗Очередная бойня в Газе

Израильская оккупация совершила очередное ужасное преступление против палестинцев. В результате авиаударов по лагерю беженцев Нусейрат было убито 20 человек, в том числе и дети.

@as_sahwa

2 views
Send as a message
Share on my page
Share in the group
ummu Fatima shared a
ترجمہ ممکن نہیں

በህመሙ ወቅት አላህን የሚያስታውስ ትውልድ ለጠላት የሚበገር ይመስልሀልን?! ከላ ወሐሻ ወላህ!

ጉዳት ደርሶበት አናቱ በፋሻ ተጠቅልሎ ወደ ሆስፒታል እየተወሰደ ሰላቱን አስታውሶ በተቀመጠበት ሐረመ። አላሁ አክበር አለ።

በሰላት ውስጥ ስክነት እንዳለ ያውቃል። ችግር ሁሉ አላህን ካላስረሳ ጀለል ነው። ጀለል ማለት ተራና ቀላል ማለት አይደለምን?! አዎ ምስሉም ስለርሱ ነው የሚናገረው።

Mahi mahisho

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
ummu Fatima shared a
ترجمہ ممکن نہیں

🚨 ኢትዮጵያ ከባድ አደጋ ተጋርጦባታል!

የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የበላይ ጠባቂ አባቶች መግለጫ አውጥተዋል።

መግለጫቸው ፤ በአውሮፓ ኅብረት እና በአፍሪካ፣ በካሪቢያንና በፓስፊክ ሀገራት መካከል የተፈረመውንና የሳሞአ ስምምነት በመባል የሚታወቀውን የንግድና የኢኮኖሚ አጋርነት ስምምነት የተመለከተ ነው።

ጉባኤው ስምምነቱ ተካተውበታል ያላቸውን ጎጂ ሀሳቦች በዝርዝር አስፍሯል።

ከነዚህም መካከል ፦

- በስምምነቱ አንቀፅ 36.2 ላይ የተጠቀሰው የወሲብና የተዋልዶ ጤናና መብቶች" ("Sexual and Reproductive Health and Rights") የሚለው ሐረግ በቀጥታ ፦

* #ከግብረሰዶም መብቶች፤

* ከፆታ መቀየር፤

* ከውርጃ፤

* ሁሉን አቀፍ የወሲብ ትምህርትና ግልሙትናን ሕጋዊ ከማድረግ በቀጥታ የተያያዘ መሆኑ በአውሮፓ ፓርላማና በዓለም የጤና ድርጅት የመረጃ ምንጮች ላይ በግልፅ መቀመጡ፤

- በስምምነቱ የአፍሪካ ፕሮቶኮል አንቀፅ 40.6 ላይ በአህጉሪቱ ለሚገኙ ልጆችና ታዳጊዎች ሁሉን አቀፍ የወሲብ ትምህርት (Comprehensive Sexuality Education) የተባለ እጅግ አደገኛ ኢግብረገባዊና ልቅ የወሲብ ትምህርት እንዲማሩ አስገዳጅ መሆኑ ለዚህም በዩኔስኮ የተዘጋጀውና እጅግ አደገኛ ይዘት እንዳለው የተረጋገጠው መተግበርያ "International Technical Guidance on Sexuality Education” በስም ተጠቅሶ መቀመጡ፤

- የፆታ ትንኮሳን (gender based violence) ማስቀረት በሚል በጣም አሻሚ የሆነ ግብረሰዶማዊ አስተሳሰቦችን ለማስረፅ እንዲረዳው በሰነዱ በበርካታ ክፍሎች ውስጥ " አካታች " (inclusive) በሚሉ ቃላት ተሸፍኖ እንዲገባ የተደረገ መሆኑ፤

- በበርካታ ሥፍራዎች የተጠቀሰው "Gender" የሚለው ቃል ወንድና ሴት ተብሎ እንደሚተረጎም በስምምነቱ በግልጽ ባለመቀመጡ ይልቁንም በርካታ ጾታዎች እንዳሉ በማስመሰል ሀገራትን የሚያደናግሩባቸው እንደ (sexual orientation እና gender identity)ን የመሳስሉ ግብረሰዶማዊ አስተሳሰቦችን የያዙ ዶክመንቶች በስም ተጠቅሰው በስምምነቱ ውስጥ መካተታቸው፤

- ስምምነቱ የወላጆችን መብት የሚጥስና የኢትዮጵያዊ ቤተሰብ እሴቶችን አደጋ ላይ የሚጥሉ አንቀፆችን የያዘ ስለመሆኑ በሰነዱ ላይ ከተደረገ የኤክስፐርቶች ጥልቅ ጥናት ተረድተናል... የሚሉት ይገኙበታል።

ጉባኤው በነዚህ እና ሌሎች ጎጂ ምክንያቶች ፦

➡ መንግስት የሳሞአ የንግድና የኢኮኖሚ የአጋርነት ስምምነትን በርካታ ጎጂ ጎኖች እንዳሉት በማመን ከዚህ ስምምነት #ኢትዮጵያ ራሷን እንድታገልል በማድረግ መንግስታዊ ኃላፊነቱንና አደራውን በተግባር እንዲወጣ በአጽንኦት ጠይቋል።

➡ የኢፌዲሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና በሥሩ ያሉ የሚመለከታቸው ቋሚ ኮሚቴዎች የስምምነት ሰነዱ ውስጥ በዝርዝር የቀረቡትን በተለይም ፦

° ከሰብኣዊ መብቶች፣

° ከወሲባዊና የተዋልዶ ጤናና መብቶች፣

° ሁሉን አቀፍ የወሲብ ትምህርት፤

° አካታችነት እና መሰል በሰነዱ የተካተቱ አንቀጾች ወይም ይዘቶች ከግብረሰዶማዊነትና ጾታን ከመቀየር እንዲሁም ከልቅ ወሲብና ከውርጃ ጋራ በቀጥታ ተያያዥነት ያላቸው ጽንስ ሃሳቦች መሆናቸውን በመረዳት ይህንን እጅግ አደገኛ ስምምነት ባለማጽደቅ ህዝባዊና ታሪካዊ አደራውን እንዲወጣ በአጽንኦት ጠይቋል።

በሙስሊሙ ዓለም የተፈጠሩ ሁሉንም አዳዲስ መረጃዎች በተለይም በወቅታዊ የፍልስጤም ጉዳይ እውነተኛ እና ሚዛናዊ መረጃ ለማግኘት የሙሐመድ ትውልድ ገፅን ፎሎው ያድርጉ

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group