አቡ አሊ Profile Picture
UMMA TOKEN INVESTOR

Qumuqta qilghuchi yo'q.

Copy

የጥንቃቄ መረጃ ‼

በአዲስ አበባ ሌቦች ሊሰርቋቹ ሲያስቡ ከሚጠቀሙት ዘዴዎች መካከል:—

✔ሞተር እና ሳይክል ወደ እርሶ ሲጠጋ ይጠንቀቁ ስንቱ ስልኩን ተበልቷልና።

✔የማያውቆት ሰው ፀያፍ ስድብ ይሰድቦታል። ለመጣላት ሲጋበዙ ገላጋይ መስለው የተሳዳቢው ተባባሪ ሌቦች ኪሶትን ያጥቦታል።

✔ ታክሲ ውስጥ ሆን ብለው የታመመ ወይም ነፍሰ ጡር የሚመስል ሰው አስቀምጠው መስኮት እንዲከፍቱ በጥድፊያ ይጠይቆታል ። እርሶም መስኮቱን ሲከፍቱ ወይም ቦታ ለመቀየር ሲያስቡ ኪሶት ይገባሉ።

✔ የታክሲ ረዳት በመመስል "የት ኖት " ብለው በሚያልፉበት መንገድ ይጠይቆታል። እርሶ ወደጠሩት ቦታ እንደሚሄዱ በማስመሰል ታክሲ ካስገቦት በኋላ ዘርፈው ደብድበው ያወርዶታል።

✔ አውቀው በታክሲ ትርፍ እንዲጫኑ ካደረጉ በኋላ " ትራፊክ መጣ፣ውረድ ፣ውረጂ " በማለት አዋክበው አውርደው በመሀል ገንዘቦትን ወይም ሞባይል ስልኮትን ይሰርቆታል።

✔ አሁን አሁንማ ማር ፣ቅቤ ተልኮለት ነው በማለት እቤት ሰተት ብለው ገብተው የላከኝን ሰው ልንገረው ስልኮትን አውሱኝ በማለት ያልተሰማቸው በማስመሰል ሹልክ ብለው ያመልጣሉ።

✔ መንገድ ላይ አጣዳፊ ካልሆነ ስልክ ባያወሩ ይመረጣል። መንታፊው በዝቷልና።

✔ ሎተሪ ደረሰኝ ብሎ ወይም የማያውቁት ሰው መንገድ ላይ እያወሮት ሲሄድ ይጠንቀቁ።

Send as a message
Share on my page
Share in the group