#የበጐ #ተግባራት #መንገዶች #በርካታ #ስለመሆናቸው
#ክፍል_10
#ሐዲሥ 13 / 126
አቡ ሁረይራ እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕክተኛ፦ \"አንድ ሰው በጉዞ ላይ እያለ ጥም ያቃጥለዋል። የውሃ ጉድጓድ አገኘና ከውስጡ ገብቶ ጠጣ። ከጉድጓድ ሲወጣ የሚያለከልክ ውሻ ተመለከተ። ከደረሰበት የውሃ ጥም ብርታት የተነሳ እርጥብ አፈር ይልሳል። \"እኔን ያጋጠመኝ ዓይነት የውሃ ጥም ይህንንም ውሻ አጋጥሞታል\" በማለት አሰበ። ወደ ጉድጓዱ በመውረድ ጫማውን ውሃ ሞላው። በአፉ ይዞ ወደ ላይ ዘለቀ። ለውሻውም አጠጣው። አላህ ይህን ጽድቅ ተግባሩን ተቀበለው። ምሕረትንም አደረገለት\" በማለት ተናገሩ። \"የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! ለእንስሳት ጽድቅ በመፈጸም ምንዳ እናገኛለን ?\" ሲሉ ጠየቋቸው። \"እርጥብ በሆነች (በሕያውያን) ሆድ ሁሉ ምንዳ ይገኛል\" በማለት መለሱ። (ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል)
በቡኻሪና ዘገባ ላይ፦ \"አላህ መልካም አድራጐቱን ተቀበለለት። ምሕረት አደረገለት። ጀንነትም አስገባው\" የሚል ተወስቷል።
በሌላ የቡኻሪና ሙስሊም ዘገባ ላይ ደግሞ፦ \"ውሻው ጥም ሊገለው ቀረበ። ጉድጓዱን በመዞር ላይ እያለ ከበኒ ኢስራኢል ሴተኛ አዳሪዎች አንዷ ተመለከተችው። ጫማውን አውልቃ ውሃ በመቅዳት ለውሻው አጠጣችው። ምሕረት ተደረላት\" የሚል ተወስቷል።
ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች
1/ ሕይወት ላላቸው ነገሮች በጐ የመዋል ጠቀሜታ። የአላህን ምንዳ ከሚያስገኙና ምሕረቱንም ለመጐናጸፍ ከሚያስችሉ መልካም ተግባራት ውስጥ የሚካተት ነው።
2/ ውሃን የማጠጣት ትሩፋት፤ በተለይም ከራስና ከቤተሰብ መሠረት ፍላጐቶች የተረፈ ሆኖ ከተገኘ ለሚፈልጉት ፍጡራን መስጠት ግዴታ ይሆናል። ወደ አላህ ለመቃረብ ከሚያስችሉ ተግባራትም አንዱ ነው።
3/ የአላህ እዝነት (ረሕመት) በአነስተኛ ተግባር ታላቅ ወንጀልን ይምራል።
Umma Life
https://ummalife.com/MuslimEthio
ቴሌግራም/ telegram/
https://t.me/ethiomuslim_1
አቡ ሁረይራ እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕክተኛ፦ "አንድ ሰው በጉዞ ላይ እያለ ጥም ያቃጥለዋል። የውሃ ጉድጓድ አገኘና ከውስጡ ገብቶ ጠጣ። ከጉድጓድ ሲወጣ የሚያለከልክ ውሻ ተመለከተ። ከደረሰበት የውሃ ጥም ብርታት የተነሳ እርጥብ አፈር ይልሳል። "እኔን ያጋጠመኝ ዓይነት የውሃ ጥም ይህንንም ውሻ አጋጥሞታል" በማለት አሰበ። ወደ ጉድጓዱ በመውረድ ጫማውን ውሃ ሞላው። በአፉ ይዞ ወደ ላይ ዘለቀ። ለውሻውም አጠጣው። አላህ ይህን ጽድቅ ተግባሩን ተቀበለው። ምሕረትንም አደረገለት" በማለት ተናገሩ። "የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! ለእንስሳት ጽድቅ በመፈጸም ምንዳ እናገኛለን ?" ሲሉ ጠየቋቸው። "እርጥብ በሆነች (በሕያውያን) ሆድ ሁሉ ምንዳ ይገኛል" በማለት መለሱ። (ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል)
በቡኻሪና ዘገባ ላይ፦ "አላህ መልካም አድራጐቱን ተቀበለለት። ምሕረት አደረገለት። ጀንነትም አስገባው" የሚል ተወስቷል።
በሌላ የቡኻሪና ሙስሊም ዘገባ ላይ ደግሞ፦ "ውሻው ጥም ሊገለው ቀረበ። ጉድጓዱን በመዞር ላይ እያለ ከበኒ ኢስራኢል ሴተኛ አዳሪዎች አንዷ ተመለከተችው። ጫማውን አውልቃ ውሃ በመቅዳት ለውሻው አጠጣችው። ምሕረት ተደረላት" የሚል ተወስቷል።
ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች
1/ ሕይወት ላላቸው ነገሮች በጐ የመዋል ጠቀሜታ። የአላህን ምንዳ ከሚያስገኙና ምሕረቱንም ለመጐናጸፍ ከሚያስችሉ መልካም ተግባራት ውስጥ የሚካተት ነው።
2/ ውሃን የማጠጣት ትሩፋት፤ በተለይም ከራስና ከቤተሰብ መሠረት ፍላጐቶች የተረፈ ሆኖ ከተገኘ ለሚፈልጉት ፍጡራን መስጠት ግዴታ ይሆናል። ወደ አላህ ለመቃረብ ከሚያስችሉ ተግባራትም አንዱ ነው።
3/ የአላህ እዝነት (ረሕመት) በአነስተኛ ተግባር ታላቅ ወንጀልን ይምራል።
Umma Life
ቴሌግራም/ telegram/