UMMA TOKEN INVESTOR

1 week Translate
Translation is not possible.

#አንድን_ግለሰብ_ለይቶ #ወይም #እንስሳን_መርገም_ስለመከልከሉ

#ክፍል_6

#ሐዲሥ 264 / 1556

አቡ ደርዳእ እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕክተኛ እንዲህ ብለዋል፦ "አንድ ሰው አንድን ነገር በሚረግም ጊዜ እርግማኑን ወደ ሰማይ ትወጣለች። የሰማይ በሮች ይዘጉባታል። ወደ ምድር ትወርዳለች። የምድር በሮች ይዘጉባታል። ከዚያም ቀኝና ግራ ትዞርና መግቢያ ካላገኘች ወደ ተረገመው አካል ትመለሳለች። ለእርግማኑ ተገቢ ሆኖ ካገኘችው ታርፍበታለች። ካለበለዚያ ወደ ረጋሚው ትመለሳለች።" (አቡ ዳውድ)

ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች

1/ እርግማን ጥንቃቄ የሚሻ ነገር ነው። ምክንያቱም የምንረግመው ሰው ለእርግማኑ ተገቢ ያልሆነ ከሆነ እርግማኑ ረጋሚውን ራሱን መልሶ ይጎዳዋል።

2/ ስለዚህም አንድን ሰው ለይቶ መርገም አደጋ እንዳለው ዓሊሞች ይናገራሉ።

3/ መርገም ካለብን ባሕሪን ወይም ሙስሊም ያልሆኑ ወገኖችን በግል ሳይሆን በጥቅሉ መሆን ይኖርበታል። ለምሳሌ፦ "ዋሾዎች የአላህ እርግማን ይውረድባቸው። በከሐዲያን ላይ የአላህ እርግማን ይውረድ" ማለት ይቻላል። አንድን ሰው ለይቶ ግን፦ "እገሌ እንዲህ ይሁን" በማለት መርገም በራስ ላይ በላእ ሊያመጣ ይችላል።

Umma Life

https://ummalife.com/MuslimEthio

ቴሌግራም/ telegram/

https://t.me/ethiomuslim_1

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
1 week Translate - Youtube
Translation is not possible.
1 view
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

★ ★ ★ #በፈታኝ_ሁኔታዎች_ውስጥ #የሚፈጸም_አምልኮ #የሚያስገኘው_ትሩፋት★ ★ ★

#ሐዲሥ 23 / 1366

መዕቂል ኢብኑ የሳር (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦ “በፈታኝ ሁኔታዎች ውስጥ የሚፈጸም አምልኮ ወደኔ የመሰደድ ያህል ነው።” (ሙስሊም)

★ ★ ★ ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች ★ ★ ★

★ ፈታኝ ሁኔታዎች ማለት ሰዎች በማይረጋጉበት፣ ፈተና በበዛበት፣ ነገሮች በተደባለቁበት ወቅት ማለት ነው።

★ በእንዲህ ዓይነት ወቅት ሰዎች ሲዘናጉና ሲርቁ አላህን ጸንቶ ማምለክ ትልቅ ዋጋ አለው።

★ «ወደኔ የተሰደደ ያህል ነው» የሚለው ወደ መዲና መሰደድ ግዴታ በሆነበት ጊዜ መሰደዱ የላቀ ምንዳ ስለሚያስገኝ ያን የሚመጥን ምንዳ እንደሚያገኝ ለመጦቆም ነው።

★ ስደት ሁለት ዓይነት እንደሆነ የነቢዩ ﷺ ሐዲሥ ያመለክታል። አንደኛ ስደት ከቦታ ቦታ መንቀሳቀስ ሲሆን፥ ከመካ ወደ መዲና ፣ ከኩፍር ሀገር ወደ ኢስላም ሀገር በአካል መሰደድ ነው። ሁለተኛው የስደት ትርጉም አላህ ከከለከለው ሐራም ነገር መታቀብ ነው። ስለዚህም በዙሪያው ያሉ ፈተናዎችን ተቋቁሞ ራሱን ከሐራም ነገር በመጠበቅ አላህን ማምለኩን የቀጠለ ወደ አላህ ተሰዷል።

Umma Life

https://ummalife.com/MuslimEthio

ቴሌግራም/ telegram/

https://t.me/ethiomuslim_1

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group