#ትዕግሥት (#ሶብር)
#ክፍል_11
#ሐዲሥ 3 / 35
ዐጧእ ኢብኑ ረባሕ (ረ.ዐ) እንዲህ ሲሉ አስተላልፈዋል፦ ኢብኑ ዐብባስ (ረ.ዐ) “ከጀንነት ሰዎች አንዷን ላመላክትህን?” አሉኝ። “አዎ!” አልኳቸው። “ይህች ጥቁር ሴት ናት። ከነቢዩ (ሶ.ዐ.ወ) ዘንድ በመምጣት፡ “እኔ, አውድቅ በሽታ አለብኝ፤ (ህመሙ ሲነሳብኝ) እራቆታለሁ። (ከበሽታዬ እፈወስ ዘንድ) አላህን ይመጸኑልኝ” በማለት ነቢዩን (ሶ.ዐ.ወ) ጠየቀች። “ከፈለግሽ ትዕግሥት (ሶብር) አድርጊና ጀንነት ይሰጥሻል። ከፈለግሽ ደግሞ ይፈውስሽ ዘንድ አላህን እለምንልሻለሁ” አሏት። “ትዕግሥት አደርጋለሁ” አለች፤ ከዚያም፦ “ስለምራቆት እንዳልራቆት አላህን ይማጸኑልኝ“ ስትል ጠየቀች። ዱዓ አደረጉላት።” (ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል)
ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች
1/ ዱንያ ውስጥ ለሚደርስ ስቅይና መከራ ትዕግሥት (ሶብር) ማድረግ ጀንነትን ለመጎናፀፍ ያበቃል።
2/ አላህን በመማጸን በሽታን ማስወገድ -ህክምና ከማድረግ ጋራ- ተገቢ ነው።
3/ አቅሙና ችሎታው እስካለ ድረስ ልዩ ፈቃዶችን (ሩኽህ) ከመጠቀም ይልቅ ራስን የላቀ ምንዳ ከሚያስገኙ ጠበቅ ያሉ ሕግጋት (ዐዚመህ) ጋር ማላመዱ በላጭነት አለው።
Umma Life
https://ummalife.com/MuslimEthio
ቴሌግራም/ telegram/
https://t.me/ethiomuslim_1
#ትዕግሥት (#ሶብር)
#ክፍል_11
#ሐዲሥ 3 / 35
ዐጧእ ኢብኑ ረባሕ (ረ.ዐ) እንዲህ ሲሉ አስተላልፈዋል፦ ኢብኑ ዐብባስ (ረ.ዐ) “ከጀንነት ሰዎች አንዷን ላመላክትህን?” አሉኝ። “አዎ!” አልኳቸው። “ይህች ጥቁር ሴት ናት። ከነቢዩ (ሶ.ዐ.ወ) ዘንድ በመምጣት፡ “እኔ, አውድቅ በሽታ አለብኝ፤ (ህመሙ ሲነሳብኝ) እራቆታለሁ። (ከበሽታዬ እፈወስ ዘንድ) አላህን ይመጸኑልኝ” በማለት ነቢዩን (ሶ.ዐ.ወ) ጠየቀች። “ከፈለግሽ ትዕግሥት (ሶብር) አድርጊና ጀንነት ይሰጥሻል። ከፈለግሽ ደግሞ ይፈውስሽ ዘንድ አላህን እለምንልሻለሁ” አሏት። “ትዕግሥት አደርጋለሁ” አለች፤ ከዚያም፦ “ስለምራቆት እንዳልራቆት አላህን ይማጸኑልኝ“ ስትል ጠየቀች። ዱዓ አደረጉላት።” (ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል)
ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች
1/ ዱንያ ውስጥ ለሚደርስ ስቅይና መከራ ትዕግሥት (ሶብር) ማድረግ ጀንነትን ለመጎናፀፍ ያበቃል።
2/ አላህን በመማጸን በሽታን ማስወገድ -ህክምና ከማድረግ ጋራ- ተገቢ ነው።
3/ አቅሙና ችሎታው እስካለ ድረስ ልዩ ፈቃዶችን (ሩኽህ) ከመጠቀም ይልቅ ራስን የላቀ ምንዳ ከሚያስገኙ ጠበቅ ያሉ ሕግጋት (ዐዚመህ) ጋር ማላመዱ በላጭነት አለው።
Umma Life
https://ummalife.com/MuslimEthio
ቴሌግራም/ telegram/
https://t.me/ethiomuslim_1