UMMA TOKEN INVESTOR

1 week Translate
Translation is not possible.
#አላህን_መፍራት
ክፍል_2
አላህ እንዲህ ብሏል፦
"አላህም ነፍሱን (ቁጣውን) ያስጠነቅቃችኋል።" (አል_ዒምራን፡ 28)
#ሐዲሥ 50/398
ኢብኑ መስዑድ (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕክተኛ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦ "ጀሀነም በመጭው ዓለም ሰባ ሺህ ልጓም ያላት ሆናና እያንዳንዱን ልጓም ሰባ ሺህ መላኢክት ይዞት፥ እየተጎተተች ትቀርባለች፡፡" (ሙስሊም ዘግበውታል)
ከሐዲሡ የምንማረው ቁምነገር
፨ ገለጻው እውነተኛ ሊሆን ይችላል፡፡ የጀሀነምን ታላቅነትና አስፈሪነት ለመግለጽ የቀረበ ምሳሌያዊ አነጋገር ሊሆንም ይችላል። ዞሮ ዞሮ የተፈለገው የሰው ልጅ በመጭው ዓለም የሚጠብቀው እጣ ፈንታ ሊያስፈራው እንደሚገባ ማስታወስ ነው።
Umma Life
https://ummalife.com/MuslimEthio
ቴሌግራም/ telegram/
https://t.me/ethiomuslim_1
image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
1 week Translate
Translation is not possible.
#አላህን_መፍራት
#ክፍል_1
አላህ እንዲህ ብሏል፦
(وَإِيَّـٰىَ فَٱرْهَبُونِ ﴿٤٠﴾)
"እኔንም ብቻ ፍሩ።" (አል_በቀራህ፡ 40)
#ሐዲሥ 50 / 397
የእውነተኞች ሁሉ እውነተኛ የሆኑት የአላህ መልዕክተኛ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ ሲሉ ነግረውናል በማለት ኢብኑ መስዑድ (ረ.ዐ) አስተላልፈዋል ፦ "ከእናንተ አንዳችሁ የሚፈጠርበት ነገር ከእናቱ ሆድ ውስጥ ለአርባ ቀናት (የዘር) ፈሳሽ ሆኖ ይቆያል። ከዚያም ለተመሳሳይ ጊዜ የረጋ ደም ይሆናል። ከዚያም ለተመሳሳይ ጊዜ የተላመጠ ሥጋ ይሆናል። ከዚያም መላኢካ ተልኮ ነፍስ ይዘራበታል። (መላኢካ) አራት ነገሮች ይታዘዛል። ሲሳዩን፣ የሚሞትበትን ወቅት፣ ሥራውንና እድለቢስ (ሸቂይ) ወይም እድለኛ (ሰዒድ) መሆኑን (እንዲጽፍ)። ከርሱ ውጭ ሌላ አምላክ በሌላው (አምላክ) እምላለሁ! ከእናንተ አንዳችሁ በርሱና በጀነት መካከል አንድ ክንድ ያክል ርቀት እስኪቀረው ድረስ የጀነት ሰዎችን ሥራ ሲሠራ ይቆያል። (ትንሽ ሲቀረው) የተጻፈበት ይቀድመውና የእሳት ሰዎችን ሥራ በመሥራት እሳት ይገባል። ከእናንተ አንዳችሁ የእሳት ሰዎችን ሥራ ሲሠራ ይቆይና (ሊገባበት) አንዲት ክንድ ሲቀረው የተጻፈው ቀድሞት የጀነት ሰዎችን ሥራ በመሥራት ጀነት ይገባል።" (ቡኻሪና ሙስሊም)
ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች
1/ በቀዷ ቀደር _መልካምም ሆነ ክፉ_ ሁሉም ነገር ከአላህ እንደሆነ ማመን ያሻል።
2/ ሐዲሡ ወደ መልካም ሥራ ሰዎች እንዲሽቀዳደሙና በርሱው እንዲዘወትሩ ያነሳሳል።
3/ የሰዎች ስኬታማነት የሚለካው በፍጻሜያቸው ነው። እናም በተሠሩት መልካም ሥራ መኮፈስ መዝናናት የሚቻልበት ሁኔታ የለም።
4/ አንድ መልካም ሥራ የሠራ ሰው ንጹሕ እንደሆነ ሊያቆየው ይገባል። በክፉ ሥራ ሊበክለው አይገባም።
5/ ሁሌም በአላህ መታገዝ፣ ፍጻሜ እንዲያምር አላህን መጠየቅ፥ ክፉ ፍጻሜን መፍራትና ከርሱ በአላህ መጠበቅ ያስፈልጋል።
Umma Life
https://ummalife.com/MuslimEthio
ቴሌግራም/ telegram/
https://t.me/ethiomuslim_1
image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
1 week Translate
Translation is not possible.
#የሰዎችን #ውጫዊ #እንቅስቃሴና #ተግባር (#አምኖ) #መቀበልና #ውስጣቸውን #ለአላህ #መተው
#ክፍል_6
#ሐዲሥ 49 / 396
ዑመር ኢብኑል ኸጧብ (ረ.ዐ) ተከታዩን ሲናገሩ አድምጫለሁ በማለት ዐብደላህ ኢብኑ ዑትባህ ኢብኑ መስዑድ (ረ.ዐ)፥ አስተላልፈዋል፦ “በነቢዩ (ﷺ) የሕይወት ዘመን የሰዎች (እውነተኛ) ማንነት በራዕይ (ወሕይ) ይገለጽ ነበር። ራዕዩ (ወሕዩ) ተቋርጧል። ስለዚህም አሁን ማንነታችሁን የምንወስነው በገሃድ በምናየው ሥራችሁ ነው። መልካም (ባሕሪና ተግባር) ያሳየንን እናምነዋለን። እናቀርበዋለን። ውስጡን የመፈተሽ መብት አልተሰጠንም። ውስጡን አላህ ይፈትሸዋል። ክፉ (ባሕሪና ተግባር) ያሳየንን ደግሞ አናምነውም። እውነት ብለን አንቀበለውም። ውስጡ መልካም እንደሆነ ቢናገረም። (ቡኻሪ ዘግበውታል)
ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች
1/ ሰዎችን በግልጽ ከሚያሳዩት ባሕሪና ሥራ አንጻር ብቻ እስልምናቸውን መቀበል ግድ ነው። ውስጥን መፈተሽ የሰዎች መብት አይደለም።
2/ መልካም ኒይያ (ልበ-ውሳኔ) ከሸሪዓዊ ቅጣት አያድንም።
Umma Life
https://ummalife.com/MuslimEthio
ቴሌግራም/ telegram/
https://t.me/ethiomuslim_1
image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
1 week Translate
Translation is not possible.
#የሰዎችን #ውጫዊ #እንቅስቃሴና #ተግባር (#አምኖ) #መቀበልና #ውስጣቸውን #ለአላህ #መተው
#ክፍል_5
#ሐዲሥ 49 / 395
ጁንዱብ ኢብኑ ዐብደላህ (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት፥ የአላህ መልዕክተኛ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) አንድ የሙስሊሞች ጦር ወደ አጋሪዎች አዘመቱ። (ሁለቱ ኃይሎች) ተገናኙ። ከአጋሪዎች መካከልም ከሙስሊሞች አንዱን (በመግደል) ከፈለገ የሚገድል (አልሞ የማይስት) አንድ አጋሪ ነበር። ከሙስሊሞች መካከል አንዱ _ ኡሳማ ኢብኑ ዘይድ ነው ብለን እናስባለን_ ሰውየው እስኪዘናጋ ጠብቆ (ሊገድለው) ሰይፍ ሲያነሳ (አጋሪው)፦ “ላ ኢላሀ ኢልለላህ” አለ። ግና ገደለው። ብስራት (መልዕክት) ነጋሪው ወደ አላህ መልዕክተኛ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ዘንድ ቀረበ። ጠየቁት፡፡ የሆነውን ሁሉ ይነግራቸው ጀመር። የሰውየውን ሁኔታና ምን እንደ ፈፀመ ሲነግራቸው (ገዳዩን) ጠርተው “ለምን ገደልከው?” ሲሉ ጠየቁት፡፡ “የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! ሙስሊሞችን አወከ። እገሌን፥ እገሌን ገደለ” በማለት ስሞችን ዘረዘረላቸው። “ዘመትኩበት፡፡ ሰይፍ ሲያይ ላ ኢላሀ ኢልለላህ አለ” ሲልም (ምክንያቱን) ነገራቸው። የአላህ መልዕክተኛም፥ “ገደልከውን?” አሉት፡፡ “አዎ” አላቸው። “በዕለተ ትንሳኤ ላ ኢላሀ ኢልለላህ ስትመጣ ምን ልታደርጋት ነው?” አሉት፡፡ “የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! ምሕረት ይጠይቁልኝ” አላቸው። “በዕለተ ትንሳኤ ላ ኢላሀ ኢልለላህ ስትመጣ ምን ልታደርጋት ነው?” ከማለት ውጭ ያከሉት ነገር የለም። (ሙስሊም ዘግበውታል)
ከሐዲሡ የምንማረው ቁምነገር
፨ ይህና ከዚህ ቀደም የተወሳው ሐዲሥ የሚተርኩልን አንድ ዓይነት ክስተት እንደሆነ ዑለሞች ይናገራሉ። የትረካ ስልቱ የተለያየው ሐዲሡን ያስተላለፉት ግለሰቦች በመለያየታቸው ነው። ስለዚህ ለላይኛው ሐዲሥ የተዘረዘሩ አስተምህሮዎችን ይህም ሐዲሥ ያስተምራል።
Umma Life
https://ummalife.com/MuslimEthio
ቴሌግራም/ telegram/
https://t.me/ethiomuslim_1
image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
1 week Translate
Translation is not possible.
#የሰዎችን #ውጫዊ #እንቅስቃሴና #ተግባር (#አምኖ) #መቀበልና #ውስጣቸውን #ለአላህ #መተው
#ክፍል_4
#ሐዲሥ 49 / 394
ኡሳማ ኢብኑ ዘይድ (ረ.ዐ) ተከታዩን አስተላልፈዋል፦ የአላህ መልዕክተኛ (ﷺ) የጁሀይና ጐሣ አባል ወደ ሆነው ጁሀይና ወደ ተባለ ጦር አዘመቱን። ሰዎችን በጧት መጣንባቸው (ማልደን ዘመትንባቸው)። እኔና አንድ የአንሷር ሰው ከነርሱ ከሆነ አንድ ሰው ጋር (ፍልሚያ) ተገናኘን። ስንከበው “ከአላህ ውጭ ሌላ አምላክ የለም” አለ። የአንሷሩ ሰው እጁን ሰበሰበ። እኔ ግን በጦር ወግቼ ገደልኩት፡፡ መዲና ስንገባ ይህ (ድርጊቴ) ለነቢዩ (ﷺ) ተነገራቸው። “ኡሳማ ሆይ! ላ ኢላሀ ኢልለላህ ካለ በኋላ ገደልከውን?” አሉኝ። “የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! ያላት እኮ ከግድያችን ለመጠበቅ ነው” አልኳቸው። “ላ ኢላሀ ኢልለላህ ካለ በኋላ ገደልከውን?” አሉኝ በድጋሜ። ከዚያን ቀን በፊት ባልሰለምኩ ብዬ እስክመኝ ድረስ (ይህን ጥያቄ) ደጋገሙት፡፡ (ቡኻሪና ሙስሊም)
በሌላ ዘገባ ደግሞ የአላህ መልዕክተኛ (ﷺ)፦ “ላ ኢላሀ ኢልለላህ ካለ በኋላ ገደልከውን?” አሉኝ። “የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! ያላት ሰይፍ ፈርቶ ነው” አልኳቸው። “የተናገራት ከአንጀቱ ይሁን ከአንገቱ ልቡን ከፍተህ አይተኸዋልን?” አሉ። የሰለምኩት የዚያኑ ቀን በሆነ ብዬ እስክመኝ ድረስ (ይህን አባባል) ደጋገሙት፡፡
ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች
1/ አንድ ሰው መስለሙን ለመቀበል ግልጽ ቃል ወይም ተግባር ማየቱ በቂ ነው። ውስጥን መፈላፈል አግባብ አይደለም። ይህ ሸሪዓዊ ድንጋጌ “ውስጡ አልሰለመም ይሆናል” በሚል ሰበብ ብቀላ ለሚሹ ወገኖች መንገድ ለመዝጋት ነው።
2/ የአላህ መልዕክተኛ በኡሳማ ላይ የሞት ብይን (ቂሷስ) ያላስተላለፉት ነገሩ ግልጽ ስላልሆነለት (ሹብሃ ስለነበረበት) ነው። የሞት ቅጣት በእንዲህ ዓይነት ሹብሃዎች ይቀራል። ይሁንና የደም ካሳ (ዲያህ) አይቀርም።
3/ ታላቅ ወንጀል የሠራ “ከዚያ በፊት ባልሰለምኩ” ብሎ መመኘት አይፈቀድለትም። ኡሳማ ይህን ያለው _ የሚፈቀድ ሆኖ ሳይሆን _ ከነቢዩ ጠንካራ ውግዘት የተነሳ ልቡ በፍርሃት ስለራደና ስለተጨነቀ ነው።
Umma Life
https://ummalife.com/MuslimEthio
ቴሌግራም/ telegram/
https://t.me/ethiomuslim_1
image
Send as a message
Share on my page
Share in the group