#ራስን #መታገል (#ሙጃሃዳ)
#ክፍል_6
አላህ እንዲህ ብሏል፦
«ከገንዘብም የምትለግሱትን አላህ እርሱን ዐዋቂ ነው።» (አል-በቀራህ፦ 273)
#ሐዲሥ 11 / 100
አቡ ሁረይራ እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕክተኛ፦ \"ጠንካራ ሙእሚን ከደካማ ሙእሚን በላጭና ከአላህ ዘንድም ይበልጥ ተወዳጅ ነው። ሁሉም መልካም ቢሆኑም፣ የሚጠቅምህን ለመፈጸም ጉጉት ይኑርህ። በአላህ ታገዝ፤ አትስነፍ። አንዳች (ክፉ) ነገር ሲገጥምህ፦ \"ይህን፥ ይህን አድርጌ ቢሆን ኖሮ (ይህ ነገር አይደርስብኝም ነበር) አትበል። ይልቁንም \"አላህ ቀድሞውኑ ወስኗል፥ የሻውንም ፈጽሟል\" በል፤ (ቢሆን ኖሮ) የሰይጣንን ሥራ ትከፍታለችና\" ብለዋል። (ሙስሊም ዘግበታውል)
ከሐዲሥ የምንማራቸው ቁምነገሮች
1/ ኃያልነት ወይም ድክመት የሚለካው ከመልካም ተግባራት አንጻር ነው። ራስን ከማረምና ከመምራት፥ ከማስተካከልና ከመግራት አንጻር። የአላህን ፍላጎት ከመሙላትና ለሰዎች ጠቃሚ የሆነ ተግባራትን ከመፈጸም አንጻር።
2/ ሰዎች ክብራቸውን፣ ዲናቸውንና ሥነ ምግባራቸውን በመጠበቅ ለዱንያውም ለቀጣዩም ዓለም ጠቃሚ የሆነ ተግባራትን ለመከወን ሊነሱ ይገባል። ለእንዲህ ዓይነቱ በጎ ተግባርም የአላህ እርዳታና ድጋፍ ያሻቸዋል። አላህ እርዳታውን የለገሠው ያሰበውን ከግብ ያደርሳል።
3/ አንዳች ክፉ አጋጣሚ በሚደርስበት ወቅት ከቁጭትና ተጨማሪ ጥፋት የሚያድን ጥሩ ብልሃት ከዚህ ዘገባ ውስጥ ተጠቅሷል። ይኸውም የአላህን ፍላጎት በውዴታ በጸጋ መቀበል ነው። ያለፈን ነገር እያነሱ ከመቆጨትም መቆጠብ፥ ለሌላ ኪሳራ ያበቃልና።
Umma Life
https://ummalife.com/MuslimEthio
ቴሌግራም/ telegram/
https://t.me/ethiomuslim_1
#ራስን #መታገል (#ሙጃሃዳ)
#ክፍል_6
አላህ እንዲህ ብሏል፦
«ከገንዘብም የምትለግሱትን አላህ እርሱን ዐዋቂ ነው።» (አል-በቀራህ፦ 273)
#ሐዲሥ 11 / 100
አቡ ሁረይራ እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕክተኛ፦ \"ጠንካራ ሙእሚን ከደካማ ሙእሚን በላጭና ከአላህ ዘንድም ይበልጥ ተወዳጅ ነው። ሁሉም መልካም ቢሆኑም፣ የሚጠቅምህን ለመፈጸም ጉጉት ይኑርህ። በአላህ ታገዝ፤ አትስነፍ። አንዳች (ክፉ) ነገር ሲገጥምህ፦ \"ይህን፥ ይህን አድርጌ ቢሆን ኖሮ (ይህ ነገር አይደርስብኝም ነበር) አትበል። ይልቁንም \"አላህ ቀድሞውኑ ወስኗል፥ የሻውንም ፈጽሟል\" በል፤ (ቢሆን ኖሮ) የሰይጣንን ሥራ ትከፍታለችና\" ብለዋል። (ሙስሊም ዘግበታውል)
ከሐዲሥ የምንማራቸው ቁምነገሮች
1/ ኃያልነት ወይም ድክመት የሚለካው ከመልካም ተግባራት አንጻር ነው። ራስን ከማረምና ከመምራት፥ ከማስተካከልና ከመግራት አንጻር። የአላህን ፍላጎት ከመሙላትና ለሰዎች ጠቃሚ የሆነ ተግባራትን ከመፈጸም አንጻር።
2/ ሰዎች ክብራቸውን፣ ዲናቸውንና ሥነ ምግባራቸውን በመጠበቅ ለዱንያውም ለቀጣዩም ዓለም ጠቃሚ የሆነ ተግባራትን ለመከወን ሊነሱ ይገባል። ለእንዲህ ዓይነቱ በጎ ተግባርም የአላህ እርዳታና ድጋፍ ያሻቸዋል። አላህ እርዳታውን የለገሠው ያሰበውን ከግብ ያደርሳል።
3/ አንዳች ክፉ አጋጣሚ በሚደርስበት ወቅት ከቁጭትና ተጨማሪ ጥፋት የሚያድን ጥሩ ብልሃት ከዚህ ዘገባ ውስጥ ተጠቅሷል። ይኸውም የአላህን ፍላጎት በውዴታ በጸጋ መቀበል ነው። ያለፈን ነገር እያነሱ ከመቆጨትም መቆጠብ፥ ለሌላ ኪሳራ ያበቃልና።
Umma Life
https://ummalife.com/MuslimEthio
ቴሌግራም/ telegram/
https://t.me/ethiomuslim_1