UMMA TOKEN INVESTOR

Translation is not possible.

#ትዕግሥት (#ሶብር)

#ክፍል_14

#ሐዲሥ 3 / 38

ኢብኑ መስዑድ (ረ.ዐ) እንዲህ ሲሉ አስተላልፈዋል፦ -ከነቢዩ (ሶ.ዐ.ወ) ዘንድ ገባሁ፤ አሟቸው ነበር ልጠይቃቸው። “የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! ከፍተኛ የህመም ስሜት ይሰማዎታል?” አልኳቸው። “አዎ! ከናንተ ሁለት ሰዎች የሚሰማቸውን ያህል የህመም ስሜት ይሰማኛል” አሉ። “ይህ ማለት እርስዎ እጥፍ ምንዳ ያገኛሉ ማለት ይሆን? በማለት ጠየቅኳቸው። “አዎ! ነገሩ እንዲያ ነው። እሾህም ትሁን ከዚያ በላይ የሆነ አዋኪ ነገር የሚያገኘው አንድም ሙስሊም የለም፡ አላህ በርሷ (ሰበብ) ወንጀሉን ያበሰለት፤ ከዛፍ ላይ ቅጠል እንደሚረግፍ ሁሉ ኃጢአቱ የተራገፈለት ቢሆን እንጅ” በማለት ተናገሩ። (ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል)

ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች

1/ አንዳች ችግር በሚያጋጥም ወቅት ትዕግሥት ከታከለበት ምንዳ እንደሚያስገኝ።

2/ ከሰው ሁሉ ይበልጥ ፈተናና ችግር የሚደርስባቸው ነቢያት ናቸው። ምክንያቱም እነርሱ ከማንም የላቀ የትዕግስት ችሎታና ጽናት አላቸውና። አላህም ለሰው ዘር አርአያ አድርጓቸዋል።

Umma Life

https://ummalife.com/MuslimEthio

ቴሌግራም/ telegram/

https://t.me/ethiomuslim_1

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
1 day Translate
Translation is not possible.

#ትዕግሥት (#ሶብር)

#ክፍል_13

#ሐዲሥ 3 / 37

አቡ ሁረይራ (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት ነቢዩ (ሶ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል፦ “አንድን ሙስሊም አንድም ችግር ወይም በሽታ፡ ሐሳብ ወይም ቁጭት፡ የሚያውክ ነገር ወይም ጭንቀት አያገኘውም -በምትወጋው እሾህ እንኳ- አላህ በርሷ (ሰበብ) ወንጀሎችን ያበሰለት ቢሆን እንጅ!” (ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል)

ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች

1/ በሽታዎችና ሌሎችም ሙስሊምን የሚገጥሙት አዋኪ ነገሮች ወንጀሉን ያራግፉለታል።

2/ እውነተኛ ችግር ያልደረሰበት ሰው ማለት ምንዳን ያልተቸረ ሰው ነው።

Umma Life

https://ummalife.com/MuslimEthio

ቴሌግራም/ telegram/

https://t.me/ethiomuslim_1

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
3 day Translate
Translation is not possible.

#ትዕግሥት (#ሶብር)

#ክፍል_12

#ሐዲሥ 3 / 36

አቡ ዐብዱረሕማን ኢብኑ መስዑድ (ረ.ዐ) እንዲህ ሲሉ አስተላልፈዋል፦ ከነቢያት መካከል ሕዝቦች ደብድበውት አድምተውት፡ ደሙን ከፊቱ ላይ እየጠረገ፡ “አላህ ሆይ! ለሕዝቦቼ ምሕረት አውርድ፤ እነርሱ አያውቁምና” በማለት አላህን ይማጸን ስለነበር አንድ ነቢይ የአላህ መልዕክተኛ (ሶ.ዐ.ወ) የተረኩት አኳኋን ዘውትር ከዓይኔ አይጠፋም።” (ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል)

ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች

1/ የነቢያት (ሶ.ዐ.ወ) ትዕግሥትና ደዕዋቸውን ለሰዎች ለማድረሱ ሂደት ላይ ይደርስባቸው የነበረው ስቃይና ፈተና።

2/ አላዋቂነትን በትዕግሥትና በይቅር ባይነት ማስተናገድ ከነቢያት መልካም ሥነ-ምግባራት መካከል አንዱ ነው።

3/ ለአላዋቂዎች እኩይ ተግባር ተመሳሳይ ምላሽ አለመስጠት።

4/ የነቢዩን (ሶ.ዐ.ወ) የመልካም ሥነ-ምግባር አርአያነት መከተል። የኡሑድ ዕለት ግንባራቸውን ተመቱ። ደማቸው በፊታቸው ላይ ተንዠቀዠቀ። “አላህ ሆይ! ለሕዝቦቼ ምሕረት አውርድ፤ እነርሱ አያውቁምና” ከማለት ውጭ ሌላ ያከሉት አልነበረም።

Umma Life

https://ummalife.com/MuslimEthio

ቴሌግራም/ telegram/

https://t.me/ethiomuslim_1

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
4 day Translate
Translation is not possible.

#ትዕግሥት (#ሶብር)

#ክፍል_11

#ሐዲሥ 3 / 35

ዐጧእ ኢብኑ ረባሕ (ረ.ዐ) እንዲህ ሲሉ አስተላልፈዋል፦ ኢብኑ ዐብባስ (ረ.ዐ) “ከጀንነት ሰዎች አንዷን ላመላክትህን?” አሉኝ። “አዎ!” አልኳቸው። “ይህች ጥቁር ሴት ናት። ከነቢዩ (ሶ.ዐ.ወ) ዘንድ በመምጣት፡ “እኔ, አውድቅ በሽታ አለብኝ፤ (ህመሙ ሲነሳብኝ) እራቆታለሁ። (ከበሽታዬ እፈወስ ዘንድ) አላህን ይመጸኑልኝ” በማለት ነቢዩን (ሶ.ዐ.ወ) ጠየቀች። “ከፈለግሽ ትዕግሥት (ሶብር) አድርጊና ጀንነት ይሰጥሻል። ከፈለግሽ ደግሞ ይፈውስሽ ዘንድ አላህን እለምንልሻለሁ” አሏት። “ትዕግሥት አደርጋለሁ” አለች፤ ከዚያም፦ “ስለምራቆት እንዳልራቆት አላህን ይማጸኑልኝ“ ስትል ጠየቀች። ዱዓ አደረጉላት።” (ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል)

ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች

1/ ዱንያ ውስጥ ለሚደርስ ስቅይና መከራ ትዕግሥት (ሶብር) ማድረግ ጀንነትን ለመጎናፀፍ ያበቃል።

2/ አላህን በመማጸን በሽታን ማስወገድ -ህክምና ከማድረግ ጋራ- ተገቢ ነው።

3/ አቅሙና ችሎታው እስካለ ድረስ ልዩ ፈቃዶችን (ሩኽህ) ከመጠቀም ይልቅ ራስን የላቀ ምንዳ ከሚያስገኙ ጠበቅ ያሉ ሕግጋት (ዐዚመህ) ጋር ማላመዱ በላጭነት አለው።

Umma Life

https://ummalife.com/MuslimEthio

ቴሌግራም/ telegram/

https://t.me/ethiomuslim_1

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
5 days Translate
Translation is not possible.

#ትዕግሥት (#ሶብር)

#ክፍል_10

#ሐዲሥ 3 / 34

የአላህ መልዕክተኛ (ሶ.ዐ.ወ) ተከታዩን ሲናገሩ አድምጫለሁ በማለት አነስ (ረ.ዐ) አስተላልፈዋል፦ “አላህ፦ “ባሪያዬን በሁለት ወዳጆች ፈተና አድርሸበት ትዕግሥት ካደረገ የምሰጠው ለውጥ (ምትክ) ጀንነትን ነው” ብለዋል።” “ሁለት ወዳጆች” የሚለው ቃል የሚያመለክተው ሁለቱን ዓይኖቹን ነው። (ቡኻሪ ዘግበውታል)

ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች

1/ ነቢዩ (ሶ.ዐ.ወ) በዚህ ሐዲሳቸው ዓይኖቹን ብቻ ለይተው የተናገሩት ከሰው ልጅ የአካል ክፍሎች መካከል እጅግ ውድ ዋጋ ያላቸው እነርሱ በመሆናቸው ነው።

2/ ጀንነት ታላቅ ለውጥ (ምትክ) ነው። ከዚህች ዓለም ላይ ለዘልዓለም አንጠቀምም። ጀንነት ግን ዘልዓለማዊ ናት።

Umma Life

https://ummalife.com/MuslimEthio

ቴሌግራም/ telegram/

https://t.me/ethiomuslim_1

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group