UMMA TOKEN INVESTOR

1 day Translate - Youtube
Translation is not possible.
Send as a message
Share on my page
Share in the group
2 day Translate
Translation is not possible.

#ራስን #መታገል (#ሙጃሃዳ)

#ክፍል_6

አላህ እንዲህ ብሏል፦

«ከገንዘብም የምትለግሱትን አላህ እርሱን ዐዋቂ ነው።» (አል-በቀራህ፦ 273)

#ሐዲሥ 11 / 100

አቡ ሁረይራ እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕክተኛ፦ \"ጠንካራ ሙእሚን ከደካማ ሙእሚን በላጭና ከአላህ ዘንድም ይበልጥ ተወዳጅ ነው። ሁሉም መልካም ቢሆኑም፣ የሚጠቅምህን ለመፈጸም ጉጉት ይኑርህ። በአላህ ታገዝ፤ አትስነፍ። አንዳች (ክፉ) ነገር ሲገጥምህ፦ \"ይህን፥ ይህን አድርጌ ቢሆን ኖሮ (ይህ ነገር አይደርስብኝም ነበር) አትበል። ይልቁንም \"አላህ ቀድሞውኑ ወስኗል፥ የሻውንም ፈጽሟል\" በል፤ (ቢሆን ኖሮ) የሰይጣንን ሥራ ትከፍታለችና\" ብለዋል። (ሙስሊም ዘግበታውል)

ከሐዲሥ የምንማራቸው ቁምነገሮች

1/ ኃያልነት ወይም ድክመት የሚለካው ከመልካም ተግባራት አንጻር ነው። ራስን ከማረምና ከመምራት፥ ከማስተካከልና ከመግራት አንጻር። የአላህን ፍላጎት ከመሙላትና ለሰዎች ጠቃሚ የሆነ ተግባራትን ከመፈጸም አንጻር።

2/ ሰዎች ክብራቸውን፣ ዲናቸውንና ሥነ ምግባራቸውን በመጠበቅ ለዱንያውም ለቀጣዩም ዓለም ጠቃሚ የሆነ ተግባራትን ለመከወን ሊነሱ ይገባል። ለእንዲህ ዓይነቱ በጎ ተግባርም የአላህ እርዳታና ድጋፍ ያሻቸዋል። አላህ እርዳታውን የለገሠው ያሰበውን ከግብ ያደርሳል።

3/ አንዳች ክፉ አጋጣሚ በሚደርስበት ወቅት ከቁጭትና ተጨማሪ ጥፋት የሚያድን ጥሩ ብልሃት ከዚህ ዘገባ ውስጥ ተጠቅሷል። ይኸውም የአላህን ፍላጎት በውዴታ በጸጋ መቀበል ነው። ያለፈን ነገር እያነሱ ከመቆጨትም መቆጠብ፥ ለሌላ ኪሳራ ያበቃልና።

Umma Life

https://ummalife.com/MuslimEthio

ቴሌግራም/ telegram/

https://t.me/ethiomuslim_1

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
5 days Translate
Translation is not possible.

#ራስን #መታገል (#ሙጃሃዳ)

#ክፍል_5

አላህ እንዲህ ብሏል፦

«...ከመልካም ሥራም ለነፍሶቻችሁ የምታስቀድሙትን ሁሉ፦እርሱ የተሻለና በምንዳም ታላቅ ኾኖ አላህ ዘንድ ታገኙታላችሁ...።» (አል-ሙዘሚል፦ 20)

#ሐዲሥ 11 / 99

ዓኢሻ እንዳስተላለፉት፥ የአላህ መልዕክተኛ፦ \"(ከረመዷን ወር) የመጨረሻዎቹ አሥር ቀናት ሌሊቶቹን በዒባዳ ያነጉ ነበር። ቤተሰቦቻቸውንም ያነቃሉ። (በዒባዳና በመልካም ክንውንም) እጅግ ይበራቱ ነበር። (ቡኻሪና ሙስሊም)

ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች

1/ የላቀ ደረጃ የተሰጣቸውን የተለዩ ወቅቶች መልካም ተግባራትን በማከናወን መጠቀም ብልህነት ነው።

2/ የረመዷን ወር _በተለይ የመጨረሻዎቹ አሥር ቀናት _ ሌሊቱን በዒባዳ ማሳለፍ እጅግ ይወደዳል።

Umma Life

https://ummalife.com/MuslimEthio

ቴሌግራም/ telegram/

https://t.me/ethiomuslim_1

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
6 days Translate
Translation is not possible.

#ራስን #መታገል (#ሙጃሃዳ)

#ክፍል_4

አላህ እንዲህ ብሏል፦

«እውነቱም (ሞት) እስክመጣህ ድረስ ጌታህን ተገዛ።» (አል-ሒጅር፦ 99)

#ሐዲሥ 11 / 98

ዓዒሻ (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት፡- የአላህ መልዕክተኛ (ሶ.ዐ.ወ) እግራቸው እስኪሰነጠቅ ድረስ ሌሊት (ለዒባዳ) ይቆሙ ነበር። «የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! አላህ ላለፉትም ወደፊት ለሚከሰቱት ጥፋትዎም ምህረት አድርጎልዎት እያለ ይህን ያህል መቸገርዎ ለምንድን ነው?» አልኳቸው። «አመስጋኝ ባሪያው መሆን አይገባኝምን?» አሉ።

(ቡኻሪና ሙስሊም ፤ የሐዲሱ ቃል የቡኻሪ ሲሆን ሙጊረት ኢብኑ ሹዕባህን በመጥቀስም ተመሳሳይ ዘገባ አስፍሯል።)

ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች

1/ አላህ ቁርአን ውስጥ የጠቀሳቸው የነቢዩ (ሶዐ.ወ) ጥፋቶች እኛ የምንፈጽማቸው ዓይነት ኃጢአቶች ሆነው ሊታሰቡ እንደማይገባ ዑለሞች ያስጠነቅቃሉ። ነቢያት ታላላቅና አስነዋር ጥቃቅን ወንጀሎችን እንደማይፈጽሙ ዑለሞች በአንድ ድምጽ (ኢጅማዕ) የተስማሙበት ነጥብ ነው። አስነዋሪ ያልሆኑ ጥቃቅን ግድፋቶችን በተመለከተ ግን በዑለሞች መካከል ውዝግብ አለ። አብዘኛዎቹ ዑለሞች «አይፈጽሙም›› በሚለው ይስማማሉ። ነቢያት ከእንዲህ አይነት ጥፋቶች የተጠበቁ ናቸው። ነቢያት ከአላህ ዘንድ የላቀ ደረጃ ስላላቸው ከመልካም ተግባራት መካከል ይበልጥ ብልጫ ያለውን አለመፈጸማቸው ነው ከግድፈት የሚቆጠርባቸው። እንዲህ ዓይነቱን «ጥፋት» አላህ ይቅር ብሏቸዋል።

2/ ጸጋዎች ለአላህ ትዕዛዝ ለማደር (ዚክር) ምክንያቶች ሊሆኑ ይገባል።

Umma Life

https://ummalife.com/MuslimEthio

ቴሌግራም/ telegram/

https://t.me/ethiomuslim_1

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
7 days Translate
Translation is not possible.

#ራስን #መታገል (#ሙጃሃዳ)

#ክፍል_3

አላህ እንዲህ ብሏል፦

«የብናኝ ክብደት ያክልም መልካምን የሠራ ሰው ያገኘዋል።» (አል-ዘልዘለህ፦ 7)

#ሐዲሥ 11 / 97

ኢብኑ አባስ (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕክተኛ (ሶ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል፦ «ብዙ ሰዎች እንደ ቀላል የሚመለከቷቸው ሁለት ጸጋዎች አሉ። እነርሱም፦ ጤንነትና እና ነፃ ጊዜ ናቸው።» (ቡኻሪ ዘግበውታል)

ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች

1/ እዚህ ላይ ሰዎች በነጋዴ፣ በጤንነትና በነፃ ጊዜ ደግሞም በካፒታል ተመስለዋል። ካፒታልን በአግባቡ ሥራ ላይ ማዋል የቻለ ትርፍ ያካብታል።ያላወቀበት ደግሞ ይከስራል።

2/ ጤንነትንና መልካም ጊዜን ወደ አላህ ለመቃረብና መልካም ተግባራትን ለመከወን ግልጋሎት በማዋል በአግባቡ እንዲንጠቀምባቸው ይህ ዘገባ ያሳስበናል።

3/ በርካታ ሰዎች እነኝህን ጸጋዎች በተገቢው መንገድ አይጠቀሙባቸውም። ጊዜያቸውን ያለ አግባብ ያባክናሉ። አካላቸውን የሚጎዳና ጤንነታቸውን ለአደጋ የሚያጋልጡ ነገሮችን ይወስዳሉ። ኢስላም ለጊዜና ጤንነት ከፍተኛ ትኩረት ይሰጣል።

Umma Life

https://ummalife.com/MuslimEthio

ቴሌግራም/ telegram/

https://t.me/ethiomuslim_1

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group