Muslim ሙስሊም Cover Image

Muslim ሙስሊም

Translation is not possible.

#ቆሻሻ_የምትመገብን_ግመል_መጋለብ #ስለመጠላቱ፣ #ቆሻሻዋን_ትታ_እጽዋት_መመገብ #ከጀመረችና_ሥጋዋ_ከጸዳ #ግን_ይህ_መጠላት_ይወገዳል

ሐዲሥ 308 / 1692

ኢብኑ ዑመር እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕክተኛ ቆሻሻ የምትመገብን ግመል መጋለብን ከልክለዋል። (አቡ ዳውድ)

ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች

1/ ቆሻሻ የምትመገብን ግመል መጋለብ ይጠላል። ይህም ዓይነ ምድርንና ሌሎች ቆሻሻዎችን አዘውትራ የምትመገብ ከሆነና ቆሻሻው ጠረኗን ከቀየረው ነው።

2/ ኢስላም ለንጽሕና ከፍተኛ ትኩረት ይሰጣል። ከቆሻሻ መራቅንና መጽዳትን ያስተምራል።

Umma Life

https://ummalife.com/MuslimEthio

ቴሌግራም/ telegram/

https://t.me/ethiomuslim_1

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

#ሁሉንም_እንስሳት፣ #ጉንዳንን_ጨምሮ #በእሳት_ማቃጠል_ስለመከልከሉ

#ክፍል_2

#ሐዲሥ 283 / 1610

ኢብኑ መስዑድ እንዲህ ሲሉ አስተላልፈዋል፤ በአንድ ጉዞ ላይ ከአላህ መልዕክተኛ ጋር ነበርን። ለጉዳያቸው ገለል አሉ። ሁለት ልጆች ያሏት አንዲት ወፍ አየን። ሁለቱን ልጆቿን ወሰድንባት። መጣችና ከበላያችን ታንዣባብ ጀመር። ነቢዩ መጡና፦ የዚህችን ወፍ ልጆች የወሰደ ማን ነው?" አሉ። እኛ ያቃጠልነውን የጉንዳን ማዕከልም ተመለከቱ። ማን አቃጠለው?" አሉ። "እኛ ነን" አልናቸው። "በእሳት የማቃጠል መብት ያለው የእሳት አምላክ ብቻ ነው" አሉን። (አቡ ዳውድ)

ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች

1/ እንስሳትን ያለሸሪዓዊ አግባብ ማንገላታት ክልክል ስለመሆኑ፤

2/ እንስሳትን፣ ቅማልን ወይም ጉንዳንን እንኳ ሳይቀር በእሳት ማቃጠል ክልክል ነው።

3/ ኢስላም ከሰብአዊ መብት አልፎ ለእንስሳት መብት እንኳ ምን ያህል ተቆርቋሪነት እንደሚያሳይ ይህ እና መሰል የሐዲሥ ዘገባዎች ያመለክታሉ። በእርግጥም ለዓለማት በረከት፡ በእርግጥም ለዓለም እዝነት።

Umma Life

https://ummalife.com/MuslimEthio

ቴሌግራም/ telegram/

https://t.me/ethiomuslim_1

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

#ሁሉንም_እንስሳት፣ #ጉንዳንን_ጨምሮ #በእሳት_ማቃጠል_ስለመከልከሉ

#ክፍል_1

#ሐዲሥ 283 / 1609

አቡ ሁረይራ እንዲህ ሲሉ አስተላልፈዋል፤ የአላህ መልዕክተኛ ከአንድ ሠራዊት ጋር አዘመቱን። "እገሌን እና እገሌን ካገኛችኋቸው በእሳት አቃጥሏቸው" ሲሉም ሁለት የቁረይሽ ሰዎችን ስም በመጥራት አዘዙን። ከዚያም መንቀሳቀስ በፈለግን ጊዜ፦ "እገሌንና እገሌን እንድታቃጥሏቸው አዝዣቹ ነበር። በእሳት አላህ እንጅ ማንም ሊቀጣ አይገባም። ስታገኟቸው ግደሏቸው" አሉ። (ቡኻሪ)

ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች

1/ በእሳት ማቃጠል ክልክል ነው።

2/ የመጨረሻው የቅጣት ዓይነት የሞት ቅጣት ብቻ ነው።

Umma Life

https://ummalife.com/MuslimEthio

ቴሌግራም/ telegram/

https://t.me/ethiomuslim_1

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

#ሁለት_ሰዎች_ሦስተኛው_ሳይፈቅድ #መንሾካሾክ_አስፈላጊ_ካልሆነ_በቀር፣ #ማለትም_ምስጢር_ማውራት #ፈልገው_እንዳይሰማቸው #ካልፈለጉ_በቀር፣ #ስለመከልከሉ፥ #ሦስተኛው_ሰው_በማያውቀው #ቋንቋ_ማውጋትም #እንደዚሁ_ስለመሆኑ

#ክፍል_1

አላህ እንዲህ ብሏል፦

"(በመጥፎ) መንሾካሾክ ከሰይጣን ብቻ ነው።" (አል ሙጃደላህ፡ 10)

ሐዲሥ 281 / 1598

ኢብኑ ዑመር እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕክተኛ እንዲህ ብለዋል፦ "ሦስት ሰዎች አብረው ካሉ ሁለቱ ብቻቸውን ሦስተኛውን አግልለው አይንሾካሾኩ።" (ቡኻሪና ሙስሊም)

አቡ ዳውድ ባሰፈሩት ዘገባ አቡ ሷሊሕ እንዳሉት፥ ኢብኑ ዑመርን፦ "አራት ከሆኑስ?" በማለት ጠየቅኳቸው። "አይጎዳህም" አሉኝ።

ማሊክ "ሙወጠእ" በተሰኘ መጽሐፋቸው እንደ ጠቀሱት ዐብደላህ ኢብኑ ዲናር እንዲህ ብለዋል፦ "እኔና ኢብኑ ዑመር ገበያው መሐከል ካለው የኻሊድ ኢብኑ ዑቅባህ ቤት ሔድን። አንድ ሰው መጣና በሹክሹክታ ሊያናግራቸው ፈለገ። ከኢብኑ ዑመር ጋር ከኔ ውጭ ሌላ ሰው አልነበረም። ኢብኑ ዑመር ሌላ ሰው ጠሩና አራት ስንሆን ለኔና ለጠሩት ሰው እንዲህ አሉን፦ "ጥቂት ጊዜ ገለል በሉ። የአላህ መልዕክተኛ ፦ ሁለት ሰዎች ሦስተኛ ሰው አስቀምጠው አይንሾካሾኩ፤ ሲሉ ሰምቻቸዋለሁ።

ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች

1/ ኢስላም እያንዳንዱን የሕይወት ክፍል ሥርዓት ለማስያዝና ለመምራት የሚያደርገውን ጥረት እናስተውላለን። ከሰዎች ጋር ባለን ግንኙነት ስሜታቸው እንዳይጎዳ እንዴት ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለብን እንኳ ያስተምረናል።

2/ ሦስት ሰዎች እያሉ አንዱን ነጥለው ሁለቱ ብቻ፣ አራት ከሆኑ ደግሞ አንዱን ነጥሎ ሦስቱ ብቻ ማንሾካሾካቸውና ምስጢር ማውራታቸው ተገቢ አይደለም። ክልክል ነው። ይህ ጥብቅ ድንጋጌ ሐላል ለሆኑና ለተፈቀዱ ምስጢራዊ ወሬዎች ሲሆን፥ ሐራም የሆነ መንሾካሾክ ግን ክልክልነቱ እጥፍ ይሆናል።

3/ ይህ ድርጊት ክልክል የሆነበት ምክንያት ሁለት ሰዎች ሦስተኛውን አግልለው በሚያንሾካሾኩበት ጊዜ እርሱ ብቻኝነት ሊሰማውና ሐዘንና ጥርጣሬ ሊገባው ስለሚችል ያን ለመከልከል ነው። ሌላ የሚያጫውተው ሰው ካለ ግን ይህ ስሜት አይፈጥርበትም። ኢብኑ ዑመር ያደረጉትም ይህንኑ ነው።

Umma Life

https://ummalife.com/MuslimEthio

ቴሌግራም/ telegram/

https://t.me/ethiomuslim_1

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

#ሙታንን_ያለ_አግባብ #እና #ሸሪዓዊ_ምክንያት #ሳይኖር_መሳደብ_ስለመወገዙ

ሸሪዓዊ ምክንያትና አግባብ የሚሰኙት ሰዎች በአመጽና በፈጠራዊ (ቢድዐ) አስተሳሰብ ወዘተ. እንዳይጠቁ ስለተሰጋ ነው። ይህንን በተመለከተ በርካታ ሐዲሦች ከዚህ በፊት በነበረው ምዕራፍ ሰፍረዋል።

#ሐዲሥ 267 / 1564

ዓኢሻ እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕክተኛ እንዲህ ብለዋል፦ "ሙታንን አትሳደቡ። እነርሱ ወዳስቀደሙት (ተግባር) ደርሰዋልና።" (ቡኻሪ)

ከሐዲሡ የምንማረው ቁምነገር

፨ ሙታንን መሳደብ ክልክል ነው። ከከሐዲያንም ቢሆን አንድን ግለሰብ ለይቶ መሳደብ አግባብ አይደለም። ስድብ የሚያስገኘው ምንም ዓይነት ፋይዳ ባለመኖሩ በተቻለ መጠን መጠንቀቅና አንደበትን በርሱ አለመበከል ተመራጭ ነው። ካልሆነ መዘዝ ይዞ ይመጣል።

Umma Life

https://ummalife.com/MuslimEthio

ቴሌግራም/ telegram/

https://t.me/ethiomuslim_1

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group