Muslim ሙስሊም Cover Image

Muslim ሙስሊም

Translation is not possible.

#ራስን #መታገል (#ሙጃሃዳ)

#ክፍል_15

#ሐዲሥ 11 / 109

አነስ እንዲህ ሲሉ አስተላልፈዋል፦ አጐቴ አነስ ኢብኑ ነድር ከበድር ፍልሚያ አልተሳተፉም ነበር። \"የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! ሙሽሪኮችን ከተፋለሙበት የመጀመሪያ ውጊያ ላይ አልተሳተፍኩም። አላህ ከሙሽሪኮች ጋር ለመፋለም ካበቃኝ የምሠራውን ለሰዎች ያሳያል\" አሉ። የኡሑድ ዕለት ሙስሊሞቹ ወደኋላ አፈገፈጉ። \"አላህ ሆይ! እነኝህ ባልደረቦቼ (ወደኋላ በማፈግፈግ) የፈጸሙትን ድርጊት ላንተ እተዋለሁ። እነዚያኞቹ (ሙሽሪኮችን ማለታቸው ነው) (ነቢዩን በመውጋት) ከፈጸሙት ድርጊት እጄን ንጹሕ አደርጋለሁ\" አሉ። ከዚያም ወደ ፍልሚያው መስክ ሲያመሩ ሰዒድ ኢብኑ ሙዓዝን አገኟቸው፦ \"ሰዒድ ኢብኑ ሙዓዝ ሆይ! ጀነትን ለመጐናጸፍ እመኛለሁ። በከዕባ ጌታ ይሁንብኝ! ከኡሑድ (ተራራ) ወዲህ ማራኪ ሽታዋ እያወደኝ ነው\" አሉ። \"እርሱ (አነስ) የፈጸመውን (የጀግንነት ተግባር) መፈጸም አልቻልኩም ነበር\" አሉ ሰዕድ። ከሰማኒያ ሦስት እስከ ሰማኒያ ዘጠኝ የሚደርሱ በጐራዴ የተመቱ፣ በጦር ወይም በቀስት ፍላፃ የተወጉ ቦታዎችን (ሰውነታቸው ላይ) ተመለክተናል። ተገድለውና አጋሪዎች አካላቸውን ቆራርጠውት ነበር ያገኘናቸው። ከእህታቸው ውጭ ያወቃቸው አልነበረም። በጣቶቻቸው አሻራዎች ነበር የለየቻቸው። ዐብባስም አክለውም እንዲህ ብለዋል፦ \"ተከታዩ የቁርኣን አንቀጽ የወረደው ለርሳቸውና መስሎቻቸው እንደሆነ እንገምታለን፦

\"ከአማኞች ለአላህ ቃል ኪዳን የገቡትን በእውነት የፈጸሙ ወንዶች አልሉ፤ ከነርሱም ስለቱን የፈጸመ (ለሃይማኖቱ የተገደለ) አልለ፤ ከነሱም ገና የሚጠባበቅ አልለ፤ (የገቡበትን ቃል) መለወጥንም አልለወጡም።\" (አል አሕዛብ፡ 23) (ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል)

ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች

1/ በመልካም ቃል ኪዳንና መልካም ሥራ ራስን ማስገደድ እንደሚፈቀድ።

2/ የመልዕክተኛው ባልደረቦች ጀግንነትን ለማግኘት የነበራቸው ጉጉትና ለመስዋዕትነት የነበራቸው ጽኑ ፍላጐት።

Umma Life

https://ummalife.com/MuslimEthio

ቴሌግራም/ telegram/

https://t.me/ethiomuslim_1

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

#ራስን #መታገል (#ሙጃሃዳ)

#ክፍል_14

#ሐዲሥ 11 / 108

አቡ ሱፍያን ዐብደላህ ኢብኑ በሽር አል-አስለሚያ (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕከተኛ (ሶ.ዐ.ወ)፦ “ከሰዎች ሁሉ በላጩ ዕድሜው የረዘመና ሥራውም መልካም የሆነለት ነው” ብለዋል። (ተርሚዚይ ዘግበውታል፤ “ሐሰን” ነውም ብለዋል)

ከሐዲሡ የምንማረው ቁምነገር

=› ዕድሜ መርዘሙ፥ በመልካም ሥራ ከደመቀ፥ ወደ አላህ ለመቃረብ የሚረዱ የመልካም ሥራዎች ስንቅ የሚካበትበት በመሆኑ፥ እጅግ የሚጓጉለት ነው። በአንጻሩ ክፋትን እንጅ ደግነትን የማከል ተስፋ ለሌለው የዕድሜው መርዘም ለበለጠ ጥፋት የሚያበቃ በመሆኑ አስፈላጊው አይደለም። ዕድሜው ረዝሞ ሥራው የከፋ ከሆነ ሰው የበለጠ መጥፎ የለም።

Umma Life

https://ummalife.com/MuslimEthio

ቴሌግራም/ telegram/

https://t.me/ethiomuslim_1

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

#ራስን #መታገል (#ሙጃሃዳ)

#ክፍል_13

#ሐዲሥ 11 / 107

የአላህ መልዕክተኛ (ሶ.ዐ.ወ) አገልጋይ አቡ ዐብደላህ -አቡ አብዱራህማንም ይባላሉ- ሠውባን (ረ.ዐ)፥ የአላህ መልዕክተኛ (ሶ.ዐ.ወ) ተከታዩን ሲናገሩ አድምጫለሁ፥ በማለት አስተላልፈዋል፦ «ሱጁድን (ሶላትን) በማብዛት አደራህን (ተጠናከር)፤ ለአላህ አንዲትን ሱጁድ አትሰግድም፥ አላህ በርሷ ደረጃን ከፍ ያደረገህ፥ ኃጢአትህንም ያበሰልህ ቢሆን እንጅ። (ሙስሊም ዘግበውታል)

ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች

1/ ትርፍ (ነዋፊል) እና ተጠዉዕ ዒባዳዎች ወንጀልን በማሰርዬት ረገድ ተጠቃሾች ናቸው።

2/ ሙስሊሞች ግዴታ የሆኑትንም ሆነ ሱንና ሶላቶችን በተገቢው አኳኋን የመስገድ ከፍተኛ ጉጉት ሊያድርባቸው ይገባል።

Umma Life

https://ummalife.com/MuslimEthio

ቴሌግራም/ telegram/

https://t.me/ethiomuslim_1

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
3 day Translate - Youtube
Translation is not possible.
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group