Ethiopian Muslim ኢትዮ ሙስሊም Cover Image

Ethiopian Muslim ኢትዮ ሙስሊም

Translation is not possible.
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.
#የበጐ #ተግባራት #መንገዶች #በርካታ #ስለመሆናቸው
#ክፍል_20
#ሐዲሥ 13 / 136
ጃቢር (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት፥ በኑ ሰለማዎች ከመስጊድ አቅራቢያ መስፈር ከጀሉ። የአላህ መልዕክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ይህ ሐሳባቸው ደረሳቸው። “ከመስጊዱ አቅራቢያ የመስፈር ሐሳብ እንዳለችሁ ደርሶኛል" አሏቸው። “አዎ! የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! ይህንኑ ፈልገናል” አሉ። “በኑ ሰለማዎች ሆይ! አሁን ያላችሁበትን ቦታ አትልቀቁ፤ በእርምጃችሁ ቁጥር (ምንዳ) ይጻፍላችኋል" አሏቸው። (ሙስሊም ዘግበውታል)
በሌላ ዘገባ፦ “እያንዳንዱ እርምጃ ደረጃን ያስጨምራል" የሚል ተወስቷል። ቡኻሪም አነስን (ረ.ዐ) በመጥቀስ ተመሳሳይ መንፈስ ያዘለ ዘገባ አስፈርዋል።
ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች
1/ አንድ ሰው አጅር የሚያገኘው አንድ መልካም ተግባር የሚጠይቀውን ያህል ጥረት ሲያደርግ መሆኑ።
2/ ለጀመዓ ሶላት ማንም ጉጉት ሊያድርበት ይገባል። ከመስጊድ ርቆ የሚኖር እንኳ ቢሆን።
3/ መስጊድና መሰል የሕዝብ መገልገያ ቦታዎችን ሌሎች አማራጮች እስካሉ ድረስ እንዲጨናነቁ ማድረግ ተገቢ አይደለም። መልዕክተኛው (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) በኒ ሰለማዎችን ካሉበት ቦታ ነቅለው ወደ መስጊድ አቅራቢያ እንዲሠፍሩ አልፈቀዱላቸውም። ሌሎችም የነርሱን ፈለግ በመከተል በሚወስዱት እርምጃ ሊከተል የሚችለውን መጨናነቅ ከወዲሁ ለመከላከል።
Umma Life
https://ummalife.com/MuslimEthio
ቴሌግራም/ telegram/
https://t.me/ethiomuslim_1
image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.
#የበጐ #ተግባራት #መንገዶች #በርካታ #ስለመሆናቸው
#ክፍል_19
#ሐዲሥ 13 / 135
የአላህ መልዕከተኛ (ሶ.ዐ.ወ) ተከታዩን መናገራቸውን ጃቢር (ረ.ዐ) አስተላልፈዋል፦ “አንድ ሙስሊም አትክልት ቢተክል፥ (በሰው ወይም በእንስሳ) የተበላበት፥ የተሰረቀው የተቀነሰበት ሁሉ ሶደቃ ይሆንለታል፡፡" (ሙስሊም ዘግበውታል)
ሌላ ሙስሊም ባሰፈሩት ዘገባ ደግሞ፦ “አንድ ሙስሊም አትክልት ተክሎ፥ ዘር ዘርቶ ሰው፣ እንስሳ ወይም ሌላ ነገር (ከምርቱ) ከተመገበለት ሶደቃ ይሆንለታል" ማለታቸው ተወስቷል። ሁለቱም ዘገባዎች በአነስ (ረ.ዐ)
የተላለፉ ናቸው።
ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገር
1/ አትክልትን መትከልና ዘርን መዝራት ያበረታታል። ትሩፋቱንም ይገልጻል። ይህ ተግባር ሰውየው በመሞቱ ምንዳቸው ከማይቋረጥ መልካም ተግባራት ውስጥ አንዱ ነው።
2/ የአላህን ፍጡራን ጥቅምና ምኞት ማስጠበቅ፥ ጉዳያቸውን መፈጸም ከጽድቅ ተግባራት ይካተታል።
3/ ሙስሊም በተሰረቀው ወይም በተቀማው ገንዘብ፥ ትዕግስት ካደረገ፥ ምንዳን ያገኛል፡፡
Umma Life
https://ummalife.com/MuslimEthio
ቴሌግራም/ telegram/
https://t.me/ethiomuslim_1
image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.
#የበጐ #ተግባራት #መንገዶች #በርካታ #ስለመሆናቸው
#ክፍል_14
#ሐዲሥ 13 / 130
የአላህ መልዕክተኛ (ሶ.ዐ.ወ) ተከታዩን መናገራቸውን አቡ ሁረይራ (ረ.ዐ) አስተላልፈዋል፦ “አምስት ወቅት ሶላቶች፥ ከጁሙዐህ እስከ ጁሙዐህ፥ ከአንዱ ረመዷን እስከ ሌላኛው ረመዷን በመካከላቸው ለሚፈጸሙ (ጥቃቅን) ወንጀሎች ማበሻዎች ናቸው፤ ታላላቅ ወንጀሎች እስካልተፈጸሙ ድረስ።” (ቡኻሪ ዘግበውታል)
ከሐዲሡ የምንማረው ቁምነገር
፨ እነኝህን ግዳጆች በአግባቡ መፈጸም ለጥቃቅን ወንጀሎች መሰረይ ምክንያት ሊሆን ይችላል፤ በአላህ እዝነት (ረሕመት) እና ትሩፋት፡፡ ሰውየው ታላላቅ ወንጀሎችን ካልፈጸመ ከወንጀል የጸዳ ይሆናል። ታላላቅና ታናናሽ ወንጀሎችን የፈጸመ ከሆነ ግን በታላላቅ ወንጀሎች ብቻ ይጠየቃል። ታላላቅ ወንጀሎችንም ቢሆን አላህ ያቀልለታል ተብሎም ይታሰባል። ግን እውነተኛ ተውበት የግድ አስፈላጊው ነው።
Umma Life
https://ummalife.com/MuslimEthio
ቴሌግራም/ telegram/
https://t.me/ethiomuslim_1
image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.
#የበጐ #ተግባራት #መንገዶች #በርካታ #ስለመሆናቸው
#ክፍል_13
#ሐዲሥ 13 / 129
አቡ ሁረይራ (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕከትኛ (ሶ.ዐ.ወ) እንዲህ ሲሉ ተናግረዋል፦ “አንድ ሙስሊም ወይም ሙእሚን ውዱእ በሚያደርግበት ወቅት ፊቱን ሲታጠብ በዓይን የፈጸመውን ወንጀል ሁሉ በፊቱ ላይ ከውሃው ወይም ከመጨረሻው የውሃው ምልስታ እንጥፍጣፊ ጋር ይወገድለታል። እጁን ሲታጠብ እጆቹ በመጨበጥ የፈጸሟቸው ወንጀሎች ሁሉ ከውሃው ወይም ከመጨረሻው የውሃው እንጥፍጣፊ ጋር ይወገዳሉ። እግሩን በሚታጠብበት ወቅት እግሮቹ የሄዷቸው ወንጀሎች ሁሉ ከውሃው ወይም ከመጨረሻው የውሃው እንጥፍጣፊ ጋር ከእግሮቹ ይወገዳሉ፤ (ከዚህች ዓለም) ከወንጀል የጸዳ ሆኖ እስኪወጣ ድረስ።” (ሙስሊም ዘግበውታል)
ከሐዲሡ የምንማረው ቁምነገር
፨ የውዱእ ትሩፋት፤ አዘውትሮ ውዱእ ማድረግ ከወንጀል ለመጽዳት ሰበብ ነው። ይህ የአላህን የላቀ ትሩፋት ያሳያል።
Umma Life
https://ummalife.com/MuslimEthio
ቴሌግራም/ telegram/
https://t.me/ethiomuslim_1
image
Send as a message
Share on my page
Share in the group