#የበጐ #ተግባራት #መንገዶች #በርካታ #ስለመሆናቸው
#ክፍል_20
#ሐዲሥ 13 / 136
ጃቢር (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት፥ በኑ ሰለማዎች ከመስጊድ አቅራቢያ መስፈር ከጀሉ። የአላህ መልዕክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ይህ ሐሳባቸው ደረሳቸው። “ከመስጊዱ አቅራቢያ የመስፈር ሐሳብ እንዳለችሁ ደርሶኛል\" አሏቸው። “አዎ! የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! ይህንኑ ፈልገናል” አሉ። “በኑ ሰለማዎች ሆይ! አሁን ያላችሁበትን ቦታ አትልቀቁ፤ በእርምጃችሁ ቁጥር (ምንዳ) ይጻፍላችኋል\" አሏቸው። (ሙስሊም ዘግበውታል)
በሌላ ዘገባ፦ “እያንዳንዱ እርምጃ ደረጃን ያስጨምራል\" የሚል ተወስቷል። ቡኻሪም አነስን (ረ.ዐ) በመጥቀስ ተመሳሳይ መንፈስ ያዘለ ዘገባ አስፈርዋል።
ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች
1/ አንድ ሰው አጅር የሚያገኘው አንድ መልካም ተግባር የሚጠይቀውን ያህል ጥረት ሲያደርግ መሆኑ።
2/ ለጀመዓ ሶላት ማንም ጉጉት ሊያድርበት ይገባል። ከመስጊድ ርቆ የሚኖር እንኳ ቢሆን።
3/ መስጊድና መሰል የሕዝብ መገልገያ ቦታዎችን ሌሎች አማራጮች እስካሉ ድረስ እንዲጨናነቁ ማድረግ ተገቢ አይደለም። መልዕክተኛው (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) በኒ ሰለማዎችን ካሉበት ቦታ ነቅለው ወደ መስጊድ አቅራቢያ እንዲሠፍሩ አልፈቀዱላቸውም። ሌሎችም የነርሱን ፈለግ በመከተል በሚወስዱት እርምጃ ሊከተል የሚችለውን መጨናነቅ ከወዲሁ ለመከላከል።
Umma Life
https://ummalife.com/MuslimEthio
ቴሌግራም/ telegram/
https://t.me/ethiomuslim_1
ጃቢር (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት፥ በኑ ሰለማዎች ከመስጊድ አቅራቢያ መስፈር ከጀሉ። የአላህ መልዕክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ይህ ሐሳባቸው ደረሳቸው። “ከመስጊዱ አቅራቢያ የመስፈር ሐሳብ እንዳለችሁ ደርሶኛል" አሏቸው። “አዎ! የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! ይህንኑ ፈልገናል” አሉ። “በኑ ሰለማዎች ሆይ! አሁን ያላችሁበትን ቦታ አትልቀቁ፤ በእርምጃችሁ ቁጥር (ምንዳ) ይጻፍላችኋል" አሏቸው። (ሙስሊም ዘግበውታል)
በሌላ ዘገባ፦ “እያንዳንዱ እርምጃ ደረጃን ያስጨምራል" የሚል ተወስቷል። ቡኻሪም አነስን (ረ.ዐ) በመጥቀስ ተመሳሳይ መንፈስ ያዘለ ዘገባ አስፈርዋል።
ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች
1/ አንድ ሰው አጅር የሚያገኘው አንድ መልካም ተግባር የሚጠይቀውን ያህል ጥረት ሲያደርግ መሆኑ።
2/ ለጀመዓ ሶላት ማንም ጉጉት ሊያድርበት ይገባል። ከመስጊድ ርቆ የሚኖር እንኳ ቢሆን።
3/ መስጊድና መሰል የሕዝብ መገልገያ ቦታዎችን ሌሎች አማራጮች እስካሉ ድረስ እንዲጨናነቁ ማድረግ ተገቢ አይደለም። መልዕክተኛው (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) በኒ ሰለማዎችን ካሉበት ቦታ ነቅለው ወደ መስጊድ አቅራቢያ እንዲሠፍሩ አልፈቀዱላቸውም። ሌሎችም የነርሱን ፈለግ በመከተል በሚወስዱት እርምጃ ሊከተል የሚችለውን መጨናነቅ ከወዲሁ ለመከላከል።
Umma Life
ቴሌግራም/ telegram/