#ራስን #መታገል (#ሙጃሃዳ)
#ክፍል_15
#ሐዲሥ 11 / 109
አነስ እንዲህ ሲሉ አስተላልፈዋል፦ አጐቴ አነስ ኢብኑ ነድር ከበድር ፍልሚያ አልተሳተፉም ነበር። \"የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! ሙሽሪኮችን ከተፋለሙበት የመጀመሪያ ውጊያ ላይ አልተሳተፍኩም። አላህ ከሙሽሪኮች ጋር ለመፋለም ካበቃኝ የምሠራውን ለሰዎች ያሳያል\" አሉ። የኡሑድ ዕለት ሙስሊሞቹ ወደኋላ አፈገፈጉ። \"አላህ ሆይ! እነኝህ ባልደረቦቼ (ወደኋላ በማፈግፈግ) የፈጸሙትን ድርጊት ላንተ እተዋለሁ። እነዚያኞቹ (ሙሽሪኮችን ማለታቸው ነው) (ነቢዩን በመውጋት) ከፈጸሙት ድርጊት እጄን ንጹሕ አደርጋለሁ\" አሉ። ከዚያም ወደ ፍልሚያው መስክ ሲያመሩ ሰዒድ ኢብኑ ሙዓዝን አገኟቸው፦ \"ሰዒድ ኢብኑ ሙዓዝ ሆይ! ጀነትን ለመጐናጸፍ እመኛለሁ። በከዕባ ጌታ ይሁንብኝ! ከኡሑድ (ተራራ) ወዲህ ማራኪ ሽታዋ እያወደኝ ነው\" አሉ። \"እርሱ (አነስ) የፈጸመውን (የጀግንነት ተግባር) መፈጸም አልቻልኩም ነበር\" አሉ ሰዕድ። ከሰማኒያ ሦስት እስከ ሰማኒያ ዘጠኝ የሚደርሱ በጐራዴ የተመቱ፣ በጦር ወይም በቀስት ፍላፃ የተወጉ ቦታዎችን (ሰውነታቸው ላይ) ተመለክተናል። ተገድለውና አጋሪዎች አካላቸውን ቆራርጠውት ነበር ያገኘናቸው። ከእህታቸው ውጭ ያወቃቸው አልነበረም። በጣቶቻቸው አሻራዎች ነበር የለየቻቸው። ዐብባስም አክለውም እንዲህ ብለዋል፦ \"ተከታዩ የቁርኣን አንቀጽ የወረደው ለርሳቸውና መስሎቻቸው እንደሆነ እንገምታለን፦
\"ከአማኞች ለአላህ ቃል ኪዳን የገቡትን በእውነት የፈጸሙ ወንዶች አልሉ፤ ከነርሱም ስለቱን የፈጸመ (ለሃይማኖቱ የተገደለ) አልለ፤ ከነሱም ገና የሚጠባበቅ አልለ፤ (የገቡበትን ቃል) መለወጥንም አልለወጡም።\" (አል አሕዛብ፡ 23) (ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል)
ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች
1/ በመልካም ቃል ኪዳንና መልካም ሥራ ራስን ማስገደድ እንደሚፈቀድ።
2/ የመልዕክተኛው ባልደረቦች ጀግንነትን ለማግኘት የነበራቸው ጉጉትና ለመስዋዕትነት የነበራቸው ጽኑ ፍላጐት።
Umma Life
https://ummalife.com/MuslimEthio
ቴሌግራም/ telegram/
https://t.me/ethiomuslim_1
#ራስን #መታገል (#ሙጃሃዳ)
#ክፍል_15
#ሐዲሥ 11 / 109
አነስ እንዲህ ሲሉ አስተላልፈዋል፦ አጐቴ አነስ ኢብኑ ነድር ከበድር ፍልሚያ አልተሳተፉም ነበር። \"የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! ሙሽሪኮችን ከተፋለሙበት የመጀመሪያ ውጊያ ላይ አልተሳተፍኩም። አላህ ከሙሽሪኮች ጋር ለመፋለም ካበቃኝ የምሠራውን ለሰዎች ያሳያል\" አሉ። የኡሑድ ዕለት ሙስሊሞቹ ወደኋላ አፈገፈጉ። \"አላህ ሆይ! እነኝህ ባልደረቦቼ (ወደኋላ በማፈግፈግ) የፈጸሙትን ድርጊት ላንተ እተዋለሁ። እነዚያኞቹ (ሙሽሪኮችን ማለታቸው ነው) (ነቢዩን በመውጋት) ከፈጸሙት ድርጊት እጄን ንጹሕ አደርጋለሁ\" አሉ። ከዚያም ወደ ፍልሚያው መስክ ሲያመሩ ሰዒድ ኢብኑ ሙዓዝን አገኟቸው፦ \"ሰዒድ ኢብኑ ሙዓዝ ሆይ! ጀነትን ለመጐናጸፍ እመኛለሁ። በከዕባ ጌታ ይሁንብኝ! ከኡሑድ (ተራራ) ወዲህ ማራኪ ሽታዋ እያወደኝ ነው\" አሉ። \"እርሱ (አነስ) የፈጸመውን (የጀግንነት ተግባር) መፈጸም አልቻልኩም ነበር\" አሉ ሰዕድ። ከሰማኒያ ሦስት እስከ ሰማኒያ ዘጠኝ የሚደርሱ በጐራዴ የተመቱ፣ በጦር ወይም በቀስት ፍላፃ የተወጉ ቦታዎችን (ሰውነታቸው ላይ) ተመለክተናል። ተገድለውና አጋሪዎች አካላቸውን ቆራርጠውት ነበር ያገኘናቸው። ከእህታቸው ውጭ ያወቃቸው አልነበረም። በጣቶቻቸው አሻራዎች ነበር የለየቻቸው። ዐብባስም አክለውም እንዲህ ብለዋል፦ \"ተከታዩ የቁርኣን አንቀጽ የወረደው ለርሳቸውና መስሎቻቸው እንደሆነ እንገምታለን፦
\"ከአማኞች ለአላህ ቃል ኪዳን የገቡትን በእውነት የፈጸሙ ወንዶች አልሉ፤ ከነርሱም ስለቱን የፈጸመ (ለሃይማኖቱ የተገደለ) አልለ፤ ከነሱም ገና የሚጠባበቅ አልለ፤ (የገቡበትን ቃል) መለወጥንም አልለወጡም።\" (አል አሕዛብ፡ 23) (ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል)
ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች
1/ በመልካም ቃል ኪዳንና መልካም ሥራ ራስን ማስገደድ እንደሚፈቀድ።
2/ የመልዕክተኛው ባልደረቦች ጀግንነትን ለማግኘት የነበራቸው ጉጉትና ለመስዋዕትነት የነበራቸው ጽኑ ፍላጐት።
Umma Life
https://ummalife.com/MuslimEthio
ቴሌግራም/ telegram/
https://t.me/ethiomuslim_1