Translation is not possible.
Copy
 
የጥንቃቄ መረጃ ‼
 
በአዲስ አበባ ሌቦች ሊሰርቋቹ ሲያስቡ ከሚጠቀሙት ዘዴዎች መካከል:—
 
✔ሞተር እና ሳይክል ወደ እርሶ ሲጠጋ ይጠንቀቁ ስንቱ ስልኩን ተበልቷልና።
 
✔የማያውቆት ሰው ፀያፍ ስድብ ይሰድቦታል። ለመጣላት ሲጋበዙ ገላጋይ መስለው የተሳዳቢው ተባባሪ ሌቦች ኪሶትን ያጥቦታል።
 
✔ ታክሲ ውስጥ ሆን ብለው የታመመ ወይም ነፍሰ ጡር የሚመስል ሰው አስቀምጠው መስኮት እንዲከፍቱ በጥድፊያ ይጠይቆታል ። እርሶም መስኮቱን ሲከፍቱ ወይም ቦታ ለመቀየር ሲያስቡ ኪሶት ይገባሉ።
 
✔ የታክሲ ረዳት በመመስል "የት ኖት " ብለው በሚያልፉበት መንገድ ይጠይቆታል። እርሶ ወደጠሩት ቦታ እንደሚሄዱ በማስመሰል ታክሲ ካስገቦት በኋላ ዘርፈው ደብድበው ያወርዶታል።
 
✔ አውቀው በታክሲ ትርፍ እንዲጫኑ ካደረጉ በኋላ " ትራፊክ መጣ፣ውረድ ፣ውረጂ " በማለት አዋክበው አውርደው በመሀል ገንዘቦትን ወይም ሞባይል ስልኮትን ይሰርቆታል።
 
✔ አሁን አሁንማ ማር ፣ቅቤ ተልኮለት ነው በማለት እቤት ሰተት ብለው ገብተው የላከኝን ሰው ልንገረው ስልኮትን አውሱኝ በማለት ያልተሰማቸው በማስመሰል ሹልክ ብለው ያመልጣሉ።
 
✔ መንገድ ላይ አጣዳፊ ካልሆነ ስልክ ባያወሩ ይመረጣል። መንታፊው በዝቷልና።
 
✔ ሎተሪ ደረሰኝ ብሎ ወይም የማያውቁት ሰው መንገድ ላይ እያወሮት ሲሄድ ይጠንቀቁ።
Send as a message
Share on my page
Share in the group