umma1698477709 Profile Picture
UMMA TOKEN INVESTOR

About me

I live in Ethiopia. I am Muslim Inshaalah selefiyun.

Translation is not possible.

አስቸኳይ ‼️‼️‼️‼️

ሼር ሼር ሼር

እዚህ ቁርአን ላይ የፊደል ስህተት አለበት።

❗❗ስህተቱ ያለው ሱራ ዩኑስ ቁጥር 52 ሲሆን ትክክለኛው አቀራር "ዙቁ" በቃፍ ሲሆን በዚህ ቁርአን ግን ያለው "ዙፉ" በ ፋ ፊደል ነው።

አስቸኳይ❗❗❗ሼር ሼር

Al Nejashi printing press

image
image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

እስራኤል ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ በፈፀመችው ጥቃት 350 ፍልስጥኤማውያን ተገደሉ

የእስራኤል ጦር ተዋጊ ጄቶች በጋዛ ከተማ አል ዳራጅ ሰፈር የአል-አሳሊ ቤተሰብ መኖሪያ ቤት ላይ በፈፀመው ጥቃት የአንድ ቤተሰብ አባላት የሆኑ 30 ፍልስጤማውያን ተገድለዋል። በቤቴ ላህያ የእስራኤል ወታደሮች በሰሜን ጋዛ በሚገኝ ትምህርት ቤት ተጠልለው የነበሩ በርካታ የአንድ ቤተሰብ አባላትን ገድለዋል። በማህበራዊ ሚዲያ ላይ በተሰራጨ ቪዲዮ መሰረት የአቡ ሳላህ ቤተሰብ የሆኑ በርካታ አስከሬኖች በኢንዶኔዥያ ሆስፒታል አቅራቢያ በሚገኘው አሌፖ ትምህርት ቤት የመጫወቻ ሜዳ ላይ ይታያል።

በሌላ በኩል በማዕከላዊ ጋዛ ሰርጥ ዋዲ አል-ሳልቃ አካባቢ፣ የእስራኤል ጥቃት በመኖሪያ ቤት ላይ ካነጣጠረ በኋላ አንድ ሕፃን ጨምሮ አራት ሰዎች ተገድለዋል።በጋዛ የሚገኘው የጤና ሚኒስቴር እንዳስታወቀው ከጥቅምት 7 ጀምሮ በእስራኤል ጥቃት የተገደሉት ፍልስጤማውያን ቁጥር 17 ሺ 1 መቶ 77 የደረሰ ሲሆን ከ46,000 በላይ ሌሎች ፍልስጥኤማውያን ቆስለዋል። ባለፉት 24 ሰዓታት ደግሞ 350 ፍልስጤማውያን መገደላቸውን ሚኒስቴሩ አክሎ ገልጿል።

በሰሜን ጋዛ የሚገኘው የጃባሊያ የስደተኞች ካምፕ የእስራኤል ታንኮች አካባቢውን ከበው ከባድ ውጊያ በዚህ ሰዓት እየተካሄደ ይገኛል። በሃማስ የሚተዳደረው የአካባቢው ባለስልጣን 100,000 የሚጠጉ ሰዎች በካምፑ ውስጥ እንደሚገኙ እና ለረሃብ አደጋ ተጋልጠዋል ብሏል።ባለፈው ሳምንት የሰብአዊ እርቅ ካበቃ በኋላ ምንም አይነት እርዳታ ወደ ሰሜን ጋዛ አልደረሰም።

በትናንትናው እለት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ሃላፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በጋዛ ያለው የሰብአዊነት ስርዓት ሊፈርስ እና ህዝባዊ ስርዓቱ ሙሉ በሙሉ ሊናጋ እንደሚችል አስጠንቅቀዋል። ገተሬዝ ይህንን አስተያየት ቢሰነዝሩም የእስራኤል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኤሊ ኮኸን ግን ተችተውታል። የጉቴሬዝ የስልጣን ቆይታ "ለአለም ሰላም አደጋ" ነው ሲሉ ጠርተውታል።

በስምኦን ደረጄ

#ዳጉ_ጆርናል

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

"እውቀት ሶስት ነገሮች ውስጥ ይገኛል። ቁርዓን ወስጥ፣ ሐዲስ ውስጥ እና "አላውቅም" የሚለው መልስ ውስጥ ይገኛል"

አብዱሏህ ኢብኑ ዑመር ሪድዋነላሂ ዐለይሂም

https://t.me/Xuqal

https://ummalife.com/BilalunaEdris1

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

ሱፍያን_ኢብኑ_ዑየይናህ ረሒመሁሏህ እንዲህ ይላሉ :-

«አስተዋይ ማለት መልካምና እና መጥፎን ያወቀ ሰው አይደለም።እነሆ አስተዋይ ማለት መልካምን ባየ ግዜ የተከተለና መጥፎን ባየ ግዜ ደግሞ የራቀው ማለት ነው።»

📚 ۞ حليـة الأوليـاء لأبي نعيـم【8/339】

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

ከዛሬው ጉባኤ የወጣ የጋራ ስምምነት መግለጫ!

🔴 በጋዛ ሰርጥ ላይ ያለውን የእብደት ጦርነት ለማስቆም ታሪካዊ፣ ልዩ እና ቆራጥ ውሳኔ ወስዷል።

🔴 በጋዛ ሰርጥ ላይ ለ17 አመታት የቆየውን ከበባ ለማንሳት ውሳኔ ሰጥቷል።

🔴 የራፋህ ድንበርን በቋሚነት በመክፈት፣ ለነዳጅ፣ ለእርዳታ እና ለህክምና ቁሳቁሶች ምቹ መተላለፊያ እንዲሆን ተወስኗል።

🔴 የጋዛ ሰርጥ መልሶ ግንባታን የሚያግዝ ፈንድ የጋራ ጥምረት በአስቸኳይ በማቋቋም ከ41 ሺህ በላይ ሙሉ በሙሉ የወደመ መኖሪያ ቤቶችን እንዲሁም ከ222 ሺህ በላይ በከፊል የወደሙ መኖሪያ ቤቶችን የመንግስት መስሪያ ቤቶችን፣ መስጊዶችን፣ ቤተክርስትያኖችን፣ ትምህርት ቤቶችን ዳግም ለመገንባት የወሰነ ሲሆን ይህን የፈፀሙ የጦር ወንጀለኞችን ለፍርድ ለማቅረብ እና ለአለም አቀፍ ፍርድ ቤቶች እና ለሚመለከታቸው ፍርድ ቤቶች ለማቅረብ የአረብ እስላማዊ የህግ አካል ለማቋቋም ተወስኗል።

🔴 የወራሪዋ አምባሳደሮች ከአረብ እና ሁሉም እስላማዊ ሀገራት ማባረር ፣የሀገራቸውን አምባሳደሮች በመጥራት እየተፈጸመ ላለው ወንጀል እና እልቂት ምላሽ እና ይህንን ወራሪ ሙሉ በሙሉ ቦይኮት ለማድረግ ተወስኗል።

🔴 ወራሪውን ከፍልስጤም ግዛት ማባረር፣ ወረራውን ማስቆም እና እየሩሳሌም ዋና ከተማዋ በማድረግ የፍልስጤም ሀገርን ለመመስረት ስምምነት ላር ተደርሷል።

የሙሐመድ ትውልድ From Ultra palestine

#palestine

Send as a message
Share on my page
Share in the group