UMMA TOKEN INVESTOR

Translation is not possible.
#8ቱ_የጀነት_በሮች
ነቢዩ (ﷺ) ስለ ጀነት በሮች ብዛት ሲናገሩ
«ጀነት ስምንት በሮች አሏት። አንደኛው አር-ረያን ሲሆን አጿሚዎች በቀር የሚገባበት የለም።» ብለዋል።
(ቡኻሪይ 3257/ ሙስሊም 1152)
በሌላ ሐዲሳቸው ደግሞ፦
«አንድ ሰው ለአላህ ብሎ ሁለት ነገሮችን ሰደቃ ቢሰጥ አላህ ጀነትን ግባ ይለዋል። እንዲሁ ሶላትን የሚሰግዱ በሶላት በር ግቡ ይባላሉ። በጂሐድ የተሳተፉ በጂሐድ በር ግቡ ይባላሉ። ሰደቃ የሰጡ በሰደቃ በር ግቡ ይባላሉ። ፆም የፆሙ በአር-ረያን በር ግቡ ይባላሉ።» አሉ። አቡበክር ሲዲቅም «የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! በሁሉም በር እንዲገባ የሚጠራ ይኖራልን?» አሏቸው። ነቢዩም (ﷺ) «አወ! አንዱ አንተ እንደምትሆን ተስፋ አደርጋለሁ።» አሉ።»
(ቡኻሪይ 1897/ ሙስሊም 1027)
ዑለማዎች ከእነዚህ ሌሎች ሰነዶች በመነሳት የስምንቱን በር ስሞች ያስቀመጡ ሲሆን እነሱም የሚከተሉት ናቸው፦
❶ ባብ አስ-ሶላት
♦️ ሰጋጆች የሚገቡበት
❷ ባብ አል-ጂሐድ
♦️ በጂሐድ የተሳተፉ የሚገቡበት
❸ ባብ አስ-ሰደቃህ
♦️ ሰደቃ የሰጡ የሚገቡበት
❹ ባብ አር-ረያን
♦️ ጿሚዎች የሚገቡበት
❺ ባብ አል-ሐጅ
♦️ ሐጂ ያደረጉ የሚገቡበት
❻ ባብ አል-ኢማን
♦️ ፅኑ ኢማን ያላቸው የሚገቡበት
❼ ባብ አል-ካዚሚን አል-ገይዝ
♦️ ቁጣቸውን የሚቆጣጠሩና ይቅር ባዮች የሚገቡበት
❽ ባብ አዝ-ዚክር
♦️ ዚክር የሚያበዙ የሚገቡበት
image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.
#ታላቁ_ቀን_ጁምዓ!
ረሱል ‏(ﷺ) እንዲህ ይላሉ፦
﴿خَيْرُ يَومٍ طَلَعَتْ عليه الشَّمْسُ يَوْمُ الجُمُعَةِ، فيه خُلِقَ آدَمُ، وفيهِ أُدْخِلَ الجَنَّةَ، وفيهِ أُخْرِجَ مِنْها، ولا تَقُومُ السّاعَةُ إلّا في يَومِ الجُمُعَةِ﴾
“ፀሀይ ከወጣችባቸው ጥሩ ‘የጁምዓ ቀን’ ነው።
➜ አደም የተፈጠረበት ነው።
➜ ወደ ጀነት የገባበት ነው።
➜ ከሷም ከጀነት የወጣበት ነው።
የትንሳዔ ቀንም በጁምዓ ቀን ቢሆን እንጂ አትቆምም።”
📚 ሙስሊም ዘግበውታል: ‍854
image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.
🚨የአል-ቃሳም ብርጌድ ወታደራዊ ቃል አቀባይ አቡ ዑበይዳ ሳምንታዊ መግለጫ፡-
🔹ባለፈው ሳምንት የአልቃሳም ተዋጊዎች 68 ወታደራዊ ተሽከርካሪዎችን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል ማውደም ችለዋል።
🔹የእኛ ተዋጊዎች በተለያዩ ዘመቻዎች 53 የጽዮናውያን ወታደሮችን ከቅርብ ርቀት መግደል ሲችሉ ተጨማሪ 9 ወታደሮችን በጥይት በመምታት ገድለዋል፣ ሌሎች በደርዘን የሚቆጠሩ ወታደሮች ሙት እና ቁስለኛ መካከል እንዲሆኑ አድርገዋል።
🔹በአንድ ሳምንት 57 የተለያዩ ወታደራዊ ተልዕኮዎች ፈፅመናል እነዚህ ተልእኮዎች ጥይቶችን ፀረ-ምሽግ እና ፀረ-ሰው ፈንጂዎችን እንዲሁም መትረየስ በመጠቀም ሰርጎ ገብ የሆኑትን የጽዮናውያን ሃይሎችን ኢላማ አድርገዋል።
🔹በተጨማሪም 4 ቤቶችን በጠላት ጦር ላይ ማፍረስ፣ የሁለት ዋሻዎች መግቢያ እና ፈንጂ የተጠመደበትን ቦታ በጠላት ወታደሮች ላይ ማፈንዳት፣ ሁለት "ስካይ ላርክ" የስለላ ሰው አልባ አውሮፕላኖች መምታት፣ 8 ድሮኖች 2 አጥፍቶ ጠፊ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን ጨምሮ መቆጣጠር ይዘዋል፡፡
🔹የጠላት ወታደራዊ ስብስቦችን በሞርታር መሳሪያ እና በአጭር ርቀት ሚሳኤሎች በሁሉም የውጊያ ግንባሮች ደብድበናል እንዲሁም የተለያዩ የሮኬት ጥቃቶችን ወደ ጽዮናዊው አካል ሰንዝረናል፡፡
በሙስሊሙ ዓለም የተፈጠሩ ሁሉንም አዳዲስ መረጃዎች በተለይም በወቅታዊ የፍልስጤም ጉዳይ እውነተኛ እና ሚዛናዊ መረጃ ለማግኘት የሙሐመድ ትውልድ ገፅን ፎሎው ያድርጉ
image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.
በቁርኣን አንዱ በሌላው ላይ ድምፅን ከፍ ማድረግ
~
ሶላት ስንሰግድ አጠገባችን ሌላ ሰጋጅ ካለ እንዳንወሰውስ ድምፃችንን ዝቅ ልናደርግ ይገባል። ልክ እንዲሁ መስጂድ ውስጥ - ለምሳሌ ጁሙዐ ቀን ሊሆን ይችላል - ቁርኣን ስንቀራ ሌሎችን በሚረብሽ መጠን ድምፃችን ከፍ ያለ መሆን የለበትም። ነብያችን ﷺ በአንድ ወቅት ኢዕቲካፍ ላይ ነበሩ። ድምፃቸውን ከፍ አድርገው የሚቀሩ ሰዎችን ሰሙ። መጋረጃቸውን ገለጥ አድርገው እንዲህ አሉ፦
أَلَا إِنَّ كُلَّكُمْ مُنَاجٍ رَبَّهُ، فَلَا يُؤْذِيَنَّ بَعْضُكُمْ بَعْضًا، وَلَا يَرْفَعْ بَعْضُكُمْ عَلَى بَعْضٍ فِي الْقِرَاءَةِ ، أَوْ قَالَ: فِي الصَّلَاةِ
"ንቁ! እያንዳንዳችሁ ከጌታው ጋር ነው እየተንሾካሾከ ያለው። ስለዚህ አንዳችሁ ሌላውን አያስቸግር። ከፊላችሁ በከፊሉ ላይ ቁርኣንን በመቅራት - ወይም በሶላት - አይጩህ።" [አቡ ዳውድ፡ 1332]
በሌላ ዘገባ ላይ ደግሞ እንዲህ ብለዋል፦
أما إن أحدكم إذا قام في الصلاة، فإنه يناجي ربه، فليعلم أحدكم ما يناجي ربه، ولا يجهر بعضكم على بعض بالقراءة في الصلاة
"አንዳችሁ ለሶላት ሲቆም ከጌታው ጋር ነው የሚንሾካሾከው። ስለሆነም ከጌታው ጋር የሚንሾካሾክበትን ይወቅ። ከፊላችሁ በከፊሉ ላይ በሶላት ውስጥ በቁርኣን አይጩህ።" [ሙስነድ አሕመድ፡ 11896]
ስለዚህ ሌሎች ሰጋጆች ባሉበት ጀማዐ ሶላት ላይ ያለፈንን ስንመልስ፣ ወይም ካጠገባችን ሌሎች ቁርኣን የሚቀሩ ሲኖሩ ድምፃችንን ዝቅ በማድረግ ልንቀራ ይገባል። ጁሙዐን እየጠበቁ በድምፅ ማጉያ ቁርኣንን ከመስጂድ መክፈትም እንዲሁ ተገቢ አይደለም።
ልክ እንዲሁ በየቤታችን ሆነን ሶላት የሚሰግድ ባለበት እየተንጫጩ ማውራትም የተለመደ ነው። ይህም መታረም ያለበት ነው። በቁርኣን አንዱ በሌላው ላይ እንዲጮህ ካልተፈቀደ በሌላ ወሬ፣ ያውም ሶላት ላይ ያለን አካል መወስወስ ግልፅ የሆነ ጥፋት ነው። ለሶላት ክብር ሊኖረን ይገባል። ልጆቻችንንም እንዲሁ አደብ ማስተማር አለብን።
Ibnu Munewor
=
* የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/IbnuMunewor
* የዋትሳፕ ቻናል፦
https://whatsapp.com/channel/0....029VaA3X1e5kg7BlsJbo
* ፌስቡክ
https://www.facebook.com/Ibnu.....Munewor?mibextid=ZbW
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.
    የሰው ልጅ
              ያለ ምንም ነገር ይመጣል:
ከዝያም
      ሁሉም ነገር ለማግኘት ሲል ይሮጣል:
ከዝያም
       ያለ ምንም ነገር ይሄዳል:
ከዝያም
      ስለ ሁሉም ነገር ይጠየቃል።
እቺ ናት ዱንያ!!
منقول
Send as a message
Share on my page
Share in the group