UMMA TOKEN INVESTOR

Qumuqta qilghuchi yo'q.

Sheikh Dr. Salih Fewzan Al-Fewzan

ሸይኽ ዶ/ር ሷሊሕ ፈውዛን አላህ ይጠብቃቸውና የአይሁዶች በፈለስጢን አካባቢ መሰባሰብ የቂያም ቀን አንዱ ምልክት ነው ይላሉ።

አላህ እነዚህን ካፊሮች ከነ አጋሮቻቸው ከምድረ ገፅ ያጥፋቸው።

192 views
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Qumuqta qilghuchi yo'q.

ሸይኽ ፈውዛን ሀፊዘሁሏህ እንዲህ ይላሉ:–

«አንች ሙስሊም እህቴ ሆይ! በወጣትነትሽ እና ተፈላጊ በሆንሽበት ስዓት ለማግባት ፍጠኝ፣ ትምህርትን ለመቀጠል ወይም ለአንድ የስራ ሀላፊነት ብለሽ ትዳርሽን አታዘግይ የተሳካ የሆነ ትዳር ደስታ እና አላማሽ እሱ ነው፤ የትኛውንም ትምህርት እና ስራ ትዳር ይተካዋል ነገር ግን የትኛውም ደረጃ ቢደርስ ትምህርት  ወይም ስራ ትዳርን  አይተካውም !!

➧በቤትሽ ስራ እና ልጆችሽን በመንከባከብ ቋሚ ሁኚ ይህ በህይወትሽ ፍሬያማ የሆነው መሰረታዊ ስራሽ ነው። ይህን ስራሽን ምንም የሚመጣጠነው ነገር ስለሌለ በእሱ ቅያሬን አትፈልጊ ጥሩ የሆነ ባል አያምልጥሽ!!!

https://t.me/kidmiyaletewhidmenhajAselefiya

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Qumuqta qilghuchi yo'q.

ለዒልም ተማሪዎች ጉርሻ

~

ኪታብ ከሚቀሩ ተማሪዎች ውስጥ ብዙዎቹ ለልፋታቸው የሚመጥን በቂ ግንዛቤ አይጨብጡም። ከነዚህ በተቃራኒ ደግሞ በቂራአት ማእድ ላይ ያላቸው ቆይታ አነስተኛ ሆኖ የተሻለ የሚጠቀሙ አሉ። ልዩነቱ ከምን የመነጨ ነው? ለዚህ ልዩነት ብዙ ምክንያቶች ሊኖሩ ይችላሉ። ከነዚህ ውስጥ አንዱ አድምቶ አለመቅራት የሚያመጣው ክፍተት ነው። የብዙ ተማሪዎች አያያዝ የለብ ለብ ነው። አንዱን ኪታብ ጥንቅቅ አድርገን ሳንይዝ ከፍ ወዳለው ለመግባት ያለን ጉጉት ብዙ ቀርተናል የሚል ጉጉታችንን ከማርካት ባለፈ ብስለት እንዳይኖረን ሊያደርገን ይችላል።

ይህንን ክፍተታችንን ለመድፈን ከሚያግዙ መንገዶች ውስጥ ሶስቱን ላንሳ፦

1- ቃላት ለቀማ

2- መልእክቱን መጨበጥ

3- ነጠብጣቦችን ማገናኘት

ላብራራቸው።

1- ቃላት ለቀማ፦

ከምንቀራው ኪታብ ውስጥ አንድ የማናውቀው ቃል መኖር የለበትም። በተቻለ መጠን ሁሉንም ልቅም አድርገን ልንይዝ ይገባል። በዚህ መልኩ ስንሄድ ደርስ በጣም እየቀለለን ነው የሚሄደው። ቃላት በቅጡ ሳንይዝ የምንጓዝ ከሆነ ግን ወደላይ በገፋን ቁጥር ይበልጥ እየከበደን ይሄዳል። በዚያ ላይ ቃላት የማንይዝ ከሆነ አጠቃላይ የደርሱን ጭብጥ የመያዝ እድላችን እያነሰ ነው የሚሄደው።

2- መልእክቱን መጨበጥ:-

ከኪታብ ትምህርት ዋናው የሚፈለገው አላማ መልእክቱን መጨበጥ ነው። ቁርኣን የወረደው፣ ሐዲሥ የተላለፈው የቃላት ትርጉም ለማስተማር ሳይሆን ለሰዎች የሚበጃቸውን መልእክት ለማስተላለፍ ነው። በብዛት በሃገራችን የተለመደው የቃል በቃል ትርጉም የማስተማር ዘዴ በዚህ በኩል ጉልህ ክፍተት አለበት። ስለዚህ ለመልእክት በቂ ትኩረት መስጠት ይገባል።

እዚህ ላይ አንድ ወሳኝ ጥያቄ ሊነሳ ይችላል። "የተማርነውን ኪታብ በበቂ ሁኔታ እንደተገነዘብነው መለኪያው ምንድነው?" የሚል። መለኪያው የተማርነውን ኪታብ ለሌላ ማስተማር በሚያስችል መጠን ይዘነዋል ወይ?" ብለን ራሳችንን መጠየቅ ነው። ለራሳችን እውነተኛ ሆነን እንመልስ። አንዳንዴ አስተማሪዎች ሲሳሳቱ "ማግኘታችን" የራስ ሽንገላ ውስጥ እንዳይከተን ልንጠነቀቅ ይገባል። የእውነት ኪታቡን በስርአት ቁጭ ብለን ማስተማር እንችላለን? ካልሆነ ወደሌላ ኪታብ ለመቀጠል ከመጓጓታችን በፊት አጥርተን እንማር። "ይህንን ኪታብ ቀርተነዋል፤ ሌላ ይሁንልን" ከማለታችን በፊት ራሳችንን እንገምግም።

3- ነጠብጣቦችን ማገናኘት:-

በዚህ ክፍል ሁለት ነጥቦችን ነው መጠቆም የፈለግኩት።

1ኛ፦ ማስረጃን ከነጥቡ ጋር፣ በአንድ ባብ (ርእስ) ስር የተደረደሩ የቁርኣን አንቀፆችንና ሐዲሦችን ከርእሱ ጋር ማገናዘብ። እየነጠሉ መረዳት በቂ አይደለም። ይሄ ሐዲሥ እንዴት ነው ማስረጃ የሚሆነው? ይሄ መልእክት ከርእሱ ጋር እንዴት ነው የሚናኘው? እያልን ማስተዋል ይኖርብናል።

2ኛ፦ ከራሳችንና ከህዝባችን ተጨባጭ ጋር ማገናኘት። ይህም የምንማረው ትምህርት ራስንም ወገንንም ለመለወጥ እንዲያግዘን ይረዳናል።

ወላሁ አዕለም

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Qumuqta qilghuchi yo'q.

ስለ ፈለስጢን ምን አዲስ ነገር አለ⁉️

========================

✍ የፈለስጢን (የጋዛ ሙስሊሞች) ጉዳይ በየቀኑ አሳዛኝነቱ ቀጥሏል። በየቀኑ የንጹሐን ህይዎት እየተቀጠፈ ነው፣ በርካታ መሠረት ልማቶች እየወደሙ ነው።

ዛሬ ይፋ በሆነው መረጃ መሠረት እስካሁን 5087 ሙስሊሞች በጽዮናዊቷ ያላባራ የቦምብ ዝናብ ተገድለዋል፣ ከነዚህ መካከል 2055 የሚሆኑት ህፃናት ሲሆኑ 1119 የሚሆኑት ሴቶች ናቸው። 217ቱ አዛውንቶች ነበሩ። 1500 የሚሆኑት በፍርስራሽ ስር እንደጠፉ ናቸው፤ ከመካከላቸው 800 የሚሆኑት ህፃናት አሉ። እስካሁን ድረስ ጀናዛቸው እንኳ አልተገኘም። 15,273 የሚሆኑት ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባቸዋል።

አጠቃላይ የተፈናቀሉት 1 ሚሊዮን 400 ሺህ አካባቢ ሲሆኑ፤ 685 ሺህ የሚሆኑት ከሌሎች ቤተሰቦቻቸው ጋር ተፈናቅለዋል፣ 565 ሺህ የሚሆኑት ከተባበሩት መንግስታት የስደተኞችና የእርዳታ ሥራ ኤጀንሲ (UNRWA) ጋር ግንኙነት ወዳላቸው ት/ቤቶች ተፈናቅለዋል፣ 101 ሺህ የሚሆኑት በመስጂዶች፣ በቤተ ክርስቲናትና በህዝባዊ ቦታዎች ተጠልለዋል፣ 70 የሚሆኑት በ67 ት/ቤቶች ተፈናቅለው ይገኛሉ።

የተለያዩ ሃገራት መንግስታት የተኩስ አቁም ስምምነት እንዲደረግ ቢጠይቁም፤ አሜሪካ በጸጥታው ም/ቤት ያላትን ድምፅን በድምፅ የመሻር መብት ተጠቅማ የፈለስጢናዊያን ጭፍጨፋ እንዲቀጥል አድርጋለች።

ምን ያክል የፈለስጢን ህፃናትና ሴቶች ተጨፍጭፈው ሲያልቁ እንደምትረካ አይታወቅም።

ሌላውም ዓለም በሰልፍ ድጋፉ እያሳዬ ቢሆንም ከዚያ የዘለለ ማድረግ አልቻለም።

በጋዛ አሁንም ቢሆን የውሃ፣ የመብራት፣ የምግብና የነዳጅ ማዕቀብ እንደተጣለ ነው። ባለፈ ብቻ 20 የሚሆኑ የጭነት መኪኖች ገብተው ነበር። ግን ለ2+ ሚሊዮን ህዝብ ምንም ማለት አይደለም። የጋዛን ሰብዓዊ ቀውስ ለመመከት በየቀኑ መቶ የጭነት መኪኖች መግባት አለባቸው።

አላህ በጥበቡ ከላይ ፈረጃውን አውርዶ ካሉበት በላእ ይገላግላቸው እንጂ እየተካሄደ ያለው ይፋዊ የዘር ማጥፋት ወንጀል ታሪክ የማይረሳው እጅግ አሰቃቂ እልቂት ነው።

ከዱዓእ ውጭ አቅም የለንምና ሁሌም ወንድሞቻችንን እናስታውሳቸው።

||

t.me/MuradTadesse

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
ABU MINHAL RESHAD Сhanged his profile picture
7 month
Qumuqta qilghuchi yo'q.

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group