Akmal Haji Balengo Profile Picture
UMMA TOKEN INVESTOR

Translation is not possible.

ሰበር

አልቃሲም ብርጌድ፡ የፍልስጤም ጦር የጽዮናውያንን የእግር ጦር በጁህር አል ዲክ አድፍጠው ጠብቀው በነፍስ ወከፍ መሳሪያ ከዜሮ ሜትር ርቀት ላይ ጨርሰዋቸዋል።

Al-Qassam Brigades: Our mujahideen trapped a Zionist foot force in a tight ambush in Juhr al-Dik, targeted them with an individual shell, and finished them off from a distance of zero.

كتائب القسام: مجاهدونا يوقعون قوة راجلة صهيونية في كمين محكم في جحر الديك ويستهدفونهم بقذيفة أفراد ويجهزون عليهم من مسافة صفر

በኢትዮጵያ በሰሜን አፍሪካ እና በመካከለኛው ምስራቅ እንዲሁም ፍልስጤምን የተመለከቱ ወቅታዊ መረጃዎች እንዲደርስዎ ይህን ገፅ ፎሎው ያድርጉ የሙሐመድ ትውልድ

#palestine

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

ሃማስ ለእስራኤል የምድር ጦር ወረራ ምለሽ ለመስጠት ዝግጁ ነኝ አለ

ሃማስ እስራኤል በጋዛ ለምታካሂደው የምድር ወረራ ተገቢውን ምለሽ ለመስጠት ዝግጁ መሆኑን አስታውቋል።

የእስራኤል ጦር ቃል አቀባይ ዛሬ ማምሻውን በሰጠት መግለጫ፤ የምድር ኃይላችን በጋዛ የሚያደርገውን ዘመቻ ከዛሬ ምሽት ጀምሮ አስፋፍቶ ያካሂዳል ብለዋል።

የህንን ተከትሎ ሃማስ እስራኤልወረራ ከፈጸመች ዝግጁ ነኝ ማለቱን አጃንስ ፍራንስ ፕሬዝ ዝግቧል። 

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

ሙዓዊያ እና ዐሊይ ረዲየላሁ ዐንሁማ በተጋጩ ግዜ ሁለት

ኢስላማዊ ስረወ መንግስት ተመሰረተ የሮሙ ንጉስ ይህን ሰምቶ

እንዲህ ሲል ደብዳቤ ፃፈ።

<<ከሮም ንጉሰ ነገስት ለ ሙስሊሞች መሪ ሙዐዊያ አቡ ሱፍያን!!

ባንተ እና በዐሊይ መካከል የተከሰተውን ግጭት

ሰምተናል።ስለዚህም ለሙስሊሞች መሪ አንተ መሆን

እንዳለብህም ስለምናምን አንተ ፍቃድህ ከሆነ የዐሊይን ጭንቅላት

ቀንጥሶ የሚያመጣልህን ወታደር ልላክልህ>>

ይህ ደብዳቤ ሙዐዊያ ጋር እንደደረሰም ሙዓዊያም

<<ከሙዓዊያ ለሮም መሪ!!! ሁለት ወንድማማቾች ስለተጣሉ

አንተ ምን አገባህ? አፍህን የማትዘጋ ከሆነ ጅማሬው እኔ ጋ የሆነ

እና ፍፃሜው አንተ ጋ የሆነ ሰራዊት ልኬ አንገትህን በማስቀንጠስ

ለዐሊይ በስጦታ መልኩ አበረክትለታለሁ>>

#ይህ_ትክክለኛ_ሙስሊሞች_ሳለን_ነው

_____

___

ካሊድ ኢብን ወሊድ ለፐርሺያው ንጉሰ ነገስት እንዲህ ሲል

ደብዳቤ ፃፈለት

<<ስለም ትድናለህ። እንቢ ያልክ እንደሆን ግን፤ እናንተ ህይወትን

የምትወዱትን ያህል ሞትን የሚወዱ ሰራዊቶችን ይዤልህ

እመጣለሁ።>>

ንጉሱ ይህን ደብዳቤ ካነበበ በኋላ የቻይናውን ንጉስ የጦር እርዳታ

ሊለምነው ደብዳቤ ፃፈለት።

የቻይናውም ንጉስ እንዲህ ሲል ደብዳቤ መልሶ ላከለት።

<<ንጉስ ሆይ! ተራራን እንኳን ለመናድ ካሰቡ ምንም

ከማያግዳቸው ወታደሮች ጋር ለመጋፈጥ አቅሙ ስለሌለኝ

ጥያቄህን መፈፀም አልችልም።>>

# ምን_ያህል_ሀያላን_እንደነበርን_ተመልከቱ

_____

____

በደውለቱል ዑስማኒያ የአገዛዝ ዘመን የሙስሊም ወታደሮች የጦር

መርከቦቻቸውን ይዘው በአውሮፓ ደሴቶች ሲያልፉ በአከባቢው ያሉ

አብያተ ክርስትያናት በሙሉ ሙስሊሞች መጥተው ፈትህ

እንዳያደርጉ በመፍራት ከበሮ ከመምታት እና ምንም አይነት ድምፅ

ከማሰማት ይቆጠቡ ነበር።

#ያኔ_ጀግና_ሳለን

_____

____

በደውለቱል ኡስማኒያ የአገዛዝ ዘመን በያንዳንዴ ቤት ደጅ ላይ

ሁለት የበር ማንኳኩያዎች ይኖራሉ። አንዱ ትልቅ ሲሆን አንዱ ትንሽ

ነው። በትልቀኛው ከተንኳኳ አንኳኪው ወንድ ነው'ና በሩን ሊከፍት

ሚመጣው ወንድ ይሆናል። ነገር ግን በትንሸኛዋ ከተንኳኳ

አንኳኪዋ ሴት መሆኗ ስለሚታወቅ ሴት ትከፍትላታለች።

በዚያ ምርጥ ዘመን አንድ ቤት ውስጥ ሰው ከታመመ ደጅ ላይ

ቀይ አበባ ይንጠለጠል ነበር። ያን አበባ የተመለከቱ ሰዎች ሁሉ

እዝያ ቤት በሽተኛ መኖሩን ስለሚያውቁ በበሩ ሲያልፉ ድምፃቸውን

ዝቅ ያደርጉ ነበር።

#ሹፍ_ምን_እንመስል_እንደነበር !!!

_____

_

ግዜው ሰላሁዱን አል አዩቢ በይተል መቅዲስን ባስመለሰበት ግዜ

ነበር። እና ጦርነቱ ነገውን ሊጀመር ማታ ላይ የጦር መሪው

ሰላሁዲን የወታደሮቹን ድንኳን እየዞረ ሲያዳምጥ፤ ግማሹ ለይል

ይሰግዳል፣ ሌላው ቁርአን ይቀራል፣ የተቀሩት ደግሞ ይዘክራሉ።

ግን ድንገት በሆነ ድንኳን አጠገብ ሲያልፍ በድንኳኑ ውስጥ ያሉት

ሁሉም ተኝተው ነበር። ይህን ግዜ፦"በዚህች ድንኳን አዳሪዎች

ምክንያት ልንሸነፍ እንችላለን" ብሎ አለፈ።

#ማንተኛበት_ዘመን

_____

___

ቀደምት ዑለማኦች በሶስት ነገራት አደራ ይባባሉ ነበር።

1፦ሰውዬው በሱ እና በአላህ መካከል ያለውን ግንኙነት ካሳመረ፤

በሱ እና በሌሎች መካከል ያለው ግንኙነት ያምርለታል።

2፦ሰውዬው ሚስጥራዊ ተግባሩን ካሳመረ አላህ ይፋዊ ተግባሩን

ያሳምርለታል።

3፦ሰውዬው የአኪራው ጉዳይ ካስጨነቀው አላህ የዱንያውንም

የአኪራውንም ጉዳይ ያግራራለታል።

_____

_

#ትልቁ_ኪሳራ_ማለት_ይህ_ነው

ጀነት ስፋቷ የምድርን እና የሰማያትን ያህል ሁና ላንተ በሷ ቦታ

ሳይኖርህ ሲቀር...ትልቅ ኪሳራ ነው።

በእለታዊ ፕሮግራምህ ውስጥ ቁርአንን መቅራት ካልተካተተ ትልቅ

ኪሳራ ነው።

ይህን ፅሁፍ በማሰራጨት ጓደኛህን እንድታነቃው ይከጀላል!

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

አላህ የነብዩላህ ሙሳን ህዝቦች ከፊርዐውን ነፃ ካደረገ ቡሀላ ወደ አሁኗ ፍልስጢን ሄደው እንዲኖሩ ነገራቸው።ሙሳም በአስራ ሁለት ነገዶች የተከፋፈሉትን ወደ ስድስት መቶ ሺህ የሚጠጉ ህዝቦቻቸውን ይዘው የከተማዋ መግቢያ ላይ ደረሱ።ያኔ አላህ ለሙሳ ገብተው ከነዋሪዎቿ ጋር እንዲዋጉ አዘዛቸው።

መጀመሪያ ሀገር ሰላም ብለው ሰተት ብለው ሊገቡ የመጡ ህዝቦችን''ተዋጉ'' በላቸው የተባሉት ነብይ ከየነገዱ ለህዝባቸው ተወካይ አድርገው የመረጧቸውን አስራ ሁለት ሰዎች ወደ ከተማዋ ገብተው ስለ ነዋሪዎቹ እንዲያጣሩ ላኩዋቸው።እዚህ ጋር ነበር ፈተናው...እነዛ ሰዎች ገብተው የነዋሪዎቹን አፈጣጠር ሲያዩ ረዣዥምና ግዙፎች ሆነው አገኟቸው።''እንዴት ከነዚህ ጋር ፍልሚያ ግጠሙ እንባላለን?''በሚል ስሜት ያዩትን ለሙሳ ዐለይሂ ሰላም ነገሯቸው።ሙሳም ነገሩን ከሰሙ ቡሀላ ወሬውን  ለማንም እንዳያደርሱ አስጠንቅቀው አላህ የሰጣቸው ቅዱስ መሬት ላይ ገብተው እንዲዋጉ ህዝቦቻቸውን እንዲህ በማለት መጣራት ጀመሩ....

يَا قَوْمِ ادْخُلُوا الْأَرْضَ الْمُقَدَّسَةَ الَّتِي كَتَبَ اللَّهُ لَكُمْ وَلَا تَرْتَدُّوا عَلَى أَدْبَارِكُمْ فَتَنقَلِبُوا خَاسِرِينَ

«ሕዝቦቼ ሆይ! ያችን አላህ ለእናንተ ያደረጋትን የተቀደሰችውን መሬት ግቡ፡፡ ወደ ኋላችሁም አትመለሱ፡፡ ከሳሪዎች ኾናችሁ ትመለሳላችሁና፡፡»

አትናገሩ የተባሉትን ሚስጥር ከሁለት ሰዎች በቀር የጠበቀ አልነበረምና ሁሉም ጋር የሰዎቹ ግዙፍነት መረጃ ደርሷል።ፊርዓውንን ያህል አመፀኛ ጌታ ነኝ ባይን ባህር ከፍሎ አሳልፏቸውና አስምጦላቸው ዛሬን እንዲያዩ ትልቅ ተዓምሩን ያሳያቸውን ጌታ እነዚህን ሰዎች ተዋጉ ብሎ ሲያዛቸው ሊያምኑትና እሺ ብለው ሊታዘዙት ሲገባ አሻፈረኝ በማለት የሰጡትን ምላሽ አላህ እንዲህ ይተርክልናል....

قَالُوا يَا مُوسَى إِنَّ فِيهَا قَوْمًا جَبَّارِينَ وَإِنَّا لَن نَّدْخُلَهَا حَتَّى يَخْرُجُوا مِنْهَا فَإِن يَخْرُجُوا مِنْهَا فَإِنَّا دَاخِلُونَ

«ሙሳ ሆይ! በርስዋ ውስጥ ኀያላን ሕዝቦች አሉ፡፡ ከርስዋም እስከሚወጡ ድረስ እኛ ፈጽሞ አንገባትም፡፡ ከርስዋም ቢወጡ እኛ ገቢዎች ነን» አሉ፡፡

ልክ ዛሬ ላይ የሙስሊም ሀገራት አላህን የሚያህል ታላቅ ጌታ እያላቸው እነ አሜሪካንን ሀያላን ናቸው ብለው በማሰብ ትንሽ መራመድ ተስኗቸው እጅ እግራቸውን አጣጥፈው እንደተመለከቱት ሆነ ነገሩ...

ሁሉም አንችላቸውም ብለው ተስፋ በቆረጡበት ሰአት አላህ የማሰብን ኒዕማ የሰጣቸው እሱ ድልን እንደሚሰጣቸው የተማመኑ ሁለት የሙሳ ዐለይሂ ሰላም ተወካዮቹ እንዲህ አሉ

قَالَ رَجُلَانِ مِنَ الَّذِينَ يَخَافُونَ أَنْعَمَ اللَّهُ عَلَيْهِمَا ادْخُلُوا عَلَيْهِمُ الْبَابَ فَإِذَا دَخَلْتُمُوهُ فَإِنَّكُمْ غَالِبُونَ وَعَلَى اللَّهِ فَتَوَكَّلُوا إِن كُنتُم مُّؤْمِنِينَ

«ከእነዚያ (አላህን) ከሚፈሩትና አላህ በእነርሱ ላይ ከለገሰላቸው የኾኑ ሁለት ሰዎች «በእነርሱ (በኀያሎቹ) ላይ በሩን ግቡ፡፡ በገባችሁትም ጊዜ እናንተ አሸናፊዎች ናችሁ፡፡ ምእመናንም እንደኾናችሁ በአላህ ላይ ተመኩ» አሉ።

እዚህ ጋር የሀማስ ወታደሮችንና አጠቃላይ የፍልስጢን ህዝቦችን ወኔ አስታወሰኝ።አላህ ላይ በጣሙን እርግጠኞች ናቸው።ድልን እንደሚሰጣቸው አይጠራጠሩም።ግን አለም ላይ ካለው ሙስሊም አንፃር እንደዛኔው ሁለቱ ሰዎች ጥቂት ናቸውና''በጋራ ከተነሳን እናሸንፋለን በአላህ ላይ ተመኩ''ሲሉ ይጣራሉ።(የሚሰማ ባይኖርም)

የሙሳ ህዝቦች እነዚህን ሁለት ሰዎች ሊሰሟቸው ፍቃደኛ አልሆኑም።እንዲያውም ጭራሽ እንዲህ ብለው ቁርጣቸውን ነገሯቸው....

قَالُوا يَا مُوسَى إِنَّا لَن نَّدْخُلَهَا أَبَدًا مَّا دَامُوا فِيهَا فَاذْهَبْ أَنتَ وَرَبُّكَ فَقَاتِلَا إِنَّا هَاهُنَا قَاعِدُونَ

«ሙሳ ሆይ! በውስጧ እስካሉ ድረስ እኛ ፈጽሞ ምን ጊዜም አንገባትም፡፡ ስለዚህ ኺድ አንተና ጌታህ ተጋደሉ እኛ እዚህ ተቀማጮች ነን» አሉ፡፡

ይሄኔ ሙሳ ዐለይሂ ሰላም እነዚህን ህዝቦች ማነሳሳት እንደማይሆንላቸው ሲገባቸው የመጨረሻ አማራጫቸው የነበረው ወደ ጌታቸው መጣራት ብቻ ነበር።ከህዝባቸው ተስፋ ቆርጠው አላህን እንዲህ አሉት

قَالَ رَبِّ إِنِّي لَا أَمْلِكُ إِلَّا نَفْسِي وَأَخِي فَافْرُقْ بَيْنَنَا وَبَيْنَ الْقَوْمِ الْفَاسِقِينَ

«ጌታዬ ሆይ እኔ ራሴንና ወንድሜን በቀር (ላስገድድ) አልችልም፡፡ በእኛና በአመጸኞቹም ሕዝቦች መካከል ለይ» አለ፡፡

በአላህ ላይ ቅንጣት ጥርጣሬ ሳይኖራቸው አብሯቸው የሚቆም አማኝ በማጣታቸው ምክኒያት ድልን የተነፈጉት ነብዩላህ ሙሳ በነሱ መሀከል አላህ እንዲለይ በምሬት እንደጠየቁት ዛሬም ነጋ ጠባ እንደ ቅጠል እየረገፉ አንድ እኛነታችን የሚፈቅድልንን ''ራሳችንን ከትላንታችን የመቀየር'' ትግል እንኳን የነፈግናቸው የፍልስጢን ወገኖቻችን''በመሀከላችን ለይ እንዳይሉብን''እሰጋለሁ።

አላህ የሙሳን ዐለይሂ ሰላምን ህዝቦችን ከተዋጉ ቅዱስ ምድርን ሊያጎናፅፋቸው ቃል የገባላቸው እሱ ላይ ያላቸውን እምነትና ታዛዥነታቸውን  ሊፈትሽ ነበርና ፈተናቸውን መውደቃቸውን ካረጋገጠ ቡሀላ እንዲህ ሲል ውሳኔውን አስተላለፈ

قَالَ فَإِنَّهَا مُحَرَّمَةٌ عَلَيْهِمْ أَرْبَعِينَ سَنَةً يَتِيهُونَ فِي الْأَرْضِ فَلَا تَأْسَ عَلَى الْقَوْمِ الْفَاسِقِينَ

እርስዋም (የተቀደሰችው መሬት) በእነርሱ ላይ አርባ ዓመት እርም ናት፡፡ በምድረ በዳ ይንከራተታሉ፡፡ «በአመጸኞችም ሕዝቦች ላይ አትዘን» አለው፡፡

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

ጋዛ የኢማሙ ሻፊዒይ ሀገር ናት!

-----

በጋዛ የተወለዱት የአህሉ ሱንና ወል ጀመዓ ኢማም ሙሐመድ ኢብን ኢድሪስ አሽ-ሻፊዒይ እንዲህ ብለው ነበር።

"ከቁርአን ውስጥ አንዲት አያት አለች። በበዳዮች (ለዟሊሞች) ላይ አውዳሚ ቀስት ስትሆን፣ ለተበዳዮች ደግሞ ተስፋ ናት"

"ያቺ አያት (አንቀጽ) የትኛዋ ናት?" ተብለው ሲጠየቁ የሚከተለው አንቀጽ መሆኑን ተናገሩ።

” ﻭﻣﺎ ﻛﺎﻥ ﺭﺑﻚ ﻧﺴﻴﺎ “

“ጌታህም ረሺ (ዘንጊ) አይደለም”

(መርየም 64)

-------

አዎን! ጌታችን በዳዮች የሚሰሩትን እያንዳንዱን ግፍ እየተመለከተ ነው። ደግሞም በዳዮች ከሰሩት ግፍ አንዱንም አይረሳም። ሁሉም ነገር በእርሱ ዘንድ እየተመዘገበ ነው። እርሱ የወሰነው ጊዜ ሲደርስ ደግሞ ለግፈኞችና ለበዳዮች የእጃቸውን ይሰጣቸዋል።

አብሽር! አብሽር!

-----

ፎቶው የጋዛ ከተማ ከሜድትራኒያን ባሕር ስትታይ የነበራትን ገጽታ ያሳያል። ዛሬ ሁሉም ነገር አፈር እየለበሰ ነው።

ይህም ያልፋል እንግዲህ።

Free Palestine.

End the Occupation

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group