UMMA TOKEN INVESTOR

Seid Hassen shared a
Translation is not possible.

🌹ረሱል ﷺ ከሶሃቦቻቸው ጋር ቁጭ ብለው በዱኒያ ላይ በጣም ስለሚዎዷቸው ነገሮች

አየተጨዋወቱ እያሉ ነብዩ ﷺ አቡበክርንረ.ዐ "ያ አባ በከር አንተ በዱኒያ ላይ በጣም የምትወደው

ነገር ምንድነው?" ብለው ጠየቁት።

አቡበክርም  ረ.ዐ "3 ነገሮችን እወዳለሁ:-

1.ከአንቱን ጋር መቀመጥ፣

2.አንቱን ማየት፣

3.አንቱ ባዘዙዋቸው ነገሮች ላይ በሙሉ ገንዘቤን መለገስ" ብሎ መለሰ።

°

ዑመርን ረ.ዐ በተራው ጠየቁት "አንተስ ያዑመር ?"

"በዱኒያ ላይ 3 ነገሮችን እወዳለሁ

1.በድብቅ እንኳን ቢሆን በመልካም ነገር ማዘዝ፣

2.በግልጽ እንኳን ቢሆን ከመጥፎ ነገር መከልከል፣

3 መራራ እንኳን ቢሆን እውነትን መናገር።" ብሎ መለሰ።

°

ዑስማንን ረ.ዐ ጠየቁት "አንተስ ያዑስማን?

በዱኒያ ላይ 3 ነገሮችን እወዳለሁ:-

1.ሰዎችን ማብላት፣

2.ሰላምታን ማብዛት፣

3.ሰዎች በተኙ ጊዜ ሶላትን ማብዛት፣

°

አልይን ረ.ዐ በተራው ጠየቁት "አንተስ ያአልይ ?"

"በዱኒያ ላይ 3ነገሮችን እወዳለሁ:-

1.እንግዳን ማክበር፣

2.በሙቀት ወቅት ፆምን መፆም፣

3.ጠላቴን በሰይፍ መቅላት፣

°

አባ ዘርን ረ.ዐ በተራው ጠየቁት "አንተስ ያአባ ዘር?"

"በዱኒያ ላይ 3 ነገሮችን እወዳለሁ :-

1.እርሃብን እወዳለሁ፣

2.በሽታን እወዳለሁ፣

3.ሞትን እወዳለሁ፣

ነብዩም ﷺ "ያ አባ ዘር ለምን እነዚህን ወደድክ?"

አቡዘር መለሰ "ረሃብን ወደድኩት ቀልቤን ፈሪ ሊያደርግልኝ ዘንድ፣

በሽታን ወደድኩት ወንጀሌን ሊያቀልልኝ ዘንድ፣

ሞትን ወደድኩት ከጌታየ ጋር ሊያገናኜኝ ዘንድ።" ብሎ መለሰ።

°

ነብዩ ﷺ " እኔም በዱኒያ ላይ

3 ነገሮችን እወዳለሁ:-

1.ሽቶን እወዳለሁ፣

2.ሚስቶቼን እወዳለሁ፣

3.የአይኔ ማረፊያ ሶላቴን እወዳለሁ፣

በዚህ መካከል ድንገት ጅብሪል አ.ሰ.ወ ዱብ አለ ሰላምታ ካወረደ በኋላ እንዲህ አለ

"አንቱ የአላህ መልዕክተኛ ﷺ በዱኒያ ላይ እኔም 3 ነገሮችን እወዳለሁ

ነብዩም ﷺ "ምንድናቸው ያ ጀብሪል?" ብለው ጠየቁት።

1.መልዕክትን ማድረስ፣

2. አማናን አደራን መጠበቅ፣

3.ሚስኪኖችን መውደድ፣

ጅብሪል አ.ሰ.ወ ተመልሶ ወደ ከሄደ በኋላ ረሱልና ﷺ ሱሃቦቻቸው ረዲየሏሁ አጅመኢን ከመቀመጫቸው ሳይነሱ

ተመልሶ መጣና አሁንም ሰላምታውን አቅርቦ:-

"አላህም ሱ.ወ. ሰላም ብሏችኋል ካለ በኋላ አላህም ሱ.ወ እንዲህ ብሏል:-

በዱኒያ ላይ 3 ነገሮችን እወዳለሁ:-

1.አላህን አውሺ የሆነችን ምላስ፣

2.አላህን ፈሪ የሆነችን ቀልብ፣

3.መከራ የበዛበት ታጋሽ የሆነችን ጀሰድ።

አላህ ሱ.ወ ታጋሾች አድርጎ ነብዩና ﷺ ሱሃቦች ረ.ዐ.አ የወደዱትን ያስወድደን!

°

Follow & Share →Abubekr Ibn Fulan

↓↓↓↓

Abubekr Ibn Fulan

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Seid Hassen shared a
Translation is not possible.

ሙዓዊያ እና ዐሊይ ረዲየላሁ ዐንሁማ በተጋጩ ግዜ ሁለት

ኢስላማዊ ስረወ መንግስት ተመሰረተ የሮሙ ንጉስ ይህን ሰምቶ

እንዲህ ሲል ደብዳቤ ፃፈ።

<<ከሮም ንጉሰ ነገስት ለ ሙስሊሞች መሪ ሙዐዊያ አቡ ሱፍያን!!

ባንተ እና በዐሊይ መካከል የተከሰተውን ግጭት

ሰምተናል።ስለዚህም ለሙስሊሞች መሪ አንተ መሆን

እንዳለብህም ስለምናምን አንተ ፍቃድህ ከሆነ የዐሊይን ጭንቅላት

ቀንጥሶ የሚያመጣልህን ወታደር ልላክልህ>>

ይህ ደብዳቤ ሙዐዊያ ጋር እንደደረሰም ሙዓዊያም

<<ከሙዓዊያ ለሮም መሪ!!! ሁለት ወንድማማቾች ስለተጣሉ

አንተ ምን አገባህ? አፍህን የማትዘጋ ከሆነ ጅማሬው እኔ ጋ የሆነ

እና ፍፃሜው አንተ ጋ የሆነ ሰራዊት ልኬ አንገትህን በማስቀንጠስ

ለዐሊይ በስጦታ መልኩ አበረክትለታለሁ>>

#ይህ_ትክክለኛ_ሙስሊሞች_ሳለን_ነው

_____

___

ካሊድ ኢብን ወሊድ ለፐርሺያው ንጉሰ ነገስት እንዲህ ሲል

ደብዳቤ ፃፈለት

<<ስለም ትድናለህ። እንቢ ያልክ እንደሆን ግን፤ እናንተ ህይወትን

የምትወዱትን ያህል ሞትን የሚወዱ ሰራዊቶችን ይዤልህ

እመጣለሁ።>>

ንጉሱ ይህን ደብዳቤ ካነበበ በኋላ የቻይናውን ንጉስ የጦር እርዳታ

ሊለምነው ደብዳቤ ፃፈለት።

የቻይናውም ንጉስ እንዲህ ሲል ደብዳቤ መልሶ ላከለት።

<<ንጉስ ሆይ! ተራራን እንኳን ለመናድ ካሰቡ ምንም

ከማያግዳቸው ወታደሮች ጋር ለመጋፈጥ አቅሙ ስለሌለኝ

ጥያቄህን መፈፀም አልችልም።>>

# ምን_ያህል_ሀያላን_እንደነበርን_ተመልከቱ

_____

____

በደውለቱል ዑስማኒያ የአገዛዝ ዘመን የሙስሊም ወታደሮች የጦር

መርከቦቻቸውን ይዘው በአውሮፓ ደሴቶች ሲያልፉ በአከባቢው ያሉ

አብያተ ክርስትያናት በሙሉ ሙስሊሞች መጥተው ፈትህ

እንዳያደርጉ በመፍራት ከበሮ ከመምታት እና ምንም አይነት ድምፅ

ከማሰማት ይቆጠቡ ነበር።

#ያኔ_ጀግና_ሳለን

_____

____

በደውለቱል ኡስማኒያ የአገዛዝ ዘመን በያንዳንዴ ቤት ደጅ ላይ

ሁለት የበር ማንኳኩያዎች ይኖራሉ። አንዱ ትልቅ ሲሆን አንዱ ትንሽ

ነው። በትልቀኛው ከተንኳኳ አንኳኪው ወንድ ነው'ና በሩን ሊከፍት

ሚመጣው ወንድ ይሆናል። ነገር ግን በትንሸኛዋ ከተንኳኳ

አንኳኪዋ ሴት መሆኗ ስለሚታወቅ ሴት ትከፍትላታለች።

በዚያ ምርጥ ዘመን አንድ ቤት ውስጥ ሰው ከታመመ ደጅ ላይ

ቀይ አበባ ይንጠለጠል ነበር። ያን አበባ የተመለከቱ ሰዎች ሁሉ

እዝያ ቤት በሽተኛ መኖሩን ስለሚያውቁ በበሩ ሲያልፉ ድምፃቸውን

ዝቅ ያደርጉ ነበር።

#ሹፍ_ምን_እንመስል_እንደነበር !!!

_____

_

ግዜው ሰላሁዱን አል አዩቢ በይተል መቅዲስን ባስመለሰበት ግዜ

ነበር። እና ጦርነቱ ነገውን ሊጀመር ማታ ላይ የጦር መሪው

ሰላሁዲን የወታደሮቹን ድንኳን እየዞረ ሲያዳምጥ፤ ግማሹ ለይል

ይሰግዳል፣ ሌላው ቁርአን ይቀራል፣ የተቀሩት ደግሞ ይዘክራሉ።

ግን ድንገት በሆነ ድንኳን አጠገብ ሲያልፍ በድንኳኑ ውስጥ ያሉት

ሁሉም ተኝተው ነበር። ይህን ግዜ፦"በዚህች ድንኳን አዳሪዎች

ምክንያት ልንሸነፍ እንችላለን" ብሎ አለፈ።

#ማንተኛበት_ዘመን

_____

___

ቀደምት ዑለማኦች በሶስት ነገራት አደራ ይባባሉ ነበር።

1፦ሰውዬው በሱ እና በአላህ መካከል ያለውን ግንኙነት ካሳመረ፤

በሱ እና በሌሎች መካከል ያለው ግንኙነት ያምርለታል።

2፦ሰውዬው ሚስጥራዊ ተግባሩን ካሳመረ አላህ ይፋዊ ተግባሩን

ያሳምርለታል።

3፦ሰውዬው የአኪራው ጉዳይ ካስጨነቀው አላህ የዱንያውንም

የአኪራውንም ጉዳይ ያግራራለታል።

_____

_

#ትልቁ_ኪሳራ_ማለት_ይህ_ነው

ጀነት ስፋቷ የምድርን እና የሰማያትን ያህል ሁና ላንተ በሷ ቦታ

ሳይኖርህ ሲቀር...ትልቅ ኪሳራ ነው።

በእለታዊ ፕሮግራምህ ውስጥ ቁርአንን መቅራት ካልተካተተ ትልቅ

ኪሳራ ነው።

ይህን ፅሁፍ በማሰራጨት ጓደኛህን እንድታነቃው ይከጀላል!

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Seid Hassen shared a
Translation is not possible.

#ኑ_ተፈደሉ አላህ ከእርሱ በቀር ሌላ አምላክ የለም፡፡ ሕያው ራሱን ቻይ ነው፡፡ ማንገላጀትም እንቅልፍም አትይዘውም፡፡ በሰማያት ውስጥና በምድር ውስጥ ያለው ሁሉ የርሱ ብቻ ነው፡፡ ያ እርሱ ዘንድ በፈቃዱ ቢኾን እንጅ የሚያማልድ ማነው? (ከፍጡሮች) በፊታቸው ያለውንና ከኋላቸው ያለውን ሁሉ ያውቃል፡፡ በሻውም ነገር እንጂ ከዕውቀቱ በምንም ነገር አያካብቡም (አያውቁም)፡፡ መንበሩ ሰማያትንና ምድርን ሰፋ፡፡ ጥበቃቸውም አያቅተውም፡፡ እርሱም የሁሉ በላይ ታላቅ ነው፡፡ 🌸አል በቀራህ 255🌸

🌸

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Seid Hassen shared a
Translation is not possible.

እስራኤል 680 የጦር ጄቶች አሏት ።

ሁሉም በሚባል መልኩ አሜሪካ ስርታ ያስረከበቻት ነው ።

ከነዚህ ውስጥ 360 የሚሆኑት ሀያሎቹ የአሜሪካ F-16 የጦር ጄቶች ናቸው !

36 የሚሆኑት ደግሞ ከራዳር እይታ ውጭ መብረር የሚችሉትና የየትኛውንም ሀገር ድንበር ጥሰው ሲገቡ የማይታዩት F-35 የጦር ጀቶች ናቸው ። ሁሉም አሜሪካ ሰራሽ ናቸው !

በዚያ ላይ 2,200 ታንኮች አሏት አብዛኛው ከአሜሪካ የተገኙ ናቸው ።

አሜሪካ እስራኤልን ከሀማስ ትከላከልበት ዘንዳ Iron dome የተሰኘውን የአየር መከላከያም አስታጥቃለች ።

እስራኤል ከ 500,000 በላይ እግረኛ ጦርም አላት ።

ወታደራዊ በጀቷ 24 ቢሊዮን ዶላር ሲሆን ከዚህ ውስጥ 4 ቢሊዮን ዶላሩ በአሜሪካ ይሸፈናል ።

ፍልስጤማዊያን የሚታገሉት ከዚህች የአሜሪካና የእንግሊዝ ልጅ ጋር ነው ።

እስራኤልን ማጥቃትም ሆነ መደብደብ ለኢራንም ሆነ ለሌሎች የእስራኤል ጠላቶች በጣም የሚያስፈራ ሆኖ አይደለም ። ዋናው ፈተና አሜሪካ ከጀርባ መሰለፏ ነው ።

ጠላት ሀያል ነው ተብሎ ሙቶ አይጠበቅምና ፍልስጤማዊያን በፅናት እየታገሉ ነው ። ይሄው ለ 22 ቀን ገትረው ይዘዋታል ። ባለቤቷን የተማመነች በግ እንዲሉ እስራኤልም ጌታዋን አሜሪካን ተማምና በእብሪቷ ቀጥላለች !

ፍልስጤሞችም አላህን ቢሞቱ ውደታውን ቢኖሩ ድሉን አምነው እየተዋደቁ ነው !

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Seid Hassen shared a
Translation is not possible.

ያ ኢላሂ አንተው ሁናቸው🤲

‌‎« أَمَّن يُجِيبُ الْمُضْطَرَّ إِذَا دَعَاهُ وَيَكْشِفُ السُّوءَ»

«ያ ችግረኛን በለመነው ጊዜ የሚቀበል፣ መከራንም የሚያስወግድ…»

[አ-ን'ነምል: 62]

قيل: المُضطر هو الذي انقطعت فيه كل السبل ولم يبقَ له ناصر أو مغيث........سوى الله.

«ችግረኛ/የተጨናነቀ» ማለት መንገዱ ሁሉ የተዘጋበት/የተቋረጠበት፣ ለርሱ ከአላህ ውጭ ረዳትም ሆነ የሚጠጋበት አንድም ያላገኘ ማለት ነው።

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group