UMMA TOKEN INVESTOR

About me

የሰው ልጅ ከአላህ በስተቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ አለመኖሩን ከማወቅ የበለጠ እውቀት አልተሰጠውም። የእውቀት ክብሩና ደረጃው የሚለካው በሚታወቀው ነገር ልክ ከሆነ፣ ከአላህ የሚበልጥ ክብር ያለው ነገር የለምና፤ ስለ አላህም ማወቅ ከእውቀቶች ሁሉ በላጭና ተቀዳሚ ተግባር ይሆናል ማለት ነው። ኡስታዝ አቡ ሀይደር

Translation is not possible.

አምስቱ ተወዳጅ ተግባራት በረመዳን

በአቡ ሀይደር

3) ኢፍጣርን ማቻኮል፡- የጸሀይ መግባት ከተረጋገጠ ወይም የመግሪብን አዛን እንደሰማን ወዲያውኑ ማፍጠር ተወዳጅ ተግባር ነው፡፡

አቢ ዘር(ረዲየላሁ ዐንሁ) እንደነገረን የአላህ መልክተኛ(ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ፡-

"ኡመቶቼ ኢፍጣርን እስካፋጠኑ ድረስ በመልካም ነገር ላይ ከመሆን አይወገዱም" (አሕመድ 21312)፡፡

ይቀጥላል...

ለበለጠ ኢስላማዊ ዳዕዋ በዚህ ይከታተሉን

በቴሌ ግራም ለመከታተል

https://t.me/islamictrueth

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

አምስት ነገሮችን ከረመዷን በፊት!!

በ አቡ ሀይደር

5ኛ) ሌላው ረመዷንን በተመለከተ ያሉ ሸሪዓዊ ድንጋጌዎችን ልታውቅ ይገባሀል፡፡ የጾም መስፈርቶች፣ ማእዘናቶች፣ ተወዳጅ (ሱና) ተግባራቶች፣ አፍራሽና የተጠሉ ተግባራቶች እንዲሁም የተፈቀዱ ተግባራቶች ምን ምን እንደሆኑ ከሚያውቁ ወንድምና እህቶች ጠይቀህ መማር አለብህ፡፡ የአላህ መልክተኛም (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንደተናገሩት፡- "አላህ ኸይር የሻለትን ሰው የዲን ግንዛቤን ይለግሰዋል" ነውና ለማወቅ መጣር ይጠበቅብሀል (ቡኻሪይ)፡፡

አላህ ይወፍቀን!

ኢስላማዊ ዳእዋ በቴሌ ግራም ለመከታታል ሊንኩን ይጫኑት!

https://telegram.me/islamictrueth

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

አምስት ነገሮችን ከረመዷን በፊት!!

በ አቡ ሀይደር

4ኛ) ይህ ወር የተውበት፣ የንሰሀና የምሕረት ወር ነው፡፡ ስለዚህ በተውበትና በኢስቲግፋር መበርታት ይጠበቅብሀል፡፡ በሐዲሥም እንደተገለጸው፡-

አቢ ሙሰል-አሽዐሪይ (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንደነገረን የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ፡- "አላህ የቀን ጥፋተኞችን ሊምራቸው በለሊት የራሕመት እጁን ይዘረጋል፡፡ የለሊትን ጥፋተኞችን ሊምራቸው በቀንም የራሕመት እጁን ይዘረጋል፡፡ ይህም የሚሆነው ጸሀይ ከመግቢያዋ በኩል ብቅ እስክትል ነው" (ሙስሊም 7165)፡፡

በሌላም ሐዲሡል ቁድሲይ ላይ ጌታችን፡- ‹‹የአደም ልጆች ሆይ! እናንተ በቀንም በለሊትም ኃጢአት ትፈጽማላችሁ፡፡ እኔ ደግሞ ኃጢአትን በመላ እምራለሁና እምራችሁ ዘንድ ማረን በሉኝ!›› ይለናል (ሙስሊም)፡፡

በተጨማሪም በሌላ ዘገባ ይኸው ጌታችን አላህ፡- ‹‹የአደም ልጅ ሆይ! ኃጢአትህ በዝቶ ሰማይ ጣሪያ ቢደርስና ከዛም ‹ጌታዬ ሆይ! ማረኝ› ብለህ ምሕረትን ብትጠይቀኝ፡ ምንም ሳይቸግረኝና ምንም ሳይመስለኝ እምርሐለሁ›› ይላል (ቲርሚዚይ 3540)፡፡

ታዲያ ዛሬ በረመዷን ወር ተውበት ያልገባህ መቼ ነው የምትቶብተው? በዚህ ወር ወደ አላህ ካልተመለስክ መቼ ነው የምትመለሰው?

ይቀጥላል...

ኢስላማዊ ዳእዋ በቴሌ ግራም ለመከታታል ሊንኩን ይጫኑት!

https://telegram.me/islamictrueth

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

አምስት ነገሮችን ከረመዷን በፊት!!

በ አቡ ሀይደር

1ኛ) የረመዷን ወር ከመጣልህና በበሩም ደጅ ላይ ከደረስህ አላህ ላንተ በማሰብ የዚህ ወር ተካፋይ እንድትሆን የላከልህ ጸጋ መሆኑን ልታስብ ይገባሀል፡፡ ዕድሜና ጤናን ሰጥቶህ ይህን የተባረከ ወር እንድትቋደስ ማድረግ ትልቅ ኒዕማ (ጸጋ) ነውና፡፡ ስንትና ስንት ልቦች ይህን ወር ተመኝተውት ነበር? የቀደር ጉዳይ ሆኖ ግን ስንቶች ወደ አኼራ ተሸኙ? አሁን እነሱ ከአፈር በታች በቀብር ይገኛሉ፡፡ አንተ ግን ሕያው ኾነህ የረመዷንን ወር ከተገኘህ የጌታህ ጸጋ መሆኑን ዐውቀህ ለዚህ ያደረሰህን አላህ አመስግነው፡፡ በልብህም በአንደበትህም፡- "ጌታዬ አምላኬ አላህ ሆይ! የረመዷንን ወር በሰላም በጤና ስላደረስከኝ እንዲሁም ስለማይቆጠረው ውለታህ ከልቤ አመሰግንሀለሁ" በል፡፡ ይህንን ካልክ ከልብህም ለወሩ ከተዘጋጀህ ጌታህ ደግሞ ሌላንም እንደሚጨምርልህ እንዲህ በማለት በቃሉ አስታውቆሀል፡-

"ጌታችሁም፦ ብታመሰግኑ በእርግጥ እጨምርላችኋለሁ ብትክዱም (እቀጣችኋላሁ)፤ ቅጣቴ በእርግጥ ብርቱ ነውና በማለት ባስታወቀ ጊዜ (አስታውሱ)።" (ሱረቱ ኢብራሂም 14፡7)፡፡

በተጨማሪም ሌላ ልታስታውሰው የሚገባህ ነገር እንዳንተው ስንቶች ረመዷንን ተገኝተው ግን ህመምና እርጅና እንዲሁም ሌላ ምክንያት ከጾምና ከቂያሙ-ለይል ያገዳቸው መኖራቸውን ነው፡፡ ታዲያ አንተ ጤናማና ጠንካራ ከሆንክ ጌታህን አመስግነውና በዚህ አካልህም ጾሙንና ዒባዳውን በአግባቡ እንድታከናውን ጌታህን እገዛ ለምነው፡፡ ያለሱ እገዛ የትም እንደማትደርስም እንዲህ በማለት ይነግርሀል፡-

"አንተን ብቻ እንግገዛለን፤ አንተንም ብቻ እርዳታን እንለምናለን (በሉ)።" (ሱረቱል ፋቲሓ 5)፡፡

ይቀጥላል...

ኢስላማዊ ዳእዋ በቴሌ ግራም ለመከታታል ሊንኩን ይጫኑት!

https://telegram.me/islamictrueth

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

ተማራማሪዎች ለማግኘት ጊዜ ይፈጅባቸዋል እንጂ ለሁሉም በሽታ መድኃኒት አለው! ይህ ደግሞ የነብዩ ሙሀመድ(ሶለላሁ አለይሂ ወሰለም) ንግግር ነዉ።

ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦

﴿ما أنْزَلَ اللَّهُ داءً إلّا أنْزَلَ له شِفاءً.﴾

“አላህ አንድን በሽታ ከሰማይ አያወርድም። ለሷ የሚሆን መዳኛ አብሮ ቢያወርድላት እንጂ።” 📚 [ቡኻሪ ዘግበውታል 5678]

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group