UMMA TOKEN INVESTOR

amrela nuri shared a
Translation is not possible.

ዓጃኢብ የሆነ ታሪክ

November 26, 2022

አጃዒብ የሆነ ታሪክ ላካፍላችሁ‼

ዲኔ ላይ ደህና ነኝ፡፡ መልክ አለኝ ባይባልም አልከፋም፡፡ በባህሪዬ ጥሩ ነኝ ብዬ አስባለሁ፡፡ ከቤተሰብ ሳልርቅ ነው ያደግኩት፡፡ የልጅነት ጊዜዬ አልፎ ወጣትነት መጣ፡፡ እንደማንኛዋም ሴት ትዳር አሰብኩ፡፡ ግና በማላውቀው ምክንያት ድርሻዬ ዘገየብኝ፡፡ ለጋብቻ የሚጠይቀኝ ጠፋ፡፡ ከኔ በኋላ የተወለዱ የቤተሰብም፣ የዘመድም፣ የሰፈርም ልጆች አንድ በአንድ አገቡ፡፡ ወለዱ፡፡ ልጆቻቸውም አደጉ፡፡ ሳላስበው 34 ዓመት ሆነኝ፡፡ እድሜዬን ሳስታውሰው ደነገጥኩ፡፡ ብቻዬን ቆሜ የቀረሁ እስኪመስለኝ ድረስ ተሰማኝ፡፡

⊙ የሆነ ጊዜ ከቅርብ ዘመድ የሆነ አንድ ወጣት ለጋብቻ ጠየቀኝ፡፡ ፈቃደኝነቴን ገለፅኩ፡፡ ሁለት ዓመት ይበልጠኛል፡፡ ዲኑም ፀባዩም ቆንጆ ነው፡፡ ደስ አለኝ፡፡ ከሀሳቤ የተገላገልኩ መሰለኝ፡፡ ቤተሰብም ደስ አለው፡፡

≅ ኒካሕ ለማሰር ተዘጋጀን፡፡ አንዳንድ ጉዳዮችን ለመጨረስ ብሎ መታወቂያዬን ይዞ ሄደ፡፡ 

.

ከሁለት ቀን በኋላ ስልክ ተደወለልኝ፡፡ እናቱ ነበረች፡፡ እንደምትፈልገኝ ነገረችኝ፡፡ ምን ይሆን ብዬ እየበረርኩ ሄደኩኝ፡፡ ቤታቸው ገባሁ፡፡ ጥቂት ካወራን በኋላ መታወቂያዬን እያሳየችኝ እዚህ ላይ የተጠቀሰው የትውልድ ቀኔ ትክክል ስለመሆኑ ጠየቀችኝ፡፡ “አዎን! ትክክል ነው” አልኳት፡፡ 

“እንግዲያውስ አንች አርባ ተጠግተሻል መውለድ አትችይም” አለችኝ፡፡ “34 ዓመቴኮ ነው እንዴት አልችልም” አልኳት፡፡ 

“አይ … አንች ሰላሳ አልፎሻል እኔ ደግሞ ልጅ አይደለም ገና የልጅ ልጅ ማየት እፈልጋለሁ” አለች፡፡ ጋብቻው እንዲሰረዝ ሞገተች፡፡ ልጇንም አሳመነች። ለቤተሰቤ ምን እንደምላቸው እያሰላሰልኩ ተስፋ ቆርጬ ወደቤቴ ተመለስኩ፡፡

≅ ቀናት አለፉ፡፡ ድፍን ስድስት ወራትን በሐዘን አሳለፍኩ፡፡ ረጃጅም ቀንና ሌሊቶችን ስብሰለሰል ከረምኩ፡፡ በር በሩን ባይ እኔን ብሎ የሚመጣ ለኔ የተፃፈ ባል ጠፋ፡፡ ብቸኝነት፣ ባይተዋርነት፣ አጥንት ድረስ ዘልቆ ተሰማኝ፡፡ 

አባቴ ሁኔታዬን ይከታተላል፡፡ ስለኔ አብዝቶ ተጨነቀ፡፡ በመጨረሻም ከወንድሜ ጋር ለዑምራ እንድሄድ መከረኝ፡፡ “ሂጂና በተከበረው የአላህ ቤት አጠገብ ብሶትሽን ተናገሪ፤ የውስጥሽን የውስጥ አዋቂ ለሆነ ጌታ ተንፍሺ” አለኝ፡፡ 

ዑምራ ሄድኩኝ፡፡ የአላህ ቤት ከዕባ ፊት ቁጭ ብዬ ረጅም ዱዓ አደረግኩ፡፡ ለርሱ የውስጥ ስሜቴን ሁሉ አንሾካሸኩ፡፡ አለቀስኩ፤ ፈረጄን ያቀርብልኝ ዘንድ ተማፀንኩት፡፡

≅ የሆነ ቀን ሱንና ከሰገድኩ በኋላ ጥቂት ቁጭ አልኩ፡፡ ከኋላዬ አንዲት ሴት ባማረ ድምጽ ቁርኣንን ታነባለች። “የአላህ ችሮታ ብዙ ነው።” የሚል ትርጉም ያለውን የቁርኣን አንቀጽ ስታነብ ቀልቤ በተለየ መልኩ ወደዚያ ተሳበ፡፡ በቁርኣን ውስጥ የዚህ ዓይነት አንቀፅ ስለመኖሩ ገረመኝ፡፡ አላህ በችሮታው ያስበኝ ዘንድ ተማፀንኩት፡፡ 

ሴትዮዋ አየችኝ፡፡ ምን እንደሆንኩ ጠየቀችኝ፡፡ ሁኔታዬን ነገርኳት፡፡ “አብሽሪ” አለችኝ “አብሽሪ አላህም ያሰብሽውን ይሰጥሻል፤ ኢን ሻኣላህ ደስም ይልሻል” አለችኝ፡፡

≅ ዑምራውን አጠናቅቄ ተመለስኩ፡፡ ድንገት የረጅም ጊዜ ጓደኛዬንና ባሏን በአይሮፕላን ማረፊያው አገኘኋቸው፡፡ የባሏን ጓደኛ ለመቀበል እየጠበቁ ነበር፡፡ ሰላምታ አቅርቤላቸው ትንሽ እንዳወጋን ጓደኛቸው ደረሰና ተሰነባበትን፡፡ ወዲያው አባቴ ደርሶ ተቀበለኝ፡፡

ጥቂት ቀናት አለፉ፡፡ አሁን ከበፊቱ በተሻለ ልቤ በመጠኑ ሰክኗል፡፡ ዱዓዬን አላቋረጥኩም፡፡

የሆነ ቀን ያች ጓደኛዬ ደወለችልኝ ያን ቀን ያየኝ የባሏ ጓደኛ ለትዳር እንዳሰበኝ ነገረችኝ፡፡ በአንድ ቀን እይታ እንዴት ሊሆን ይችላል ብዬ ተገረምኩ፡፡ ግና ለአላህ ምን ይሳነዋል!!፡፡ 

በእውነቱ የማይታሰብ ነገር ሆነብኝ፤ ማመን አቃተኝ፡፡ እሱ ግን የምሩን ነበር፡፡ ስለኔ ሁሉን ነገር ከጓደኛዬ ከሰማ በኋላ አላንገራገረም፡፡ ወደ ቤተሰቦቼ ሽማግሌ ላከ፡፡ ደስ አለኝ፡፡ ተስፋዬ ለመለመ፡፡ ወዜ ተመለሰ፡፡ ስሜቴ ታደሰ፡፡

በመጨረሻም አገባሁ። ጥሩ አፍቃሪ፣ መልካምና ደጋፊ፣ አዛኝና አሳቢ ባል … አላህ ሰጠኝ። ለኔም ለወላጆቹም ጥሩ ሰው ነበር፡፡

ካገባሁ ቀናት ሄዱ፣ ሁለትና ሶስት ወራት ተተኩ፡፡ ሌላ ሀሳብ አስጨነቀኝ፡፡ የእርግዝና ምልክት ናፈቀኝ፡፡ ግና እስካሁን ምንም አላስተዋልኩም፡፡ ሲበዛ አሳሰበኝ፡፡ እንቅልፍ አጣሁ፡፡

መመርመር እንደምፈልግ ለባሌ ነገርኩት፡፡ ወደ ሀኪም ቤት ሄድን፡፡ ጥቂት ቆይተን ለውጤቱ ተጠራን፡፡ ልቤ መምታቱን ጨመረ፡፡ ገና እንደገባሁ “መዳም መብሩክ!” አለችኝ ሀኪሟ፡፡

አርግዤ ነበር፡፡ ሱብሐነላህ! ለዚህ ብስራት ነበር እንዴ አላህ እዚህ ድረስ ያመጣኝ አልኩ፡፡

የእርግዝና ጊዜዬ ሰላማዊ ነበር፡፡ ግና የእድሜዬ መግፋት መጠነኛ ተጽእኖ ነበረው፡፡ ሆዴ እያደገ ሲመጣ ሰውነቴ ከበደኝ፡፡ እንደምንም የድካሙ ወራት አለፈ፡፡ የምጡ ቀን ደረሰ፡፡ በቀዶ ጥገና ነበር የወለድኩት፡፡ ከተሰጠኝ ሰመመን ስነቃ ቤተሰቦቼና ባለቤቴ ዙርያዬ ተሰብስበዋል፡፡ ይስቃሉ፣ ይጫወታሉ፡፡

“ምን ወለድኩ?” አልኳቸው ያለሁበትን ሁኔታ እያስታወስኩ፡፡

የተመካከሩ ነበር የሚመስለው፡፡ አንድ ላይ ሆነው ነበር ሰርፕራይዝ ያደረጉኝ “ወንድ እና ሴት!” አሉኝ፡፡ መንታ!!፡፡ የኔን መንቃት ሲጠብቅ የነበረው ባሌ በደስታ ተፍነከነከ፡፡ እኔንም ሀሴት የምሆነውን አሳጣኝ፡፡ ብችል ተነስቼ በዘለልኩ፡፡ ቁስሌ ገና እርጥብ ነው፡፡ ሱጁድም ራቀኝ፡፡ በተኛሁበት እንባዬ በሁለቱም ጉንጮቼ በኩል ዝም ብሎ ሲፈስ ይታወቀኛል፡፡ በትኩስ እንባ ፊቴ ታጠበ፡፡ ምስጋናዬን ያወጣሁበት ቃል እሱ ነበር፡፡ 

  የሚለውን የቁርኣን አንቀጽ አስታወስኩ፡፡ ስለ አላህ አሰብኩና በሀሳብ ርቄ ሄድኩ፡፡ የሱ ሥራ አብዝቶ ገረመኝ፡፡ እኛ ተስፋ እንቆርጣለን እንጂ እሱ ያዘጋጀልን ነገር አለ፡፡ እኛው ሁለት ልብ ሆነን ተቸገርን እንጂ በርግጠኝነት በአንድ ሆነን ልብ ይሰጠናል ብለን ብንለምነው ይሰጠናል፡፡ 

እኛው እንቸኩላለን እንጂ እሱ ለሁሉም ነገር መላና መፍትሄ አለው፤ ለሁሉም ነገር ምክንያትና ጊዜ አለው፡፡ ለአላህ ውሳኔ መታገስና ፈረጃውን መጠበቅ ትልቅ ዒባዳ ነው፡፡ 

እንኳን እኛ ነቢዩ ዘከርያም በልጅ እጦት ተፈትነዋል፡፡ “ጌታዬ ሆይ ብቻዬን አትተወኝ!!” ሲሉ ነበር ዱዓ ያደረጉት፡፡ 

ኢን ሻኣላህ ፈጣሪሽ ያሰብሽውን ይሰጥሻል፤ አንቺም አንድ ቀን ደስ ይልሻል፡፡

📚 “ቂሶሱን ሚነል ዋቂዕ” ከተሰኘ መጽሐፍ የተወሰደ፡፡ 

☑️ ተስፋ የቆረጡ ተስፋቸው ይለመልም ዘንድ እባክዎ ሼር ያድርጉ።

Send as a message
Share on my page
Share in the group
amrela nuri shared a
Translation is not possible.

ሙዓዊያ እና ዐሊይ ረዲየላሁ ዐንሁማ በተጋጩ ግዜ ሁለት

ኢስላማዊ ስረወ መንግስት ተመሰረተ የሮሙ ንጉስ ይህን ሰምቶ

እንዲህ ሲል ደብዳቤ ፃፈ።

<<ከሮም ንጉሰ ነገስት ለ ሙስሊሞች መሪ ሙዐዊያ አቡ ሱፍያን!!

ባንተ እና በዐሊይ መካከል የተከሰተውን ግጭት

ሰምተናል።ስለዚህም ለሙስሊሞች መሪ አንተ መሆን

እንዳለብህም ስለምናምን አንተ ፍቃድህ ከሆነ የዐሊይን ጭንቅላት

ቀንጥሶ የሚያመጣልህን ወታደር ልላክልህ>>

ይህ ደብዳቤ ሙዐዊያ ጋር እንደደረሰም ሙዓዊያም

<<ከሙዓዊያ ለሮም መሪ!!! ሁለት ወንድማማቾች ስለተጣሉ

አንተ ምን አገባህ? አፍህን የማትዘጋ ከሆነ ጅማሬው እኔ ጋ የሆነ

እና ፍፃሜው አንተ ጋ የሆነ ሰራዊት ልኬ አንገትህን በማስቀንጠስ

ለዐሊይ በስጦታ መልኩ አበረክትለታለሁ>>

#ይህ_ትክክለኛ_ሙስሊሞች_ሳለን_ነው

_____

___

ካሊድ ኢብን ወሊድ ለፐርሺያው ንጉሰ ነገስት እንዲህ ሲል

ደብዳቤ ፃፈለት

<<ስለም ትድናለህ። እንቢ ያልክ እንደሆን ግን፤ እናንተ ህይወትን

የምትወዱትን ያህል ሞትን የሚወዱ ሰራዊቶችን ይዤልህ

እመጣለሁ።>>

ንጉሱ ይህን ደብዳቤ ካነበበ በኋላ የቻይናውን ንጉስ የጦር እርዳታ

ሊለምነው ደብዳቤ ፃፈለት።

የቻይናውም ንጉስ እንዲህ ሲል ደብዳቤ መልሶ ላከለት።

<<ንጉስ ሆይ! ተራራን እንኳን ለመናድ ካሰቡ ምንም

ከማያግዳቸው ወታደሮች ጋር ለመጋፈጥ አቅሙ ስለሌለኝ

ጥያቄህን መፈፀም አልችልም።>>

# ምን_ያህል_ሀያላን_እንደነበርን_ተመልከቱ

_____

____

በደውለቱል ዑስማኒያ የአገዛዝ ዘመን የሙስሊም ወታደሮች የጦር

መርከቦቻቸውን ይዘው በአውሮፓ ደሴቶች ሲያልፉ በአከባቢው ያሉ

አብያተ ክርስትያናት በሙሉ ሙስሊሞች መጥተው ፈትህ

እንዳያደርጉ በመፍራት ከበሮ ከመምታት እና ምንም አይነት ድምፅ

ከማሰማት ይቆጠቡ ነበር።

#ያኔ_ጀግና_ሳለን

_____

____

በደውለቱል ኡስማኒያ የአገዛዝ ዘመን በያንዳንዴ ቤት ደጅ ላይ

ሁለት የበር ማንኳኩያዎች ይኖራሉ። አንዱ ትልቅ ሲሆን አንዱ ትንሽ

ነው። በትልቀኛው ከተንኳኳ አንኳኪው ወንድ ነው'ና በሩን ሊከፍት

ሚመጣው ወንድ ይሆናል። ነገር ግን በትንሸኛዋ ከተንኳኳ

አንኳኪዋ ሴት መሆኗ ስለሚታወቅ ሴት ትከፍትላታለች።

በዚያ ምርጥ ዘመን አንድ ቤት ውስጥ ሰው ከታመመ ደጅ ላይ

ቀይ አበባ ይንጠለጠል ነበር። ያን አበባ የተመለከቱ ሰዎች ሁሉ

እዝያ ቤት በሽተኛ መኖሩን ስለሚያውቁ በበሩ ሲያልፉ ድምፃቸውን

ዝቅ ያደርጉ ነበር።

#ሹፍ_ምን_እንመስል_እንደነበር !!!

_____

_

ግዜው ሰላሁዱን አል አዩቢ በይተል መቅዲስን ባስመለሰበት ግዜ

ነበር። እና ጦርነቱ ነገውን ሊጀመር ማታ ላይ የጦር መሪው

ሰላሁዲን የወታደሮቹን ድንኳን እየዞረ ሲያዳምጥ፤ ግማሹ ለይል

ይሰግዳል፣ ሌላው ቁርአን ይቀራል፣ የተቀሩት ደግሞ ይዘክራሉ።

ግን ድንገት በሆነ ድንኳን አጠገብ ሲያልፍ በድንኳኑ ውስጥ ያሉት

ሁሉም ተኝተው ነበር። ይህን ግዜ፦"በዚህች ድንኳን አዳሪዎች

ምክንያት ልንሸነፍ እንችላለን" ብሎ አለፈ።

#ማንተኛበት_ዘመን

_____

___

ቀደምት ዑለማኦች በሶስት ነገራት አደራ ይባባሉ ነበር።

1፦ሰውዬው በሱ እና በአላህ መካከል ያለውን ግንኙነት ካሳመረ፤

በሱ እና በሌሎች መካከል ያለው ግንኙነት ያምርለታል።

2፦ሰውዬው ሚስጥራዊ ተግባሩን ካሳመረ አላህ ይፋዊ ተግባሩን

ያሳምርለታል።

3፦ሰውዬው የአኪራው ጉዳይ ካስጨነቀው አላህ የዱንያውንም

የአኪራውንም ጉዳይ ያግራራለታል።

_____

_

#ትልቁ_ኪሳራ_ማለት_ይህ_ነው

ጀነት ስፋቷ የምድርን እና የሰማያትን ያህል ሁና ላንተ በሷ ቦታ

ሳይኖርህ ሲቀር...ትልቅ ኪሳራ ነው።

በእለታዊ ፕሮግራምህ ውስጥ ቁርአንን መቅራት ካልተካተተ ትልቅ

ኪሳራ ነው።

ይህን ፅሁፍ በማሰራጨት ጓደኛህን እንድታነቃው ይከጀላል!

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
amrela nuri shared a
Translation is not possible.

ከአንተ በሥተቀር በሀቅ የሚመለክ አምላክ የሌለን አላህ ሆይ

እንደ ቅጠል የሚረግፉ የፍልሥጤም ህፃኖችን አንተ ፈረጃዉን አቅርብላቸዉ የሞቱትንም ለቤተሠቦቻቸዉ ሸፈዓ አድርግላቸዉ።

ጌታችን ሆይ   በአለም ላይ ንፁሀን ደም  የጨቀየችን ምድር አንተ ሠላም አዉርድ የበደለኞችን ግፍ በቃ በለን ሙስሊሞችን የበላይ አድርጋቸው።

🤲🤲🇵🇸🇵🇸

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
amrela nuri shared a
Translation is not possible.

እናትና ልጅ በጠባቧ ክፍላቸው ውስጥ ተቀምጠዋል።

"እማ ርቦኛል" አለ ዩሱፍ ሆዱን እያሻሸ።

"ሀቢቢ ትንሽ ጠብቀኝ ቲማቲም ስልስ እሰራልሃለሁ" አለች እናት ፀጉሩን እያሻሸች።

ቤት ውስጥ የሚላስ የሚቀመስ ባለመኖሩ የዩሱፍን ርሐብ ለማስታገስ ሁለት የቲማቲም ዘለላዎችን ፍለጋ ከቤት ወጣሁ። በበር በኩል አጮለቅኩና እስክመለስ በሩን እንዲዘጋ ነገርኩትና ወደ ጎረቤታችን ቤት አቀናሁ። ደጋግሜ አንኳኳሁ። መልስ የሚሰጠኝ አላገኘሁም። ከመንገዱ ማዶ ወደሚገኘው ወደ ኡሙ ሚቅዳድ ቤት አመራሁ።

አንኳኩቼ ገባሁ። እንዴት ነሽ ልጆችሽስ ብዬ ሰላምታን አቀረብኩላት።

"አልሀምዱሊላህ ደህና ነን አላህ ይጠብቀን" ብላ መለሰችልኝ።

እያንዳንዱ ሰከንድ የመጨረሻ ሊሆን ይችላልና እኛ ፍልስጤማዊያን ጦርነት ውስጥ ስንሆን እንዲህ ነን ብዙ አንናገርም።

"ባለቤቴ ውሎ አዳሩ ሆስፒታል ሆኗል። ጦርነቱ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ ወደ ቤት አልተመለሰም። አልሐምዱሊላህ" አልኩና ቲማቲም ካላት እንድትሰጠኝ ጠየቅኳት። በፌስታል ቋጥራ ያቀበለችኝን ቲማቲም ይዤ ልወጣ ስል "ሁኔታዎች ከባድ ሆነዋል በዱዓ እንተዋወስ" አለችኝ።

"በአላህ እርዳታ ይህ ሁሉ ያልፋል ኢንሻ አላህ..." እያልኳት ገና ንግግሬን ሳልጨርስ ከባድ ፍንዳታ ተሰማ። በጥቁር ደመና አየሩን ተሸፈነ። አካባቢው በአቧራ ተሞላ። አእምሮዬ የዩሱፍን ስም አቃጨለ። ከራሴ ጋር እየታገልኩ ወደ ጎዳናው ሮጥኩ። ሁሉም ይጮኻል።

ዩሱፍን አይታችዋል..? እዚህ አካባቢ አንድ ትንሽ ፍሪዝ የሆነ ልጅ አጊኝታችኋል? እያልኩ ጮኽኩ። መልስ የሰጠኝ ማንም አልነበረም። በአንቡላንስ ተጭኜ ሄድኩ። የመኪናው በር ሲዘጋ በዩሱፍ ላይ የዘጋሁት በር ታወሰኝ።

እየተብሰለሰልኩ አሽ-ሺፋእ ሆስፒታል ደረስኩ። ዩሱፍ....የሱፍ.... ብዬ ተጣራሁ። ለአላፊ አግዳሚው የ7 አመት ቆንጅዬ ልጄን አይታቹታልን? እያልኩ ጠየቅኩ።

የዓይኔ ማረፍያ ባለጥቅልል ፀጉሩ ጥቃቱ ፊቱን ከማበላሸቱ በፊት ቆንጆ ምስሉን በአእምሮዬ ሳልኩ። ፍርስራሽ አቧራ ከሰውነቱ ጋር ተጣብቆ በደም ተጨማልቆ አልጋ ላይ ተንጋሎ አገኘሁት። ዩሱፍ በባዶ ሆዱ ጌታውን ተገናኘ።

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
amrela nuri shared a
Translation is not possible.

በፍልስጤሟ ምድር ጋዛ ወራሪዋ ከሰማይ በወረወረችው የድሮን እሳት ቤታቸው ዶግ አመድ ሆኖ በላያቸው ላይ ተናደ። አስራ አንድ ሙሉ ቤተሰብ ከፍርስራሹ መሐል ተጋደመ። በቦታው የደረሱት የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች ቆፍረውና ቧጠው ሲያወጧቸው ሁሉም ሞተው እናት ነፍሷ ከጀሰዷ ሊላቀቅ የመጨረሻ እስትንፋሷ ላይ ነበረች።

በዝግታ አይኗን እያስለመለመች ታቃስታለች። በሆዷ የታቀፈችው ፅንስ በህይወት ይቆይ ዘንድ እግሯን ከፈት ልጇን ደገፍ አድርጋ ተንጋላለች። ሆስፒታል እንደደረሰች እስትንፋሷ ተቋርጦ ጌታዋን ስትገናኝ ፅንሱ ግን በህይወት ነበር። ዶክተሮች በአላህ ፈቃድ የልጁን ህይወት ማትረፍ ቻሉ። አስራ አንድ ሙሉ ቤተሰቦቹን ባጣበት ቅፅበት እርሱ ይህቺን አለም ተቀላቀለ። መገን የአላህዬ ነገር።

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group