UMMA TOKEN INVESTOR

Translation is not possible.

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በኾነው፡፡

«ዘመዴ የሆነችን ሴት ማግባት በሸሪዓው እንዴት ይታያል?።» ብሎ ለጠየቀ ሰው የተሰጠ ምላሽ።

በአንዳንድ ብሔረ-ሰቦች ዘንድ በራሳቸው ልምድና ባህል መነሻነት፣ሸሪዓ የፈቀደውንና በቁርዓን ከተከለከሉት ዝርዝር ውስጥ የማይካተተውን የዘመዳሞችን መጋባት ከመቃወም አልፎ፣ጭራሽ የተጋቡትን እስከማፋታት ድረስ የሚደርስ እጅግ አደገኛና አላህ ሀላል ያደረገውን እነርሱ ሀራም ለማድረግ የሚዳዳቸው፣አዋቂ ነኝ የሚሉ ግን ያለማወቅን ኩታ ያጣፉ የጎሳ መሪዎች በብዛት ይስተዋላሉ።በመሰረቱ ኒካህን የደነገገልን አላህ፣ሸሪዓውን ያብራሩልን ነብይም፣አንድ ሰው ሊያገባቸው እርም የሚሆኑበትን ሴቶች ዝርዝር ነግረውናል።ከተዘረዘሩት ውጭ የተቀረው ሁሉ መስፈርቱ ተጠብቆ፣ሸሪዓው እስከፈቀደልህ ቁጥር ድረስ ለማግባት ሀላል ነው።ነገር ግን እኛ እንደ ማ/ሰብ ጭራሽ በአያት ኣሊያም በቅድመ-አያት የሚገናኙትን ብቻ ሳይሆን፣በሰባተኛ አያትም ከተገናኙ መጋባታቸውን ይቃወማሉ።ነገር ግን በሸሪዓችን የአጎትን ልጅ ወይም የአክስትን ልጅ ማግባት እንደሚቻል በቁርዓንም ሆነ በሐዲስ ተነግሮ እናገኛለን፣ተተግብሯልም።ነቢዩ ለአሊይ ልጃቸውን ፋጢማን ድረውታል።በሌላ በኩል የአጎታቸው የአባስ ልጅ መሆኑን አትርሱ።ለራሳቸው ዘይነብ ቢንት ጀሕሽን አግብተዋል።በአባት የአክስታቸው የኡመይማ ቢንት አብዲልሙጠሊብ ልጅ ናት።ቁርዓንም በግልፅ ለነቢዪ የሚከተለውን ብሏቸዋል፦ «አንተ ነቢዩ ሆይ! እኛ እነዚያን መህሮቻቸውን የሰጠሃቸውን ሚስቶችህን፣ አላህ ባንተ ላይ ከመለሰልህም እነዚያን እጅህ የጨበጠቻቸውን ምርኮኞች፣ እነዚያንም ከአንተ ጋር የተሰደዱትን የአጎትህን ሴቶች ልጆች፣ የአክስቶችህንም ሴቶች ልጆች፣ የየሹማህንም(በእናትህ በኩል አጎትህ)ሴቶች ልጆች፣ የየሹሜዎችህንም(በእናትህ በኩል አክስትህ) ሴቶች ልጆች (ማግባትን) ለአንተ ፈቅደንልሃል፡፡» አል-አሕዛብ : 50።እኛ ግን ብዙም ስላልተለመደ፣አንድ ሰው የአጎቱን ልጅ ቢያገባ ዝምድና ቆረጠ ብለን መደንፋት ነው ስራችን።ለመሆኑ ይሄንን አንቀፅ አስተውለነው እናውቅ ይሆን?፦

«ከሃይማኖት አላህ በእርሱ ያልፈቀደውን ለእነርሱ የደነገጉ ተጋሪዎች ለእነርሱ አልሏቸውን? የፍርዱ ቃል ባልነበረ ኖሮ በመካከላቸው (አሁን) በተፈረደ ነበር፡፡ በደለኞችም ለእነርሱ አሳማሚ ቅጣት በእርግጥ አልላቸው፡፡» አሽ-ሹራ : 21።

እንግዲህ የፈቀድኩትን አይፈቀድም የሚሉ ወየውላቸው እያለን ነው አላህ። ያረብ ከቁጣህ በአንተ እንጠበቃለን።

ኢንሻአላህ በቀጣይ ፖስት ሙሉ በሙሉ ሀራም የሆኑ፣ነገር ግን እንደ ሀላል የሚታዩና የተለመዱ የጋብቻ አይነቶችን በወፍ-በረር እናያለን።

አቡ አብዲላህ አልወራቢይ፣

አልመዲነቱል-ሙነወረህ፣

ጁማደልዑላ 7/1445 ዓ.ሂ።

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በኾነው፡፡

ወላሂ በጣም ልቤን ከሚሰብሩኝ ነገሮች አንዱ ተቸግረው የሰው እጅ የሚያዩ ሰዎችን ማየት ነው።በተለይ ደግሞ ለልጆቻቸው ዳቦ ፍለጋ የወጡ ወላጆችና በሕመም የሚሰቃዩና ለሕክምና የሚውል ገንዘብ የሚጠይቁ ወገኖች ሲኾኑ ከባድ ነው።

የትም አግኟቸው ከያዛችሁት ትንሽዬም ቢሆን ጣል እያደረጋችሁ እለፉ።

ደግሞ በጥሩ ኒያ 5 ብርም ቢሆን ሞባይልህን ተጠቅመህ በአካውንት አስተላልፍ።ብዙዎቻችን ምን ልትፈይድ? እንል ይሆናል።ችግሩ የምንሰጠውን ነገር ዋጋ ማሳጣታችን ነው። ብዙ 5 ብሮች ሲደማመሩ ለተመፅዋች ቁም ነገር ይሆናሉ።የምንሰጠው ለሐብታሙ አላህ ነው።ያ ማለት እሱ ዘንድ ቀና እሳቤና ኢኽላስ ነው ዋናው ነገር።ይሄ ሲባል አላህ ለቀቅ አድርጎልን እያለ በየ ቦታው ሲጠየቅ 100 ብር እንስጥ ማለት አይደለም። 1ብርም እንኳን ከሆነ መስጠት የምትችለው እሷኑ ስጥ ነው።ነቢዩ ከሰደቃ ሁሉ በላጩ የቱ ነው? ተብለው ሲጠየቁ«ደሃ ሰው እየተቸገረም ቢሆን የአቅሚቲ የሚሰጠው ነው።»ብለዋል።

በሌላ ዘገባ ላይ «አንድ ዲርሀም አንድ መቶ ሺ ድርሀምን ቀደመች።»ኣሉ፣ እንዴታ?፣ ሲባሉ፦ «አንድ ሰው ሁለት ዲርሀሞች ነበሩት፣አንዷን ሰደቃ ሰጠ።ሌላ ግለ-ሰብ ግን ከብዙ ንብረቱ አንድ መቶ ሺህ ድርሀም ሰጠ።»ኣሉ።የመጀመሪያው ግማሽ ካፒታሉን ነው የሰጠው፣ሁለተኛው ግን ከብዙ ሀብቱ ነው መቶ ሺህ የሰጠውና።

ሰደቃን አትናቁ።በየ ቦታው ጣል የምታደርጋትን፣በተመፅዋች እጅ ከመድረሷ አስቀድሞ አላህ በቀኝ እጁ ተቀብሎ ያፏፏታል፣የቂያማ ቀንም እጥፍ ድርብ አድርጎ ለባለቤቷ ያቀርባታል ብለዋል።ሰርተን የረሳናቸው ብዙ ወንጀሎች ስላሉብን፣ሰርተን የምንረሳቸው ነገር ግን አላህ የማይረሳቸው ብዙ መልካም ስራዎች ያስፈልጉናል።ሙዕሚን ሁሌም የሚቆጥረው ወንጀሉን ነው፣ሳያውቅ ተጠራቅሞ እንዳያጠፋው በመፍራት። መልካም ስራህማ ልክ ስትሰራው በማይረሳው በጌታህ መዝገብ ስለሰፈረ አታጣውም አያሳስብህ።

ሰደቃ ተቆጥሮ የማያልቅ ትሩፋት ኣለው።

ኻቲማህ እንዲስተካከል፣ከአደጋ እንድትጠበቅ፣ሀጃህ እንዲወጣ፣ከአላህ ቁጣ እንድትድን፣ሐብታም እንድትሆን፣ከበሽታ እንድትፈወስ...በቃ ምን አለፋህ ትሩፋቱ ተዘርዝሮ አያልቅም ሀቂቃ።

አላህ ሆይ ሪዝቃችንን በሐላል መንገድ አስፋልን፣የሰጠሀንን ሐብትም በውዴታህ የሚያወጡ ጀግኖች አድርገን።በሱም ዲንህን ለማስፋፋት፣ባሮችህን ለመንከባከብ ሰበብ አድርገን።

መስጠት ኣኺራንና ጀነትን ለሚመኝ ሙዕሚን ቀርቶ ኢ-አማኒያን ራሱ በሕይወታችሁ ትልቁን ሐሴት የሚሰጣችሁ ነገር ምንድነው? ሲባሉ፣ «የሰዎችን ችግር ፈትቼ ሲደሰቱ ማየት» ሲሉ መስማት የተለመደ ነው።

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.
image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

ኢትዮጲያ በፍልስጤም ጉዳይ አስቸኳይ ምግብ ይግባ አይግባ ለሚለው ውሳኔ በድምፀ ተዓቅቦ አሳለፈች !

ተመድ በጠራው ስብሰባ ላይ ሀገራችን ኢትዮጲያ የፍልስጤም ጉዳይን በተመለከተ 120 ሀገራት ምግብ በአስቸኳይ ይግባ ብለው ድምፅ ሲሰጡ ኢትዮጲያ በዝምታ አልፋዋለች :-D

ባለፈው ጁሙዓ ፍልስጤምን እና እስራኤልን በተመለከተ በተባበሩት መንግስት በተመድ ስብሰባ ተደርጎ ነበር

የሰብዓዊ ተኩስ አቁም ጥሪ የቀረበበት የውሳኔ ሀሳቡ ፦

- በ120 ድጋፍ፣

- በ14 ተቃውሞ

- በ45 ድምጸ ተአቅቦ በአብላጫ ድምፅ ጸድቋል።

በዚህም መሰረት ተመድ በጋዛ አስቸኳይ የሰብዓዊ ተኩስ አቁም እንዲደረግ ውሳኔ አሳልፏል።

የውሳኔ ሃሳቡን ከተቃወሙት ውስጥ አሜሪካ ፣ እራሷ እስራኤል ፣ ሃንጋሪ ፣ ኦስትሪያ ይገኙበታል።

ድምፅ ተአቅቦ ካደረጉት መካከል ደግሞ ሀገራችን #ኢትዮጵያ ፣ ጀርመን ፣ ካናዳ፣ ግሪክ፣ ፊንላንድ፣ ዴንማርክ፣ ስውዲን፣ ኢራቅ፣ ጃፓን፣ ጣልያን፣ ሕንድ ፣ዩናይትድ ኪንግደም፣ ዩክሬን፣ ቱኒዝያ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ዛምቢያ ይገኙበታል።

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

To Day Best Photo

Send as a message
Share on my page
Share in the group