UMMA TOKEN INVESTOR

6 уйӑх Куҫарас
Çĕнĕ çулахне йывăçлăх

አተህያቱ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

ነብያችን”ﷺ” በለይለቱል ኢስራ ወል ሚዕራጅ ጉዞዋቸዉ ወቅት አላህ ሲገናኙ እንዲህ ነበር ያሉት’’

አተህያቱ ሊላሂ ወሰለዋቱ ፤ ወጠይባ’’ التَّحِيَّاتُ لِلّٰهِ وَالصَّلَوَاتُ وَالطَّيِّبَاتُ،

ማለትም ’’ክብር ሁሉ ለአላህ ነዉ፤ ሶላቶች እና መልካም ተግባራቶችም ለአላህ ሲባል የሚደረጉ ናቸዉ" አሉ።

አላህም መለሰላቸዉ፦ ’’አሰላሙ አለይከ አዩሃ ነቢዩ ወራህመቱላሂ ወበረካቱ" اَلسَّلَامُ عَلَيْكَ أَيُّهَا النَّبِيُّ وَرَحْمَةُ اللهِ وَبَرَكَاتُهُ، ማለትም ’’አንተ ነብይ ሆይ! ሰላም በአንተ ላይ ይዉረድ፡፡ የአላህ እዝነትና ዉዴታም ይስፈንብህ"

ነብያችን”ﷺ” እንዲህ በማለት መለሱ፦ "’አሰላሙ አለይና

ወዐላ ዒባዲላሂ አሷሊሒይን’’´ اَلسَّلَامُ عَلَيْنَا وَ عَلٰى عِبَادِ اللهِ الصَّالِحِيْنَ، ማለትም "በእኛ እና በአላህ ቅን ባሪያዎችም

ላይ ሰላም ይስፈን"

ይህንን የሰላምታ ቃለ-ምልልስ እየሰሙ የነበሩ መላእክቶች እንዲህ አሉ፦

’’አሽሃዱ አን ላ ኢላሃ ኢለላህ ወአሽሃዱ አነ ሙሃመደን ዐብዱሁ ወረሱሉሁ’’ أَشْهَدُ أَنْ لَا إِلٰهَ إِلَّا اللهُ، وَأَشْهَدُ أَنَّ مُحَمَّدًا عَبْدُهُ وَ رَسُوْلُهُ ማለትም "ከአላህ ዉጪ ሌላ አምላክ እንደሌለ እመሰክራለሁ፤ ሙሐመድም የአላህ ባሪያና መልእክተኛዉ እነደሆነ አመሰክራለሁ"፡፡

እንግዲህ ይህ ነዉ በጌታችንና በነብያችን”ﷺ” መካክል የተደረገዉ የሰላምታ ልዉዉጥ፡፡ጥበብ የተሞላበት የነብያችን”ﷺ” ኡመትን ሁሉ ያካለለ ቅዱስ ንግግር ነዉ፡፡ ልብ ብላችሁ ከሆነ አላህ ’’አንተ ነብይ ሆይ! ሰላም በአንተ ላይ ይዉረድ፡፡ የአላህ እዝነትና ዉዴታም ይስፈንብህ" ሲላቸዉ፤ እርሳቸው "በእኛ እና በአላህ ቅን ባሪያዎችም ላይ ሰላም ይስፈን" ነበር ያሉት፤ ነቢያችን በእኔ ላይ ሰላም ይስፈን አላሉም ይልቁንስ በእኛ የሚለዉን ቃል ነዉ የተጠቀሙት፡፡

ትርጉሙን የማታዉቁ ሰዎች ከአሁን በኃላ ኢንሻላህ እንዲህ አይነት ስሜት ይኖራችኋል ብዬ አስባለው።

✍️ከኡሥታዝ ወሒድ ዐቃቢ ኢሥላም

የበለጠ ለማወቅ

https://t.me/tiriyachen

ወሰላሙ አለይኩም

Хыпар пек ярас
Ман тетелӗ питра пайлас
Ушкӑнта пайлас
6 уйӑх Куҫарас
Çĕнĕ çулахне йывăçлăх

እስራኤል የአል-ሺፋ ሆስፒታልን በዒላማ ውስጥ ያስገባችው ለምንድነው?

------

አፈንዲ ሙተቂ

------

በጋዛ ከተማ መሀል የሚገኘው "አል-ሺፋዕ" ሆስፒታል በዓለም ሚዲያ ስሙ በሰፊው እየተነሳ ነው። ይህም የሆነው እስራኤል "የሀማስ ኮማንድ ፖስት በሆስፒታሉ ውስጥ አለ" በሚል ማመካኛ የጦር ኃይሏን ወደ ሆስፒታሉ አስገብታና ታካሚዎችን፣ ሀኪሞችን፣ ሰራተኞችንና በሆስፒታሉ የተጠለሉ አንድ ሺህ ያህል ንጹሐን ሲቪሎችን እያንገላታች በመሆኑ ነው።

በእውነት ሆስፒታሉ የሃማስ ኮማንድ ፖስት ነውን?

-----

ስለሆስፒታሉ በጥልቀት የሚያውቁ የጋዛ ነዋሪዎችና በሆስፒታሉ ዙሪያ መረጃ ያሰባሰቡ ወገኖች የሀማስ ኮማንድ ፖስት በሆስፒታሉ ግቢ እንደሌለ መስክረዋል። እስራኤል ሆስፒታሉን የምትደበድበው እና ዓለም አቀፍ ህግን በተጻረረ ሁኔታ የጦር ኃይሏን ወደ ግቢው ያስገባችው በሚከተሉት ምክንያቶች ነው።

=> አል-ሺፋ ሆስፒታል በጋዛ ካሉት ሆስፒታሎች ሁሉ ትልቁ ነው። በዕድሜውም ከአህሊ ዐረብ ሆስፒታል ቀጥሎ ሁለተኛው ነው። ሆስፒታሉ የተቋቋመው እስራኤል ከመመሥረቷ በፊት ነው። በመሆኑም በታሪካዊነቱ በፍልስጥኤም የአደራ አስተዳደር (Mandatory Palestine) ዘመን የነበረውን ሁኔታ ይመስክራል። እንግዲህ እስራኤል ታሪካዊነቱን ዋጋ ቢስ ለማድረግ ስትል ነው አል-ሺፋ ሆስፒታልን ድምጥማጡን ለማጥፋት የወሰነችው።

2. ሁለተኛው ምክንያት አሁን በጋዛ የቀረው መንግሥት እንደ ኮሚኒኬሽን ቢሮ የሚጠቀምባቸው ክፍሎች በሆስፒታሉ ህንጻ ላይ የሚገኙ መሆናቸው ነው። ይህ ቢሮ የእስራኤልን ወንጀሎች እያጋለጠ መሆኑ ይታወቃል። በመሆኑም እርሱን ጸጥ ለማድረግ ስትል ጦሯን ወደ ሆስፒታሉ አስገብታለች።

3. ከሁሉም በላይ ግን የፍልስጥኤም ጤና ሚኒስቴር የጋዛ ቅርንጫፍ በሆስፒታሉ ዋና ህንጻ ላይ የሚገኝ መሆኑ ነው ሆስፒታሉን የእስራኤል ዒላማ ያደረገው። እንደሚታወቀው የእስራኤል ጦር በየቀኑ በጋዛ የሚገድላቸውን ሲቪሎች (በተለይም ሕጻናት እና ሴቶች) መረጃ እያጠናቀረ በዓለም ዙሪያ የሚያሰራጨው ይህ የጤና ሚኒስቴር ቅርንጫፍ ነው። እርሱ የሚያሰራጫቸው መረጃዎች አስተማማኝ መሆናቸው በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት እና በሌሎች ዓለም አቀፍ ድርጅቶች ተረጋግጧል። በዚህም የተነሳ የጋዛው የጤና መምሪያ የሚሰጣቸውን መረጃዎች የሚሰብስቡ የዓለም አቀፍ ሚዲያ ሪፖርተሮች በሆስፒታሉ ግቢ መገኘታቸው የየዕለቱ ትእይንት ሆኗል።

እስራኤል በውጊያው መስክ የበላይነትን ብትይዝም በፕሮፓጋንዳው መስክ የትም መድረስ አልቻለችም። ከዓለም ሕዝብ አብዛኛው እጅ ጭካኔዋን በደንብ ተረድቷል። የእስራኤልን ጭካኔ እያጋለጡ ካሉት ትልቅ ተቋማት አንዱ በፍልስጥኤም ጤና ሚኒስቴር የጋዛው ቅርንጫፍ ነው። በመሆኑም የዚህን መስሪያ ቤት ሰራተኞች አንደበት ለመዝጋት ስትል በታንክና በብረት ለበስ ተሽከርካሪዎች ጭምር ወደ አል-ሺፋ ሆስፒታል ቅጽር-ግቢ ገብታለች።

-------

የጋዛው ጭፍጨፋና ጦርነት አርባኛ ቀኑን ይዟል። እስራኤልም በዘር ማጥፋት ዘመቻዋ ቀጥላለች። ሀማስም ሮኬቶቹን መተኮሱን ቀጥሏል። የእስራኤል እብሪት የት እንደሚያደርሳት አናውቅም። ፈጣሪ የፍልስጥኤምን ሕዝብ ከገጠመው ፈተና እንዲታደገው እንማጸናለን።

------

አፈንዲ ሙተቂ

ህዳር 5/2016

Хыпар пек ярас
Ман тетелӗ питра пайлас
Ушкӑнта пайлас
Aziza Berhan Ӳкерчӗке улӑштарнӑ
6 уйӑх
Çĕнĕ çулахне йывăçлăх

image
Хыпар пек ярас
Ман тетелӗ питра пайлас
Ушкӑнта пайлас
Aziza Berhan пайларӗ
7 уйӑх Куҫарас
Çĕнĕ çулахне йывăçлăх

ምርጥ ተውበት !

የ ታላቁ አሊም ማሊክ ኢብን ዲናር የተውበት ታሪክ 🍃

 ማሊክ ኢብን ዲናር ህይወታቸውን በስካር በመጠጥ ነበር የጀመሩት፣ከዛም በአንድ ግዜ አግብተው ልጅ መውለድ ተመኙ አናም አገቡም አላህ 1ሴት ልጅ ሰጣቸው ስሟንም ፋጢማ አሏት። የዛኔ ልባቸው ወደ ኢማን እየተቃረበ መጣ ውጪ ይጠጡ የነበረውን ቤት መጠጣት ጀመሩ። ፋጢማንም ጭናቸው ላይ አድርገው ነበር የሚጠጡት፣አንድ ቀን ፋጢማ በ2 አመቷ እያለ መጠጡን ገፍታ ደፋችባቸው የዛኔ ይህ አላህ በፋጢማ ተው እያለኝ ነው ብለው አሰቡ፣ ከአመት በኃላም ፋጢማ 3አመት ሞላት ከዛም ፋጢማ ሞተች። ከዛም ድጋሚ እንደበፊቱ መጠጣት መስከር ጀመሩ፣ ታዲያ አንድ ቀን ሸይጧን ወሰወሰኝ አሉ ዛሬ ሰክረኸው የማታውቀውን ስካር ነው የምትሰከረው አለኝ እሺ ብየ መጠጥ መጠጣት ጀመርኩ በጣም ሰከሬ ወደኩ አሉ ። ከዚያም በህልሜ ቂያማ የቆመ መሰለኝ ፀሀይቱ ጠቁራለች፣ ሰወ ሁሉ አላህ ፊት ተሰብስቧል፣ባህሩ ይነዳል የሰው ሁላ ስም ሲጠራ ቆየና ማሊክ ኢብኑ ዲናር ና ለሂሳብ ትፈለጋለህ ተባልኩ ከዛም ትልቅ ዘንዶ ማሳደድ ጀመረኝ እሱን  ለመሸሽ ሰሮጥ አንድ ሽማግሌ አገኙሁ አግዘኝም አልኩት እኔ አቅሜ ደካማ ነው አለኝ ሰሮጥ የእሳት ጫፍ ላይ ደረስኩ፣ ዘንዶውን ፈርቼማ አሳት አልገባም ብየ ተመልሼ ሮጥኩ ድጋሚም ሽማግሌውን አገኙሁት አግዘኝም አልኩት አቅሜ ደካማ ነው እስቲ የምትድን ከሆነ ወደዛ ተራራ ሩጥ አለኝ። ከዚህም እየሮጥኩ እያለ  ከተራራው ላይ ህፃኖች ፋጢማ አባትሽን ዘንዶ ሊበላው ነው ሲሉ ሰማሁ ። ለካ በ 3 አመቷ የሞተች ልጅ አለችኝ ብየ ወደ ፋጢማ ሮጥኩ ፋጢማም ዘንዶውን ገፍታ ጣለችው። እኔም ልጄ ሆይ እስቲ ያ ዘንዶ ምንድነው የሚያባረኝ አልኳት እሷም ያ መጥፎ ስራህ ነው አለችኝ እሺ ያ ሽማግሌውስ ያ ጥሩ ስራህ ነው አለችኝ ጥሩ ስራህ ደካማ ሰለሆነ ከመጥፎ ስራህ ሊያስጥልህ አልቻለም አለችኝ። ከዛም 1የቁርአን አያ ቀራችልኝ።

"እነዛ ምእመናን ልባቸው ለአላህ ግሳፄ የሚፈራበት ግዜ አልደረሰምን?" የሚለውን አነበበችልኝ ። ልክ አኔም ከእንቅልፌ አዎ ግዜው ደርሷል አያልኩ እያለቀስኩ ተነሳሁ ሻወር ወሰድኩ ሱብሂ ወደ መስጂድም ሄድኩ። መስጂድም ኢማሙ ይህንኑ አያ እየቀሩት ነበር አልቅሼ ተመለስኩ ይሉናል ታላቁ ኢማም።

እኝህ ሰው ህዝቡን የሚያስተምሩ ታላቅ ኢማም ሆኑ። ሁሌም መስጂድ አንተ አላህን ያመፅክ ባሪያ ሆይ ወደ ጌታህ ተመለስ ይሉ ነበር።

‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌┄┅┅┄┅✶🌹✶┅┄┅

Хыпар пек ярас
Ман тетелӗ питра пайлас
Ушкӑнта пайлас
Aziza Berhan пайларӗ
Çĕнĕ çулахне йывăçлăх

ሙዓዊያ እና ዐሊይ ረዲየላሁ ዐንሁማ በተጋጩ ግዜ ሁለት

ኢስላማዊ ስረወ መንግስት ተመሰረተ የሮሙ ንጉስ ይህን ሰምቶ

እንዲህ ሲል ደብዳቤ ፃፈ።

<<ከሮም ንጉሰ ነገስት ለ ሙስሊሞች መሪ ሙዐዊያ አቡ ሱፍያን!!

ባንተ እና በዐሊይ መካከል የተከሰተውን ግጭት

ሰምተናል።ስለዚህም ለሙስሊሞች መሪ አንተ መሆን

እንዳለብህም ስለምናምን አንተ ፍቃድህ ከሆነ የዐሊይን ጭንቅላት

ቀንጥሶ የሚያመጣልህን ወታደር ልላክልህ>>

ይህ ደብዳቤ ሙዐዊያ ጋር እንደደረሰም ሙዓዊያም

<<ከሙዓዊያ ለሮም መሪ!!! ሁለት ወንድማማቾች ስለተጣሉ

አንተ ምን አገባህ? አፍህን የማትዘጋ ከሆነ ጅማሬው እኔ ጋ የሆነ

እና ፍፃሜው አንተ ጋ የሆነ ሰራዊት ልኬ አንገትህን በማስቀንጠስ

ለዐሊይ በስጦታ መልኩ አበረክትለታለሁ>>

#ይህ_ትክክለኛ_ሙስሊሞች_ሳለን_ነው

_____

___

ካሊድ ኢብን ወሊድ ለፐርሺያው ንጉሰ ነገስት እንዲህ ሲል

ደብዳቤ ፃፈለት

<<ስለም ትድናለህ። እንቢ ያልክ እንደሆን ግን፤ እናንተ ህይወትን

የምትወዱትን ያህል ሞትን የሚወዱ ሰራዊቶችን ይዤልህ

እመጣለሁ።>>

ንጉሱ ይህን ደብዳቤ ካነበበ በኋላ የቻይናውን ንጉስ የጦር እርዳታ

ሊለምነው ደብዳቤ ፃፈለት።

የቻይናውም ንጉስ እንዲህ ሲል ደብዳቤ መልሶ ላከለት።

<<ንጉስ ሆይ! ተራራን እንኳን ለመናድ ካሰቡ ምንም

ከማያግዳቸው ወታደሮች ጋር ለመጋፈጥ አቅሙ ስለሌለኝ

ጥያቄህን መፈፀም አልችልም።>>

# ምን_ያህል_ሀያላን_እንደነበርን_ተመልከቱ

_____

____

በደውለቱል ዑስማኒያ የአገዛዝ ዘመን የሙስሊም ወታደሮች የጦር

መርከቦቻቸውን ይዘው በአውሮፓ ደሴቶች ሲያልፉ በአከባቢው ያሉ

አብያተ ክርስትያናት በሙሉ ሙስሊሞች መጥተው ፈትህ

እንዳያደርጉ በመፍራት ከበሮ ከመምታት እና ምንም አይነት ድምፅ

ከማሰማት ይቆጠቡ ነበር።

#ያኔ_ጀግና_ሳለን

_____

____

በደውለቱል ኡስማኒያ የአገዛዝ ዘመን በያንዳንዴ ቤት ደጅ ላይ

ሁለት የበር ማንኳኩያዎች ይኖራሉ። አንዱ ትልቅ ሲሆን አንዱ ትንሽ

ነው። በትልቀኛው ከተንኳኳ አንኳኪው ወንድ ነው'ና በሩን ሊከፍት

ሚመጣው ወንድ ይሆናል። ነገር ግን በትንሸኛዋ ከተንኳኳ

አንኳኪዋ ሴት መሆኗ ስለሚታወቅ ሴት ትከፍትላታለች።

በዚያ ምርጥ ዘመን አንድ ቤት ውስጥ ሰው ከታመመ ደጅ ላይ

ቀይ አበባ ይንጠለጠል ነበር። ያን አበባ የተመለከቱ ሰዎች ሁሉ

እዝያ ቤት በሽተኛ መኖሩን ስለሚያውቁ በበሩ ሲያልፉ ድምፃቸውን

ዝቅ ያደርጉ ነበር።

#ሹፍ_ምን_እንመስል_እንደነበር !!!

_____

_

ግዜው ሰላሁዱን አል አዩቢ በይተል መቅዲስን ባስመለሰበት ግዜ

ነበር። እና ጦርነቱ ነገውን ሊጀመር ማታ ላይ የጦር መሪው

ሰላሁዲን የወታደሮቹን ድንኳን እየዞረ ሲያዳምጥ፤ ግማሹ ለይል

ይሰግዳል፣ ሌላው ቁርአን ይቀራል፣ የተቀሩት ደግሞ ይዘክራሉ።

ግን ድንገት በሆነ ድንኳን አጠገብ ሲያልፍ በድንኳኑ ውስጥ ያሉት

ሁሉም ተኝተው ነበር። ይህን ግዜ፦"በዚህች ድንኳን አዳሪዎች

ምክንያት ልንሸነፍ እንችላለን" ብሎ አለፈ።

#ማንተኛበት_ዘመን

_____

___

ቀደምት ዑለማኦች በሶስት ነገራት አደራ ይባባሉ ነበር።

1፦ሰውዬው በሱ እና በአላህ መካከል ያለውን ግንኙነት ካሳመረ፤

በሱ እና በሌሎች መካከል ያለው ግንኙነት ያምርለታል።

2፦ሰውዬው ሚስጥራዊ ተግባሩን ካሳመረ አላህ ይፋዊ ተግባሩን

ያሳምርለታል።

3፦ሰውዬው የአኪራው ጉዳይ ካስጨነቀው አላህ የዱንያውንም

የአኪራውንም ጉዳይ ያግራራለታል።

_____

_

#ትልቁ_ኪሳራ_ማለት_ይህ_ነው

ጀነት ስፋቷ የምድርን እና የሰማያትን ያህል ሁና ላንተ በሷ ቦታ

ሳይኖርህ ሲቀር...ትልቅ ኪሳራ ነው።

በእለታዊ ፕሮግራምህ ውስጥ ቁርአንን መቅራት ካልተካተተ ትልቅ

ኪሳራ ነው።

ይህን ፅሁፍ በማሰራጨት ጓደኛህን እንድታነቃው ይከጀላል!

image
Хыпар пек ярас
Ман тетелӗ питра пайлас
Ушкӑнта пайлас