UMMA TOKEN INVESTOR

About me

አጫጭር መረጃዎች፣የግል ምልከታዎችና ጠቃሚ ቁም ነገሮች ይለጠፋበታል! በሚመችዎት ፕላትፎርም ቤተሰብ ይሁኑኝ ╰┈➢https://he1.me/atOM2 قال ابن تيمية -رحمه الله-: {قوام الدين كتاب يهدي وسيف ينصر وكفى بربك هادياونصيرا} مجموع الفتاوى [10/13]

Translation is not possible.
#ናክባ_ሲታወስ!
🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸
“ለአንድ ሳምንት ብለን ወጣን... 77 ዓመታት አለፉ!”— የ95 ዓመቷ መርየም የመመለስ ናፍቆት!🔑🔐
🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸
“ጀርመን ሁለተኛውን የዓለም ጦርነት ካሸነፈች የሚቀሩ አይሁዶች አይኖሩም፣ እንግሊዝ ካሸነፈች ደግሞ የሚቀሩ ዐረቦች አይኖሩም!”
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~
🕊️ሕያው ትዝታ ከናክባ ፍርስራሽ ጀርባ!
አሳዛኙ የፍልስጢኖች የግድያ እና የመፈናቀል ታሪክ ከዓይን እማኝ!
https://t.me/Seyfel_Islam
🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸
ስለ 1948ቱ የፍልስጤም ናክባ (ታላቁ መፈናቀል) ብዙ ታሪካዊ ዘገባዎችና ሰነዶች ተጽፈዋል። ነገር ግን ናክባ ለስምንት አስርት ዓመታት ያህል ደም የሚፈስ ቁስል እንጂ በቀላሉ የሚነበብ የታሪክ ርዕስ አይደለም። ናክባ በሰዎች አካል፣ በድምፃቸው እና በቤታቸው ውስጥ የኖሩበት፣ በድንገት ተገፍተው የወጡበትና ትዝታቸው የታጠረበት መራራ እውነት ነው።
መጽሐፍት ሰፊ ምስል ቢሰጡንም፣ ታሪክ ግን በቀለም ብቻ አይጠናቀቅም። ናክባን በሕያው ትዝታዎች፣ በፍርሃትና በመጥፋት ውስጥ ባለፉ ምስክሮች አንደበት ብንሰማውስ? ያኔ ወደ ሕዝቡ የልብ ምት እንጠጋለን። 🇵🇸
👵የዕድሜ ባለፀጋዋ የመርየም ዐብደል ሃሚድ ምስክርነት🎯
🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸
የ95 ዓመቷ ፍልስጤማዊት መርየም ዐብደል ሃሚድ የዚህ ታሪክ ሕያው ምስክር ናቸው።በሰሜናዊ ፍልስጤም በባህር ዳርቻ ትገኝ ከነበረችው #አልዚብ መንደር ተፈናቅለው ዛሬ በደቡባዊ ሊባኖስ አይን አል-ሂልዌህ የስደተኞች ካምፕ ውስጥ ይገኛሉ።
መርየም ሙሉ በሙሉ ያልተዘጋ የድሮ በር እንደሚከፍት ሰው፣ትዝታዎቿን ደጋግማ ትከፍታለች።ስለ መንደሯ ውበትና ዛሬ ስለቀሩት ፍርስራሾች ትተርካለች።🇵🇸
🌊 አል-ዚብ፡ከክርስትና በፊት የነበረች ጥንታዊት መንደር!
🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸
ታሪኩ የሚጀምረው በመርየም የትውልድ መንደር በአል-ዚብ ነው።ይህች መንደር፦
📍ከአክሬ ከተማ 13.5 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ትገኛለች።
📜 ጥንታዊ ስሟ "አክዚብ" የሚል ሲሆን በከነዓናውያን የተመሰረተች ናት።
🏛️ በታሪኳ የሮማውያንን፣ የኦቶማን ግዛትንና የመስቀል ጦረኞችን አልፋለች።
 
🎯የኢኮኖሚና ማህበራዊ ህይወት🎯
🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸
አል-ዚብ በግብርና (ስንዴ፣ ገብስ፣ ፍራፍሬ) እና በአሳ ማጥመድ የበለፀገች ነበረች። በ1882 በኦቶማን ግዛት የተገነባ ትምህርት ቤት፣ መስጊድና ክሊኒክም ነበራት። በ1945 የሕዝብ ቁጥሯ 1,910 ደርሶ ነበር።
 
🛡️ወረራ እና ስደት፡የመንደሯ መጥፋት
🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸
በ1948 የጽዮናውያን ሚሊሻዎች (በተለይ የሃጋናህ ካርሜሊ ብርጌድ) መንደሯን ኢላማ አደረጉ።
🚀 ኦፕሬሽን ቤን-አሚ:
🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸
በተባለው ጥቃት ነዋሪዎቿ እንዲፈናቀሉ ተደረገ።
🔥የጥፋት ትዕዛዝ:
🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸
ወታደራዊው ባለስልጣን ሞሼ ካርሜል ነዋሪዎቹ ተመልሰው እንዳይመጡ መንደሩ ሙሉ በሙሉ እንዲወድም ትዕዛዝ ሰጠ።
🏚️ በታህሳስ 1948 የአይሁድ ብሔራዊ ፈንድ ባለስልጣኑ ዮሴፍ ዌይትዝ “መንደሯ መሬት ላይ ወድማለች” ሲል በይፋ አስታወቀ።
ይህ የሆነው "ትልቁ የበቀል እርምጃ" በሚል ስም ሲሆን፣ ዓላማውም የፍልስጤማውያንን ታሪክ አጥፍቶ ሰፋሪዎችን በቦታው ማስፈር ነበር።
ይህ ታሪክ የመርየም ብቻ ሳይሆን የጠቅላላ ፍልስጤም የቁስል እና የናፍቆት ታሪክ ነው!
🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸
 
🎯የናክባ መቅድም፡ፍርሃትን የፈጠረ እልቂት📌
https://t.me/Seyfel_Islam
🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸
በካምፑ ውስጥ ባለ ቀላል ክፍል ውስጥ፣ የታዋቂው የሃማስ መሪ የ #ያህያ_ሲንዋር ፎቶ በተሰቀለበት፣ወ/ሮ መርየም ዐብደል ሃሚድ በአል-ዚብ መታሰቢያ ውስጥ የቀረውን እና ከናክባ በፊት እና በኋላ የተከሰተውን ነገር እያስታወሱ ተቀምጠዋል። 👵📜
እንደ ታሪክ ጸሐፊ ሳይሆን እንደ ሽታ፣ ድምጾች፣ የመንገድ እይታዎች፣ የባህር እና የድንበር እይታዎችን የሚያስታውስ ምስክር ሆና ትናገር ነበር። 🌊🕊️
 
⛰️የአመፁና የትግሉ ትውስታ
🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸
የመርየም ዐብደል ሃሚድ ታሪክ በ1936 የፍልስጤም አመፅ ወደ 90 ዓመታት ገደማ ይመልሰናል።በወቅቱ የስድስት ዓመት ልጅ እንደነበረች እና #ከብሪታንያ ሥልጣን ጋር የሚዋጉ የፍልስጤም አማፂያን በተራሮች ላይ እየተጠለሉ እንደነበር ከአባቷ እንደሰማች ትናገራለች፤ ከእነዚህም መካከል ከአልዚብ የመጣውን አማፂ ማህሙድ አብደል ሃፊዝን ጨምሮ። 🛡️⛰️
በአማፂያኑ መካከል የነበሩት ሰማዕታት በሌሊት በድብቅ እንደተቀበሩ እና መቃብሮቹ በትላልቅ የእንጨት ቁርጥራጮች እንደተሸፈኑ እና ቦታቸው ለቤተሰቦቻቸው ብቻ እንደሚታወቅ ትተርካለች።🕯️
🚢 የለውጡ መጀመሪያ
🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸
በልጅነቷ የሊባኖስ-ፍልስጤም ድንበርን ከቤቷ ጣሪያ ላይ ማየት እንደምትችል ገልጻለች፤ አክላም እንዲህ ብላለች፡-
«በናኩራ የሚገኘውን የፈረንሳይ-እንግሊዝ የፍተሻ ጣቢያ እንመለከት ነበር፤ እንዲሁም መኪኖቹ በዚያ የፍተሻ ጣቢያ በኩል ወደ ፍልስጤም እና ወደ ፍልስጤም ሲመለሱ እናያለን።» 🚗🛂
የዘጠና ዓመቷ ሴት ብዙ አይሁዶችን የጫኑ ግዙፍ መርከቦችን ወደ ፍልስጤም ሲወርዱ እንዳየች እና ናሃሪያ ለዚህ ዘመቻ ዋና ዋና ማቆሚያዎች አንዷ እንደነበረች ገልጻለች።እንዲህ ትላለች፡- 🚢⚓
“በወቅቱ ወደ ፍልስጤም የሚመጡ አይሁዶች ከብሪቲሽ ማኒዳቴ ባለስልጣናት የተዘጋጁ የመታወቂያ ካርዶችን እንደተቀበሉ እና እንደኛ ዜጎች እንደሆኑ ይነገር ነበር። ነገሮች በፍጥነት ተከስተዋል፣ ዜናው ተሰራጭቷል፣ እናም ወደ መንደሩ የመጡ ሰዎች እና ሌሎች አካባቢዎችን የጎበኘ እና ከዚያም ዜናውን ይዘው ከተመለሱ የአልዚብ ሰዎች ምን እየተከናወነ እንዳለ እንሰማ ነበር።" 📢📰
🏥 ግንኙነቶችና ትንቢቶች
🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸
ሆኖም፣መርየም ዐብደል ሃሚድ በወቅቱ በፍልስጤማውያን እና በአይሁዶች መካከል የነበረው የዕለት ተዕለት ግንኙነት በኋላ ላይ እንደነበረው ሁልጊዜ ውጥረት እንደነበረው አፅንዖት ሰጥቷል። ከአይሁድ ዶክተሮች ህክምና እንዳገኘች ትናገራለች፡- 🩺💊
“ስማቸውን በትክክል አስታውሳለሁ፡ የመጀመሪያው ናታን የተባለ አጠቃላይ ሐኪም ነበር፣ እና ኪዊ የሚባል ሌላ ዶክተር እንዲሁም ሚሪያም የተባለ የማህፀን ሐኪም ነበር።"
አንዳንድ አይሁዶች ለፍልስጤማውያን እንዲህ ይሉ ነበር፡-
“ጀርመን ሁለተኛውን የዓለም ጦርነት ካሸነፈች የሚቀሩ አይሁዶች አይኖሩም፣ እና እንግሊዝ ካሸነፈች የሚቀሩ አረቦች አይኖሩም።’⚠
እነዚህ ቃላት ያለማቋረጥ ይደገሙ ነበር፣ እና ሰዎች ስለሚነገረው ነገር ይፈሩ ነበር፣ ነገር ግን ናክባ ፈጽሞ ያልተጠበቀ ነበር። ህይወታችን የተለመደ ነበር፣እናም እንደተከሰተው እንደምንፈናቀል የሚያሳይ ምንም ምልክት አልነበረም።🏠🚫
💔የመጀመሪያው ድንጋጤ
🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸
መርየም ዐብደል ሃሚድ እንደሚሉት፣ በ1948 መጀመሪያ ላይ፣ከናክባ ጥቂት ቀደም ብሎ፣ “የመጀመሪያው ድንጋጤ” ብለው የገለጹት ነገር የተከሰተው ከአል-ዚብ የመጡ ፍልስጤማውያን በናሃሪያ መግቢያ ላይ አይሁዶች ባቆሙት የፍተሻ ጣቢያ ላይ ሲገ**,ደሉ ነው፡-🩸🔥
“ወጣት ፍልስጤማውያንን የያዘ ሚኒባስ ነበር፣ እና ተኩስ ከፍተው አስሩን ገድለዋል።ሌላ መኪና ሚኒባስን ለመከተል እየሞከረ ነበር፣ነገር ግን ተሳፋሪዎቹ ከታለመው ተሽከርካሪ ወፍራም ጭስ ሲወጣ ካዩ በኋላ ቆመ፣ ከዚያም በእሳት አቃጥለውታል። 🚐💨
ከዚያ በኋላ አል-ዚብ ፍርሃት ያዘ፣እና ብዙ ሰዎች እንዳይገደሉ በመፍራት ወደ ናሃሪያ ከመሄድ ተቆጠቡ።” 😨👣
 
🎯የአል-ዘብ ጥፋት፡ትውስታና ስደት📌
🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸
ጥቃቱ የጀመረው ከ"አል-ራምል" አቅጣጫ ነበር።
🌊በአል-ዘብ የባህር ዳርቻ አቅራቢያ "አል-ራምል" የሚባል ስፍራ ነበር።እዚህ ቦታ ላይ የመንደሩ ነዋሪዎች ከአሮጌው መንደር ወጣ ብለው አዳዲስና ዘመናዊ ቤቶችን የገነቡበት መንደር ነበር።መርየም አብደል ሃሚድ በወቅቱ የነበረውን ሁኔታ ስታስታውስ ጥቃቱ በድንገት ከአል-ራምል በኩል እንደመጣ ትገልጻለች።የአይሁድ ታጣቂ ቡድኖች በጀልባዎች መጥተው ወደ መንደሩ ዘለቁ።
“ከአል-ራምል የባህር ዳርቻ ጥቃት ሰንዝረዋል... አስፈሪ ነበር!”😱
 
💔የመጀመሪያዎቹ ሰለባዎች📌
🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸
በዚያን ጊዜ የታጠቁ አይሁዶች “ሸይኽ ጦሃ” የተባሉትን ሰው በበግ ማጎሪያ ውስጥ አግኝተው ከሌላ እረኛ ጋር ገደ'ሏቸው።የሼኩ ባለቤት ግድያውን ስትመለከት፣ታጣቂዎቹ እንዳያገኟት በጭስ ማውጫ ውስጥ ተደበቀች።እነሱ ሲሄዱም ወደ አል-ካብሪ አካባቢ ሸሸች።
ታጣቂዎቹ ጉዟቸውን በመቀጠል “ዳውድ አል-ሐጅ አብዶ” የሚባል ሌላ ሰላማዊ ሰው ገደ*'ሉ።የግድያዎቹ ዜና ወደ አሮጌው መንደር ሲደርስ፣ወጣቶቹ በመግቢያዎቹ ላይ ጥበቃቸውን አጠናከሩ።በተለይም በናሃሪያ መግቢያ ላይ የአሸዋ ከረጢቶችን ድንበር አድርገው መከላከያ አበጁ!🛡️
 
⚔️ ያልተመጣጠነ ጦርነት
🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸
በራምል ግድያው እየተባባሰ መጣ፤ ብዙዎች እንደ ሰማዕት ወደቁ። 🩸 ማምለጥ የቻሉት ወደ አሮጌው ከተማ ሸሹ።መርየም ዐብደል ሃሚድ እንዲህ ትላለ
ች፦
"በዚብ ሰዎች እና በአጥቂዎቹ መካከል ግጭት ተከስቷል።የመንደሩ ነዋሪዎች ግን ከባድ መሳሪያ አልነበራቸውም፤ቢበዛ የአደን ጠመንጃ ብቻ ነበር።እንዲያውም በቢላ የተያዘ ማንኛውም ሰው ይታሰር ስለነበር፣አብዛኛው ሰው እጁ ላይ መሳሪያ አልነበረም!?
?🔫
 
🛶 የመመለስ ተስፋ የታከለበት ስደት
🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸
ጥቃቱ ሲበረታና ወንበዴዎቹ ወደ መንደሩ ሲጠጉ ሰዎች መሸሽ ጀመሩ።አብዛኛዎቹ መዳረሻቸው ወደ ሊባኖስ 🇱🇧 ነበር። አንዳንዶች በእግር፣አንዳንዶች በመኪና፣ ሌሎች ደግሞ በጀልባ ወደ ደቡባዊ ሊባኖስ ጢሮስ ከተማ ተጓዙ። 🛶
መርየም ዐብደል ሃሚድ “ናክባ(Nakba)” በተከሰተበት ወቅት የ18 ዓመት ወጣት እና ባለ ትዳር ነበረች።አማቷ ማህሙድ አል-ሳዲ የአል-ዘብ መሪ እና በአክሬ ውስጥ ታዋቂ ሰው ነበር።ቤቱ ዛሬም ድረስ በአካባቢው ለታሪክ ቆሞ ይገኛል።🏠
 
⏳የአንድ ሳምንት ቀጠሮ... የ77 ዓመት ስደት😔
🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸
ወደ ጢሮስ የሄዱት ከትውልድ ቀያቸው መራቅ ስላልፈለጉና በቅርቡ የመመለስ ትልቅ ተስፋ ስላላቸው ነበር።መርየም ዐብደልሃሚድ የመጨረሻውን ቀን እንዲህ ታስታውሳለች፦
“ልንወጣ ስንል ከአረብ ነፃ አውጪ ጦር የመጣ አንድ ኃይል መጣና ወዲያውኑ መውጣት እንዳለብን፣ጦርነቱን እንደሚቆጣጠሩ እና መፈናቀላችን ከመመለሳችን አንድ ሳምንት ብቻ እንደሚቆይ ነገሩን!”
🗝️መልእክቱ ቀጥተኛ ነበር።በዚህም ምክንያት ሰዎች ቤቶቻቸውን በቁልፍ ዘግተው፣አስፈላጊ ንብረቶቻቸውን ብቻ ይዘው ለጥቂት ቀናት እንደምንርቅ አስበን ወጣን።ጦርነቱ ለአረብ ነፃ አውጪ ጦር ድልን እንደሚያመጣ ብናስብም፣ እውነታው ግን ሌላ ሆነ።
“ቤታችንን ለቅቀን ወጣን፤ነገር ግን እስከዛሬ አልተመለስንም።እጣ ፈንታችንን ሳናውቅ የያዝነውን ሁሉ ትተን ወጣን። መፈናቀላችን ከጥቂት ቀናት በላይ እንደማይቆይ አምነን ነበር... ነገር ግን ወደ 77 ዓመታት ዘለቀ።" 🗝️🇵🇸
 
⛺“የማፈናቀል ድንኳኖች” የማይነገር ስቃይ🎯
https://t.me/Seyfel_Islam
🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸
መርየም ዐብደል ሃሚድ እና ቤተሰቧ በጢሮስ የቆዩበት ጊዜ ለአጭር ጊዜ ነበር።ከናክባ በኋላ በተለያዩ ቦታዎች ለፍልስጤማውያን ካምፖችን ስለማቋቋም ወሬ ተጀመረ።በጊዜ ሂደት ጊዜያዊ ሳይሆን ማለቂያ የሌለው ህይወት በሆነው “የድንኳን ዓለም” ውስጥ ምግብና ውሃ እየተጠበቀ ስደት ቀጠለ።💧🥖
 
⛺️የአይን አል-ሂልዌህ መከራ🎯
🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸
መርየም ዐብደል ሃሚድ ከቤተሰቧ ጋር ወደ "ሲዶን አይን አል-ሂልዌህ" አካባቢ ተዛወረች።እዚያም ለተፈናቃዮች ትልቅ ካምፕ ተመሠረተ።
“ድንኳኖቹ ለቤተሰቦቹ ተዘርግተዋል፣ እኛም እዚያ ቆየን።ስቃዩ እጅግ ከፍተኛ ነበር።”💔
"የእርዳታ ድርጅቶች በየቀኑ ምግብ ይሰጡን ነበር፤መታጠቢያ ቤቶች የተገነቡት በጣም ርቀት ላይ ስለነበር እነሱን ለመድረስ ረጅም መንገድ በእግር እንድንሄድ እንገደድ ነበር።ስቃዩ መራራ እና ሊገለጽ የማይችል ነበር!"🚶‍♀️⛈️
አይን አል-ሂልዌህ የተገነባበት መሬት የስንዴ ማሳና አፈሩም ሎማም ነበር። መርየም ዐብደል ሃሚድ ትዝታዋን እንዲህ ትቀጥላለች፦“በአንድ ወቅት ከባድ ዝናብ ዘንቦ ብዙ ድንኳኖችን ያወደመ የመሬት መንሸራተት አስከትሏል።በአስቸጋሪ ሁኔታዎች ውስጥ እንኖር ነበር፤ ከተለያዩ ከተሞች የተውጣጡ ቤተሰቦች በሌሊት በድንኳኑ ውስጥ በገመድ በተሰቀሉ ብርድ ልብሶች ብቻ ተለያይተው አንድ ድንኳን እንዲጋሩ ተገደዋል!”⛺🌧️
🗺️የስደት መንገዶች🎯
🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸
መርየም ዐብደል ሃሚድ በአይን አል-ሂልዌህ ብቻ ሳይሆን በሊባኖስ ውስጥ በተለያዩ ቦታዎች ብትዘዋወርም ልቧ ግን ሁሌም ከፍልስጤም ጋር ነበር።
መጀመሪያ ወደ ሲዶና(የአል-ራኢ ቤተሰብ ንብረት ወደሆነ የገበሬ ቤት) ተዛወረች።
በመቀጠል በሊባኖስ ተራራ ወደሚገኘው #ሞንቴቨርዴ አካባቢ ሄደች።ባለቤቷ እዚያ አትክልተኛ ሆኖ ተቀጠረ!🌳
“የናክባ ክስተቶች ያለምንም ማዛባት ለዓለም በትክክል መተላለፍ አለባቸው፤ በተለይም የፍልስጤማውያን ሕዝብ ስቃይ ከሌላው የተለየ ስለሆነ።" 🗣️📢
🏘️ ወደ ዚብ ሰፈር መመለስ🎯
🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸
በ1975 የሊባኖስ የእርስ በርስ ጦርነት ሲፈነዳ፣ሁኔታዎች እየተባባሱ በመምጣታቸው ሞንቴቨርዴን ለቀው እንደገና ወደ አይን አል-ሂልዌህ ካምፕ ተመለሱ።ከዚያን ጊዜ ጀምሮ እዚያው ይኖራሉ።🏚️
በአሁኑ ጊዜ የምትኖረው “ዚብ” በተባለ ሰፈር ውስጥ ነው።ይህ ስያሜ የተሰጠው በመጀመሪያው መንደሯ ስም ሲሆን፣ዚብ በአሳ አጥማጆችና በመርከበኞች የምትታወቅ ውብ መንደር ነበረች(መጀመሪያ ላይ እንዳየነው)
🛶🐟
"ከደቡባዊ ሊባኖስ መንደሮች የመጡ ሊባኖሳውያን በግብርና ለመስራት ወደ ዚብ ይመጡ እንደነበር አስታውሳለሁ። የሊባኖስ ወንዶች ከዚብ ሴቶችን አግብተው እዚያ ይሰፍሩ ነበር።በሁለቱ ወገኖች መካከል ያለው ግንኙነትና ንግድ ከናክባ በፊት የጠበቀ ነበር!
”🤝✨
📢የፅናት መልእክት ለዓለም
🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸
መርየም ዐብደል ሃሚድ አገሯን የሚያገለግል ማንኛውንም ነገር ከማድረግ ወደኋላ አትልም።እንዲያውም ዩናይትድ ስቴትስ ድረስ በመሄድ በኮንፈረንሶች ላይ ስለ ፍልስጤም ናክባ እውነቱን መስክራለች፦🇺🇸✈️
“በኮንፈረንሶች ላይ ተቀምጬ ስለ ናክባ እውነቱን እናገራለሁ፤ ምክንያቱም እኛ እውነቱን አይተናል፣ አሳዛኝ ሁኔታዎችንም ራሳችን ገጥመናል። የፍልስጤም ህዝብ ስቃይ ልዩ ስለሆነ ያለ ምንም ተዛብቶ ለዓለም መድረስ አለበት!”
“ሀገራዊ መልእክቴ ለዓለም ግልጽ ነው፦ፍልስጤም የእኛ ነበረች፣ የእኛም ትሆናለች!”🇵🇸
“የመመለሻ መብታችንን(Right of Return) አጥብቀን እንይዛለን፤ምንም ዓይነት ማስፈራራት ቢኖርም አንተወውም! ወደ ፍልስጤም ተመልሼ በምድሬና በከተማዬ እዚያ ለመቀበር ተስፋ አደርጋለሁ፤ምክንያቱም ሥሮቻችን እዚያ ናቸው፣ በፍጹም አንተዋቸውም!” 🗝️🌳
 
🇵🇸ወደ ሊባኖስ የሚጎርፉት ስደተኞች ለምን በጣም ጎልተው ታዩ?
https://t.me/Seyfel_Islam
🇵🇸 🇱🇧🇵🇸 🇱🇧🇵🇸 🇱🇧🇵🇸 🇱🇧🇵🇸 🇱🇧
በ1948ቱ ናክባ ወቅት፣ከ100,000 እስከ 130,000 የሚደርሱ ፍልስጤማውያን ወደ ሊባኖስ ለመሸሽ ተገደዋል።በዚያን ጊዜ በሊባኖስ የሚገኙ የፍልስጤም ስደተኞች ከጠቅላላው የፍልስጤም ስደተኞች ብዛት 13.8% የሚሆኑት ሲሆኑ፣ይህም ወደ 760,000 የሚደርስ ነበር (UNSCAP ስታቲስቲክስ)
📍መነሻቸው ከየት ነበር?
🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸 🇵🇸
ወደ ሊባኖስ የመጡት አብዛኛዎቹ ስደተኞች ከ #ገሊላ ክልል የመጡ ነበሩ፤ በተለይም ከሚከተሉት ከተሞችና መንደሮች፦
📌ዐከር 🏘️
📌ናዝሬት ✨
📌ሴፍድ 🏔️
📌ቲቤሪያስ 🌊
🤝የሊባኖስ አቀባበልና ታሪካዊ ትስስር
🇵🇸 🇱🇧🇵🇸 🇱🇧🇵🇸 🇱🇧🇵🇸 🇱🇧🇵🇸 🇱🇧
በዚያን ጊዜ የሊባኖስ መንግሥት ስደተኞቹን በደስታ ተቀብሏል፡
#ፕሬዝዳንት_ቤቻራ_ኤልኩሪ ለፍልስጤማውያን “አገራችሁ ግቡ” በማለት ሊባኖስ ሁለተኛ ቤታቸው እንደሆነች አፅንዖት የሰጡ የወቅቱ የሊባኖስ ፕሬዝዳንት!🏠
#ጠቅላይ_ሚኒስትር_ሪያድ_አልሶልህ የሊባኖስ ሕዝብ “ከፍልስጤማውያን ጋር ዳቦ ለመጋራት” ዝግጁ መሆኑን ያረጋገጡ የወቅቱ የሊባኖስ ጠቅላይ ሚኒስተር ነበሩ።🥖🤝
🔗 ጥብቅ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ትስስር🇵🇸 🤝🇱🇧
🇵🇸 🇱🇧🇵🇸 🇱🇧🇵🇸 🇵🇸 🇱🇧🇵🇸 🇱🇧
የፍልስጤም ስደተኞች ወደ ሊባኖስ መጎርፋቸው በጋብቻ እና በማህበራዊ ትስስር ላይ የተመሰረተ ነበር፡
ጋብቻ፦ በዚብ መንደር የሊባኖስ ዜጎች የመንደሩን ነዋሪዎች ያገቡ ነበር። 💍
ንግድ፦ በአክሬ እና በሲዶን መካከል ያለው የንግድ ልውውጥ ግንኙነቱን አጠናክሮታል። 🚢
ስራ፦ ብዙ ሊባኖሳውያን በሃይፋ ወደብ እና በነዳጅ ኩባንያዎች ውስጥ ይሰሩ ነበር። ⛽🛠️
⌛ በቅርቡ እንመለሳለን የሚል ተስፋ
ፍልስጤማውያን መመለሳቸው በቅርቡ እንደሚሆን በማመን፣ ወደ ከተማዎቻቸው ቅርብ የሆኑ የድንበር ቦታዎችን መርጠዋል። 🛤️ ለምሳሌ ማርያም አብደል ሃሚድ በመጀመሪያ በጢሮስ ለመቆየት መርጣ ነበር። ⛺
📜 ማጠቃለያ
የአል-ዚብ ታሪክ የመፈናቀል አሳዛኝ ሁኔታን ተከትሎ የፍልስጤማውያንን ስቃይ የሚያብራራ ትልቅ ምስክር ነው። የናክባ ታሪክ የደም መፍሰስ ቁስልን የፈጠረ ዘመን ማስረጃ ሲሆን፣ የፍልስጤም ዓላማ ያለፈ ታሪክ ሳይሆን ሕያው ትዝታ መሆኑን ያስታውሰናል። 🕊️ የፍልስጤም የመመለሻ መብት እስካልተሟላ ድረስ ይህ ታሪክ ለትውልድ ይተላለፋል። 🇵🇸🗝️
📚 ማጣቀሻዎችና ምንጮች
ቃለ ምልልስ፦ ከወ/ሮ መርየም ዐብደል ሃሚድ ጋር (የ1948 ናክባ ስደተኛ) 👵
ኢንሳይክሎፔዲያ፦ የአል-ዘብ መንደር ታሪክ 📖
መጽሐፍ፦ "እንዳንረሳው" - ዋሊድ ካሊዲ (1997) 📑
ጥናት፦ የአል-ዘይቱና የጥናት ማዕከል - ቤሩት (2008) 🔍
ምንጭ፦ለአል-አራቢ የቴሌቪዥን ድህረ ገጽ 📺
✍𝓐𝓫𝓭𝓮𝓵𝓪𝔃𝓲𝔃 𝓑𝓲𝓷𝓜𝓾𝓱𝓪𝓶𝓶𝓮𝓭
(Seyfel Islam AlHabeshi)
ታህሳስ 10/2018
December 19/2025
ቴሌግራም👇
https://t.me/Seyfel_Islam
https://t.me/Seyfel_Islam
image
image
image
image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.
☀️ #ዕለቱን_በታሪክ_ቁጥር1_ለ☀️
¤¤¤¤¤¤¤¤¤¤¤¤¤¤¤¤¤¤¤
ዛሬ በሒጅራ አቆጣጠር ጀማዱል ኣኺር 26ኛ ቀን ነው!
የዛሬ 612 አመታት ወደ ኋላ ስንመለስ በ835 ሒጅራ ጀማዱል ኣኺር 26ኛው ቀን ገና በወጣትነቱ #ቆስጠንጥያን በመክፈት የረሱልን ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም የድል ትንብይት እውን ያደረገው ጀግና ሱልጣን #ሙሐመድ_አል_ፋቲህ የተወለደበት ቀን ነው።
ምንም እንኳን ሱልጣኑ የተወለዱት ረጀብ 26ኛው ቀን ነው የሚሉ መረጃዎች በመኖራቸው በታሪክ ምሁራን መካከል ሁለት አመለካከቶች ቢኖሩም ጀማዱል ኣኺር 26ኛ ነው ባሉት ምሁራን መሰረት ታሪኩን ከውልደት እስከ ህልፈት እና ከታሪኩ የምንማራቸውን ቁም ነገሮች ለማንበብ በሚመች አቀራረብ አዘጋጅቸላችኋለሁ።
ሱልጣኑ የተወለዱት ጀማዱል ኣኺር 26ኛው ቀን ነው ያሉ ምሁራንን ማስረጃ መጨረሻ ላይ ታገኛላችሁ!
🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱
ታላቁ የኡስማንያ መሪ ሱልጣን ሙሐመድ አል-ፋቲህ (መሐመድ ዳግማዊ) በታሪክ ውስጥ ጉልህ ስፍራ ካላቸው መሪዎች አንዱ ነው።የቁስጥንጥንያ(ኢስታንቡል) ድል አድራጊ በመሆኑም "አል-ፋቲህ" (ድል አድራጊው) የሚል ቅጽል ስም ተሰጥቶታል።
በዛሬው“ዕለቱን በታሪክ”አምዳችን የዚህን ጀግና ታሪክ በወፍ በረር ከውልደት እስክ
ህልፈቱ ላስዳስሳችሁ እሞክራለሁ መልካም ንባብ።
https://t.me/Seyfel_Islam
 
📌ክፍል1:የሙሐመዱል ፋቲህ ውልደት፣እድገት፣እንድሁም ስለ ወላጆቹ እና በግዜው ስለነበረው ሁኔታ በአጭሩ📌
⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️
ሱልጣን ሙሐመድ አል-ፋቲህ መጋቢት 30 ቀን 1432 እ.ኤ.አ ወይንም በጀማዱልኣኺር 26/835ሒጅራ(በብዙ መረጃዎች ደግሞ ረጀብ 26፣835 ሂጅራ የሚል ተጠቅሶ እናገኛለን)በወቅቱ የኡስማንያ (ኦቶማን) ግዛት ዋና ከተማ በነበረችው #ኤድርኔ (Edirne) ተወለደ።
ሙሐመድ አል-ፋቲህ ከመወለዱ በፊት የነበረው ዓለም አቀፋዊ ሁኔታ በትቂቱ ይሄን ይመስል ነበር:-
📍1ኛ:የቢዛንታይን ግዛት መዳከም⚡️
~~~~
በአንድ ወቅት ኃያል የነበረው የቢዛንታይን (የምስራቅ ሮም) ግዛት ተዳክሞ በቁስጥንጥንያ ቅጥር ግቢ ብቻ ተወስኖ ነበር።ሆኖም ከተማዋ በጂኦግራፊያዊ አቀማመጧ ምክንያት አሁንም ለንግድና ለጦርነት ቁልፍ ነበረች።
📍2ኛ:የኡስማንያ ግዛት መረጋጋት⚡️
~~~~
ግዛቱ ከአንካራ ጦርነት ሽንፈት (ከቲሙር ላንግ ጋር ከነበረው ግጭት) በኋላ መልሶ እያገገመና እየተጠናከረ የነበረበት ወቅት ነበር።
📌የነብዩ ሙሐመድ-ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም-ትንቢት📌
=======================
ነቢዩ ሙሐመድ(ሰ.ዐ.ወ)“ቁስጥንጥንያ በእርግጥ ትከፈታለች፤እሷን የሚከፍተው መሪ ምንኛ ምርጥ መሪ ነው!ያ ሰራዊትም ምንኛ ምርጥ ሰራዊት ነው!”ሲሉ የተናገሩትን ትንቢት ለመፈጸም ለ800 ዓመታት ሲመኙ ነበር።
📌የወላጆቹ ሁኔታ📌
======================
📍አባቱ -ሱልጣን ሙራድ ዳግማዊ📍
~~~~
አባቱ ሱልጣን ሙራድ ጠንካራ መሪና ፍትሃዊ ሰው ነበሩ።ግዛቱን በማስፋፋትና የውስጥ አመጾችን በማርገብ ይታወቃሉ። ሙራድ ዳግማዊ ልጃቸው ሙሐመድ ለታላቅ ዓላማ እንዲበቃ ከፍተኛ ጥረት አድርገዋል።
📍እናቱ - ሁማ ሃቱን📍
~~~
ስለ እናቱ ማንነት የታሪክ ምሁራን የተለያዩ ሃሳቦችን ይሰነዝራሉ።ነገር ግን እርሷ በልጇ አስተዳደግና ስብዕና ላይ ትልቅ ሚና የነበራት፣ለልጇ ሃይማኖታዊና ስነ-ምግባራዊ እሴቶችን ያወረሰች እናት ነበረች።
📌አስተዳደግና ትምህርት📌
========================
የሙሐመድ አል-ፋቲህ አስተዳደግ “ለታላቅነት የታጨ”ሰው አስተዳደግ ነበር ማለት ይቻላል።
በልጅነቱ እልከኛና ትንሽ አስቸጋሪ እንደነበር ይነገራል።ነገር ግን አባቱ ሱልጣን ሙራድ በወቅቱ የነበሩ ታላላቅ ምሁራንን በመመደብ የባህሪ ለውጥ እንዲያመጣ አድርገዋል።ለምሳሌ:
📍አቅ ሸምሰዲን⚡️
~~~~
ሙሐመድ ላይ ትልቁን ተጽዕኖ ያሳረፉት መምህራቸው ናቸው።እርሳቸው ለሙሐመድ “ቁስጥንጥንያን የምትከፍተው አንተ ነህ” የሚለውን መንፈስ በውስጡ የዘሩትና በመንፈሳዊ ጥንካሬ ያነጹት ሰው ናቸው።
📍ሁለገብ እውቀት⚡️
~
ሙሐመድ ሃይማኖታዊ እውቀትን (ቁርኣን፣ ሐዲስ፣ ፊቅህ) ብቻ ሳይሆን ሳይንስን፣ ፍልስፍናን፣ ጂኦግራፊንና ስነ-መንግስትን ተምሯል።
📍የቋንቋ ችሎታ⚡️
~~~
በቋንቋ በኩል እጅግ የተዋጣለት ነበር።ቱርክኛ፣አረብኛ፣ፋርስኛ፣ግሪክኛ፣ላቲን፣ሰርቢያኛ እና ዕብራይስጥ ቋንቋዎችን በደንብ ይናገርና ይረዳ ነበር።ይህም ለወደፊቱ ዲፕሎማሲያዊ ስራው ትልቅ በር ከፍቶለታል።
📍የተግባር ልምድ⚡️
~~~
ገና በ12 ዓመቱ አባቱ ለተወሰነ ጊዜ ስልጣን በውክልና ሰጥተውት ነበር።ይህ የልጅነት የንግስና ልምድ የአስተዳደርን ከባድነትና የፖለቲካን ሴራ ቀድሞ እንዲረዳ አስችሎታል።
 
📌ክፍል ሁለት፡ወደ ስልጣን መምጣትና ለታላቁ ድል የተደረጉ ዝግጅቶች📌
⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️
የሱልጣን ሙሐመድ አል-ፋቲህ ወደ ስልጣን መምጣትና ለቁስጥንጥንያ ከበባ ያደረገው ዝግጅት፣ በታሪክ ውስጥ እጅግ አስደናቂ ከሆኑ ስልታዊ እቅዶች አንዱ ተደርጎ ይወሰዳል።
⚡️ወደ ስልጣን መምጣት (ሁለተኛው ንግስና)⚡️
========================
ሙሐመድ አል-ፋቲህ ለመጀመሪያ ጊዜ በ12 ዓመቱ ወደ መንበሩ ቢወጣም፣ በልጅነቱና በውጭ ወራሪዎች ስጋት ምክንያት አባቱ ሱልጣን ሙራድ ዳግማዊ ወደ ስልጣን ተመልሰው ነበር።በ1451 እ.ኤ.አ አባቱ ሲያርፉ፣በ19 ዓመቱ ለሁለተኛ ጊዜ ሱልጣን ሆነ።
⚡️የውስጥ ተቃውሞ⚡️
~~~~ብዙዎች “ገና ወጣት ነው፣ግዛቱን መምራት አይችልም!” ብለው ንቀውት ነበር።
⚡️የቢዛንታይን ስህተት⚡️
~~~~
የቢዛንታይን ንጉስ ቆስጠንጢኖስ 11ኛ፣ ሙሐመድን እንደ ልምድ የሌለው ወጣት በመቁጠር የግዛቱን ወሰን ለማስገፋትና የተለያዩ ጥያቄዎችን ለማቅረብ ሞከረ። ይህ ስህተታቸው ለሙሐመድ ወሳኝ እርምጃ እንዲወስድ ምክንያት ሆነው።
 
⚡️ስልታዊ ዝግጅቶች(Strategic Preparation)⚡️
=========================
ሙሐመድ አል-ፋቲህ ስልጣን እንደያዘ ዋነኛ ትኩረቱ "የማይደፈረውን" የቁስጥንጥንያ ግንብ ሰብሮ መግባት ነበር።ለዚህም የሚከተሉትን ተግባራት አከናወነ፡-
📌ነኛ:ሩሜሊ ሂሳሪ(Rumeli Hisarı) ግንብ መገንባት⚡️
========+===============
ቁስጥንጥንያ ከጥቁር ባህር የሚመጣላትን እርዳታ ለማቋረጥ፣ በቦስፈረስ ባህረ ሰላጤ (Bosphorus Strait) አውሮፓዊው ክፍል ላይ እጅግ ግዙፍ የሆነ ምሽግ በ4 ወራት ውስጥ ብቻ አስገነባ።ይህ ምሽግ ከባህር የሚመጡ መርከቦችን ለመቆጣጠር አስቻለው።
📌2ኛ:ግዙፉ መድፍ(The Great Cannon/Urbans's Gun)⚡️
=======================
የቁስጥንጥንያ ግንቦች እጅግ ወፍራም በመሆናቸው በወቅቱ በነበሩ መሳሪያዎች አይሰበሩም ነበር። #ሙሐመድ_ኡርባን የተባለ #ሃንጋሪያዊ የመድፍ ባለሙያን ቀጥሮ፣በታሪክ ታይቶ የማይታወቅ ግዙፍ መድፍ አሰራ።ይህ መድፍ ግማሽ ቶን የሚመዝን ድንጋይ ከአንድ ማይል በላይ መወርወር የሚችል ነበር።
 
📌3ኛ:የባህር ኃይል ግንባታ⚡️
========================
ከተማዋ በሶስት አቅጣጫ በውሃ የተከበበች በመሆኗ፣ሱልጣኑ ከ400 በላይ ትናንሽና ትላልቅ መርከቦችን በማዘጋጀት የባህር ኃይሉን አጠናከረ።
⚡️ድንቅ ስልታዊ ብልሃት፡መርከቦችን በየብስ ላይ ማጓጓዝ⚡️
=======================
ይህ የሙሐመድ አል-ፋቲህ ድንቅ ወታደራዊ ጥበብ የታየበት ክስተት ነው።
ሆኖም ቢዛንታይኖች የ"ጎልደን ሆርን" (Golden Horn) የባህር ወሽመጥን በግዙፍ ሰንሰለት ዘግተውት ነበር። የኦቶማን መርከቦች ወደዚያ መግባት ሳይችሉ ቀሩ።
🔐ነገር ግን ሙሐመድ አልፋቲሕ ለዚህ መፍትሄ መርከቦቹን በባህር ፋንታ በየብስ (በመሬት) ላይ እንዲጓጓዙ አዘዘ።በአንድ ሌሊት ውስጥ፣በቅባት በተቀቡ እንጨቶች ላይ በማንሸራተት 70 የሚሆኑ መርከቦችን ከኮረብታ ጀርባ በማሳለፍ ወደ ወሽመጡ አስገባቸው‼አሏሁ አክበር!ምን አይነት ብልሃት ነው?!
ጠዋት ላይ የቢዛንታይን ሰራዊት መርከቦቹን ከጀርባቸው ሲያይ ድንጋጤ ውስጥ ወደቀ!
⚡️መንፈሳዊና ስነ-ልቦናዊ ዝግጅት⚡️
=========================
ሙሐመድ ሰራዊቱን ለማነቃቃት የነቢዩን (ሰ.ዐ.ወ) ትንቢት ዘወትር ያስታውሳቸው ነበር።መምህሩ አቅ ሸምሰዲን በየቀኑ በድንኳኖች ውስጥ እየተዘዋወሩ ሰራዊቱን በዱዓ እና በንግግር ያጠናክሩ ነበር። ሱልጣኑ ራሱ ሳይንቲስትና መሐንዲስ ስለነበር፣ የጦርነቱን ካርታና ምህንድስና በራሱ እጅ ይነድፍ ነበር።
⚡️የመጨረሻው ጥቃት መጀመር⚡️
========================
ሚያዝያ 6፣1453 እ.ኤ.አ ከበባው በይፋ ተጀመረ።ለ53 ቀናት የዘለቀው ይሄ ከበባ፣ ዓለምን ለዘላለም የሚቀይር የታሪክ ምዕራፍ መጀመሪያ ነበር!
 
📌ክፍል ሦስት፡ታላቁ ድል፣ የቁስጥንጥንያ መውደቅ እና የድል አድራጊው ሰብዓዊነት📌
⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️
በዚህ ክፍል የ53 ቀናት ከበባ እንዴት ወደ ፍጻሜ እንደመጣ እና ዓለምን የለወጠው ያ ታሪካዊ ቀን እንዴት እንደነበረ በዝርዝር እናያለንደ
⚡️የመጨረሻው ጥቃት (ግንቦት 29፣ 1453)⚡️
=========================
ከ53 ቀናት ተከታታይ ከበባ እና ድካም በኋላ፣ሱልጣን ሙሐመድ አል-ፋቲህ ሰራዊቱን ለታላቁና ለመጨረሻው ጥቃት አዘጋጄ!
📌መንፈሳዊ ዝግጅት:
~~~
ግንቦት 28 ምሽት ላይ፣ሱልጣኑ መላው ሰራዊት እንዲጾም፣እንዲጸልይና በየድንኳኑ መብራት እንዲያበራ አዘዘ።ሌሊቱን ሙሉ የ"ተክቢራ" ድምፅ በቁስጥንጥንያ ቅጥር ዙሪያ ያስተጋባ ነበር።አሏሁ አክበር!
📌የጥቃቱ ስልት፦
~~~
ጥቃቱ ጎህ ሳይቀድ በሦስት አቅጣጫ ተጀመረ።መጀመሪያ “አዘቦች”(መደበኛ ያልሆነ ሰራዊት)፣ቀጥሎ የአናቶሊያ ሰራዊት፣በመጨረሻም የሱልጣኑ ምርጥ የጦር ክፍል የሆኑት “ጃኒሰሪዎች” እንዲገቡ ተደረገ።
📌ግንቡ መጣስ⚡️
=======================
በኡርባን ግዙፍ መድፍ የተመታው የቅዱስ ሮማነስ ደጃፍ (St. Romanus Gate) በመጨረሻ #ፈረሰ።አሏሁ አክበር!
#ሀሳን_አል_ሉባትሊ የተባለ ወጣት ወታደር ከ30 ጓደኞቹ ጋር በመሆን፣ ቀስቶችና ድንጋዮች እየዘነቡበት የግንቡ አናት ላይ በመውጣት የመጀመሪያውን የኡስማንያ ሰንደቅ ዓላማ #ሰቀለ‼
ይህ ክስተት ለኦቶማን ሰራዊት ትልቅ ወታደራዊ ወኔ ሰጠ!
 
⚡️ወደ ከተማዋ መግባት⚡️
=========================
የቢዛንታይን ንጉስ ቆስጠንጢኖስ 11ኛ እስከ መጨረሻው ተዋግቶ በጦርነቱ ሜዳ ላይ #ወደቀ።በዚያው እለት ከሰዓት በኋላ፣ ሱልጣን ሙሐመድ አል-ፋቲህ በነጭ ፈረሱ ላይ ሆኖ በታላቅ ግርማ ወደ ከተማዋ #ገባ!!አሏሁ አክበር ወሊላሂል ሐምድ!
⚡️የመጀመሪያው ስግደት⚡️
=========================ሱልጣኑ በቀጥታ ወደ #አያ_ሶፊያ(Hagia Sophia) አመራ።እዚያም ከፈረሱ ወርዶ ሱጁድ አደረገ!
አያ ሶፊያም ወደ መስጂድነት ተቀየረች! የመጀመሪያው የጁምዓ ሶላትም እዚያው ተሰገደ!!!
📌አዲስ ስም⚡️
~~~
ከተማዋ #ኢስላምቡል” (የእስልምና ከተማ)የሚል ስም ተሰጣት፣ይህም በኋላ ወደ “ኢስታንቡል” ተቀየረ።
⚡️የድል አድራጊው ሰብዓዊነትና ፍትህ⚡️
========================
ሙሐመድ አል-ፋቲህ ከተማዋን ሲቆጣጠር ያሳየው ስነ-ምግባር በወቅቱ ለነበረው ዓለም አስገራሚ ነበር፦
📌የምህረት አዋጅ⚡️
~~~~
በአያ ሶፊያ ውስጥ ተሸሽገው በድንጋጤ ይንቀጠቀጡ ለነበሩ #ክርስቲያኖች “ወደ ቤታችሁ በሰላም ሂዱ፣ዛሬ በእናንተ ላይ ምንም ቅጣት የለም!ነፃነታችሁና ህይወታችሁ የተጠበቀ ነው!” የሚል የደህንነት ዋስትና ሰጣቸው‼
እስልምና እንድህ ነው!
📌የሃይማኖት ነጻነት⚡️
~~
የግሪክ #ኦርቶዶክስ_ቤተክርስቲያን_መሪ (Patriarch) እንዲመረጥ ፈቀደ! #የአይሁድና የሌሎች እምነት ተከታዮችም የራሳቸው ፍርድ ቤትና የሃይማኖት ነጻነት እንዲኖራቸው የሚያደርግ “የሚሌት ስርዓት (Millet System)” ዘረጋ!
📌ከተማዋን መልሶ መገንባት⚡️
~~
ጦርነቱ ያፈራረሳቸውን ህንጻዎች በፍጥነት እንዲጠገኑ አዘዘ።ከተለያዩ የዓለም ክፍሎች የእጅ ጥበብ ባለሙያዎችን፣ ነጋዴዎችንና ሳይንቲስቶችን ወደ ኢስታንቡል ጋበዘ።
⚡️የድሉ ውጤቶች(Global Impact):
የመካከለኛው ዘመን ማብቂያ⚡️
========================= የታሪክ ምሁራን የቁስጥንጥንያ መውደቅን የ"መካከለኛው ዘመን (Middle Ages)” ማብቂያና የ“ህዳሴ(Renaissance)” መጀመሪያ እንደሆነ ይቆጥሩታል።
📌የሐር መንገድ መዘጋት⚡️
~~~~
አውሮፓውያን ወደ ምስራቅ (ህንድና ቻይና) የሚወስደው የየብስ መንገድ በኦቶማን ቁጥጥር ስር ስለዋለ፣አዳዲስ የባህር መንገዶችን መፈለግ ጀመሩ(ይህም የአሜሪካን መገኘት መንገድ ከፍቷል)።
📌የእስልምና የበላይነት⚡️
~~~~
ለዘመናት ሙስሊሞች ሲመኙት የነበረው ትንቢት በመፈፀሙ፣የኡስማንያ ግዛት በሙስሊሙ ዓለም ላይ ያለው ክብርና ተሰሚነት ከፍተኛ ሆነ።
 
📌ክፍል አራት፡የሥልጣኔ ግንባታ፣ ሌሎች ድሎች እና የሱልጣኑ ሕልፈት📌
⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️
የቁስጥንጥንያ ድል የሱልጣን ሙሐመድ አል-ፋቲህ የጉዞ መጀመሪያ እንጂ መጨረሻ አልነበረም።በቀሪው የንግስና ዘመኑ ግዛቱን በማስፋፋትና የዓለም የሳይንስ ማዕከል በማድረግ አሳልፏል።
 
⚡️ግዛቱን የማስፋፋት ስራዎች⚡️
=========================
ከቁስጥንጥንያ ድል በኋላ ለቀጣዮቹ 28 ዓመታት ሱልጣኑ ሳይያርፍ ተዋግቷል።ዋና ዋናዎቹም፡-
📌የባልካን አገራት ድል⚡️
~~
ሰርቢያን፣ቦስኒያን እና አልባንያን በሙሉ በቁጥጥሩ ስር አደረገ።
📌የጥቁር ባህር ቁጥጥር⚡️
~~~~
የክራይሚያን ባሕረ ገብ መሬት በማሸነፍ ጥቁር ባህርን “የኦቶማን ባህር” አደረጋት።
📌ወደ ጣሊያን ያደረገው ጉዞ⚡️~~~~የሱልጣኑ ትልቁ ህልም #ሮምን መያዝ ነበር።በ1480 እ.ኤ.አ የጣሊያኗን #ኦትራንቶ(Otranto) ከተማ ተቆጣጠረ።ሆኖም ወደ ሮም ለመጓዝ ሲዘጋጅ ህይወቱ በማለፉ የሮም መያዝ ሳይሳካ ቀረ።
https://t.me/Seyfel_Islam
 
📚የሳይንስና የጥበብ ሰው🌱📚
=========================
ሙሐመድ አል-ፋቲህ ተራ ተዋጊ ሱልጣን ብቻ አልነበረም።ይልቁንም ለእውቀትና ለጥበብ ትልቅ ቦታ የሚሰጥ የጥበብ ሰውም ነበር።
⚡️በኢስታንቡል ውስጥ በወቅቱ የነበሩትን ከፍተኛ የሳይንስና የሃይማኖት ትምህርቶችን የሚሰጡ ዩኒቨርሲቲዎችን መሰረተ።
📌የቤተ-መጻሕፍት ፍቅር⚡️
~~~
በግሪክ፣በላቲን እና በፋርስ ቋንቋዎች የተጻፉ በሺዎች የሚቆጠሩ መጻሕፍትን ሰብስቧል።የአውሮፓ ሰዓሊያንን (ለምሳሌ፦ ጄንቲሌ ቤሊኒ) ወደ ቤተ-መንግስቱ በመጋበዝ ስነ-ጥበብን ያበረታታ ነበር።
📌የሕግ ማሻሻያ⚡️
~~
“ቃኑን ናሜ(Kanunname)” የተባለውን የሕግ መድብል በማዘጋጀት የኡስማንያን አስተዳደራዊ መዋቅር ዘመናዊ አደረገ።
⚡️የሱልጣኑ ሕልፈት(1481እ.ኤ.አ)
========================
ግንቦት 3 ቀን 1481 እ.ኤ.አ ሱልጣኑ ለሌላ አዲስ ወታደራዊ ዘመቻ ሰራዊቱን ይዞ ከወጣ በኋላ በመንገድ ላይ በድንገት ታመመ።
📌የህልፈቱ ምክንያቶች⚡️
~~~~
አንዳንዶች በህመም (Gout) ምክንያት እንደሞተ ሲናገሩ፣ሌሎች ደግሞ በሐኪሞቹ አማካኝነት #መርዝ ሳይሰጠው እንዳልቀረ በታሪክ ይገምታሉ።
ያም ሆነ ይህ በተወለደ ገና በ49 ዓመቱ እጅግ ታሪካዊ ጀብዱ ከፈፀመ እና የዓለምን ካርታ ከቀየረ በኋላ ወደማይቀረው አኼራ ሄደ።
إنالله وإنا إليه راجعون
 
📌የሱልጣኑ ሌጋሲ📌
⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️
ሙሐመድ አል-ፋቲህ በታሪክ ውስጥ የሚታወሰው በሚከተሉት ነጥቦች ነው፡-
📌የእምነት ምልክት⚡️
~
የነቢዩን (ሰ.ዐ.ወ) ትንቢት እውን በማድረጉ በሙስሊሙ ዓለም ትልቅ ክብር አለው።
📌የመቻቻል ምሳሌ⚡️
~
ድል አድራጊ ሆኖ ሳለ ለተሸናፊዎች ያሳየው ምህረትና የሃይማኖት ነጻነት ዛሬም ድረስ እንደ ምሳሌ ይጠቀሳል።
📌የኢስታንቡል መስራች⚡️
~~~~ኢስታንቡል የዓለም የንግድ፣የጥበብና የፖለቲካ ማዕከል እንድትሆን መሰረቱን የጣለው እርሱ ነው።
⚡️ማጠቃለያ⚡️
=====================
ሱልጣን ሙሐመድ አል-ፋቲህ የጥንካሬ፣ የዕውቀት እና የፍትህ ድምር ውጤት ነበር።
“መሬትን በሰይፍ፣ልብን ደግሞ በፍትህ የገዛ መሪ!”ይባላል።
 
⚡️የአሁኑ ሙስሊም ወጣት እና ታዳጊ ከሱልጣን ሙሐመድ አል-ፋቲህ ስብዕና እና የሕይወት ታሪክ ሊቀስሟቸው የሚገቡ እጅግ ጠቃሚና ወቅታዊ ቁም ነገሮች⚡️
=========================
📌ትልቅ ራዕይና ዓላማ መያዝ (Having a Vision)⚡️
🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱
ሙሐመድ አል-ፋቲህ ገና በልጅነቱ ነበር “ቁስጥንጥንያን እከፍታለሁ” የሚል ትልቅ ራዕይ የሰነቀው።
🔐ወጣቶች በጊዜያዊ መዝናኛ ብቻ ሳይወሰኑ፣ለሕይወታቸው ትልቅና ዓለምን የሚቀይር ግብ ሊኖራቸው ይገባል።ራዕይ የሌለው ወጣት ጉዞው አቅጣጫ እንደሌለው መርከብ ነው!
📌ሁለገብ ዕውቀትን መገብየት (Multidisciplinary Learning)⚡️
🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱
ፋቲህ ሃይማኖታዊ ዕውቀትን ከዘመናዊ ሳይንስ (ሒሳብ፣ ምህንድስና፣ ጂኦግራፊ) እና ከቋንቋ ጋር አጣምሮ ተምሯል።
🔐የዛሬ ወጣቶችም በአንድ ዘርፍ ብቻ ሳይወሰኑ ዕውቀታቸውን ማስፋት አለባቸው።በተለይም ቋንቋዎችን መማር ለዓለም አቀፍ ግንኙነት ያለውን ፋይዳ ከእርሱ መማር ይቻላል።
“አንድ ቋንቋ አንድ ሰው ነው” እንደሚባለው እርሱ 7 ቋንቋዎችን ማወቁ ለስኬቱ ቁልፍ ነበር!
📌 ለምሁራንና ለመምህራን ክብር መስጠት⚡️
🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱
ሙሐመድ አል-ፋቲህ ለታላቁ መምህሩ ለ አቅ ሸምሰዲን የነበረው አክብሮት እጅግ ከፍተኛ ነበር።ምንም እንኳ ንጉስ ቢሆንም በመምህሩ ፊት ትሁት ነበር።
🔐የዛሬው ትውልድም ዕውቀትን ከሚያስጨብጡት መምህራንና ታላላቅ ምሁራን ጋር ያለው ግንኙነት በአክብሮት ላይ የተመሰረተ መሆን አለበት።ስኬት የሚገኘው ከዕውቀት ጋር ስነ-ምግባር (አደብ) ሲታከልበት ነው!
📌ተስፋ አለመቁረጥና የፈጠራ ብልሃት (Innovation)⚡️
🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱
መርከቦቹን በየብስ ላይ እንዲጓዙ ያደረገበት ስልት “የማይቻል ነገር የለም!” የሚል ትልቅ ትምህርት ይሰጣል።ግንቡን ለመስበር የነበረው መድፍ ሳይሳካ ሲቀር ተስፋ ቆርጦ አልተመለሰም፤ይልቁንም አዲስ የመድፍ ቴክኖሎጂ ፈጠረ!
🔐የዛሬ ወጣቶችም በሕይወታቸው የሚያጋጥሟቸውን መሰናክሎች እንደ ማለቂያ ሳይሆን አዲስ የፈጠራ መንገድ መፈለጊያ አድርገው ሊጠቀሙባቸው ይገባል!
📌ስነ-ምግባርና መቻቻል (Character and Tolerance)⚡️
🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱
ከተማዋን ድል ካደረገ በኋላ በጠላቶቹ ላይ የበቀል እርምጃ አልወሰደም! ይልቁንም ለሃይማኖቶች ነጻነት ሰጠ፤ ለሰብዓዊ መብት ቅድሚያ ሰጠ።
🔐ኃይል ወይም ዕውቀት ሲገኝ በትዕቢት ከመወጠር ይልቅ ለሌሎች እውቅና መስጠት፣መቻቻልና ፍትሃዊ መሆን ለዘላቂ ስኬት ወሳኝ ነው!
📌በራስ መተማመንና የኃላፊነት ስሜት⚡️
🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱
በ19 ዓመቱ ግዙፍ ግዛት የመምራት ኃላፊነት ሲረከብ “ገና ወጣት ነኝ” ብሎ አልሸሸም።ይልቁንም በራሱና በፈጣሪው በመተማመን ኃላፊነቱን ተወጣ!
🔐ወጣቶች ዕድሜያቸውን ለኃላፊነት እንደ ማገጃ መጠቀም የለባቸውም።በቂ ዝግጅትና በራስ መተማመን ካለ በማንኛውም ዕድሜ ትልቅ ለውጥ ማምጣት ይቻላል‼
🌱በአጭሩ የሙሐመድ አል-ፋቲህ ሕይወት ለዛሬው ወጣት ዕውቀትን ከእምነት፣ጀግንነትን ከትሕትና እንዲሁም ራዕይን ከሥራ ጋር እንዴት አቀናጅቶ መጓዝ እንደሚቻል የሚያሳይ ታላቅ ትምህርት ቤት ነው!📌
 
#ማሳሰቢያ!
መግቢያ ላይ እንደጠቀስኩላችሁ የሱልጣኑን የሒጅራ አቆጣጠር የልደት ቀን በተመለከተ ሁለት አስተያየቶች(ረጀብ 26ኛው እና ጀማዱልኣኺር 26ኛው) ያሉ ሲሆን የሱልጣን ሙሐመድ አልፋቲህ የተወለዱት በዛሬው ቀን ጀማዱል ኣኺር 26ኛው ቀን ካሉ የታሪክ ምሁራን መካከል:
1ኛ: #አሕመድ_ቢን_ሉጥፉላህ ወይም በታሪክ “ሙነጂም ባሺ”
“ጃሚዕ አድ-ዱወል” በሚባል ታዋቂ መፅሐፋቸው
⚡️የኦቶማን መንግስት መዛግብት በብዙ የጥንት የኦቶማን ታሪክ ተመራማሪዎች በጠቀሱት መሠረት ጀማዱል ኣኺር 26 ነው!
⚡️ኢስማኢል ሐሚ ዳኒሽመንድ (Ismail Hami Danişmend) የተባሉት እጅግ ታዋቂ የጥንታዊ ቱርክ ታሪክ ፀሀፊ "Izahli Osmanli Tarihi Kronolojisi" (የኦቶማን ታሪክ የዘመን አቆጣጠር ማብራሪያ) በተባለው ዝነኛ መጽሐፉ፣የሱልጣኑን ልደት አስመልክቶ ያሉትን ልዩነቶች መርምሮ #ጀማዱል_ኣኺር_26፣835 ሂጅሪያ መሆኑን ፅፏል።
========================
✍𝓐𝓫𝓭𝓮𝓵𝓪𝔃𝓲𝔃 𝓑𝓲𝓷𝓜𝓾𝓱𝓪𝓶𝓶𝓮𝓭
(Seyfel Islam AlHabeshi)
ጀማዱል ኣኺር 26/1447
December 17/2025
ታህሳስ 8/2018
እንደዚህ ጠቃሚ ትምህርቶችን ለማግኘት በቴሌግራም ቤተሰብ ይሁኑ!👇
https://t.me/Seyfel_Islam
image
image
image
image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Seyfel Islam Сhanged his profile picture
1 week
Translation is not possible.
image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.
✨ የየመን እና የሻም (ሶርያ) ምድር በሐዲሦች ብርሃን ✨
فعن أبي هريرة عن النبي صلى الله عليه وسلم قال: أتاكم أهل اليمن هم أرق أفئدة وألين قلوبا الإيمان يمان والحكمة يمانية والفخر والخيلاء في أصحاب الإبل والسكينة والوقار في أهل الغنم. متفق عليه.
አቢ ሁረይረህ ረዲየሏሁ ዐንሁ ባስተላለፉት ሐዲስ ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል፦
"የየመን ሰዎች ወደ እናንተ መጥተዋል። እነርሱ ልባቸው በጣም ለስላሳ፣ ኅሊናቸውም እጅግ የረቀቀ ነው። እምነት የየመን ነው፣ ጥበብም የየመን ናት። ትዕቢትና ኩራት የግመል ባለቤቶች (የበረሃ ነዋሪዎች) ባሕሪ ሲሆን፣ ጸጥታና መከበር ግን የበግ ባለቤቶች (የየመን ሰዎች) ባሕሪ ነው።" (ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል)
ይህ ሐዲስ የየመን ሰዎችን ልስላሴ፣ የጥበብ ባለቤትነታቸውን እና የእምነት ጥንካሬያቸውን ያመላክታል።
وعن زيد بن ثابت قال: قال رسول الله صلى الله عليه وسلم: طوبى للشام قلنا لأي ذلك يا رسول الله؟ قال: لأن ملائكة الرحمن باسطة أجنحتها عليها. رواه أحمد والترمذي.
ዘይድ ኢብኑ ሳቢት (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት፣ የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ አሉ:-
"ለሻም ደስታ ይገባታል (ጡባ ሊሻም)!"
እኛም "የአሏህ መልእክተኛ ሆይ! በምን ምክንያት?" ብለን ስንጠይቅ፦
እርሳቸውም፦ "ምክንያቱም የአር-ረሕማን (የአዛኙ) መላእክት ክንፎቻቸውን በላዩ ላይ ዘርግተዋልና!" (አሕመድ እና ቲርሚዚይ ዘግበውታል።)
 
وعن ابن حوالة قال: قال رسول الله صلى الله عليه وسلم: سيصير الأمر إلى أن تكونوا جنودا مجندة جند بالشام وجند باليمن وجند بالعراق. فقال ابن حوالة خر لي يا رسول الله، إن أدركت ذلك، فقال: عليك بالشام فإنها خيرة الله من أرضه يجتبي إليها خيرته من عباده فأما إن أبيتم فعليكم بيمنكم واسقوا من غدركم فإن الله توكل لي بالشام وأهله. رواه أحمد وأبو داود والترمذي وصححه الألباني.
 
ኢብኑ ኸውላ (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት የአሏህ መልእክተኛ (ሰ.ዐወ) እንድህ አሉ:-
“ነገሩ ሁሉ ወደተሰባሰበ ጦርነት ይለወጣል።አንድ ጦር በሻም፣አንድ በየመን እና አንድም በዒራቅ ይሆናል!”
ኢብኑ ኸውላም“የአሏህ መልእክተኛ ሆይ!ያንን ዘመን ካገኘሁ የት እንድኖር ትመርጥልኛለህ?”ብሎ ጠየቀ።
እርሳቸውም መለሱ፦"ሻምን ያዝ! እርሷ የአሏህ ምርጥ ምድር ናትና!ከባሮቹ መካከል ምርጦቹን ወደ እርሷ ይሰበስባል።እምቢ ካላችሁ ደግሞ የመናችሁን ያዙና ከውሃ መቋጠሪያዎቻችሁ ጠጡ።አሏህ የሻምንና የሕዝቦቿን ነገር ተረክቦኛል።" (አሕመድ፣ አቡ ዳውድና ቲርሚዚይ ዘግበውታል)
وعن ابن عمر أن رسول الله صلى الله عليه وسلم قال: اللهم بارك لنا في شأمنا اللهم بارك لنا في يمننا، قالوا: وفي نجدنا، قال: اللهم بارك لنا في شأمنا وبارك لنا في يمننا، قالوا: وفي نجدنا، قال: هناك الزلازل والفتن وبها أو قال منها يخرج قرن الشيطان. رواه الترمذي وقال: هذا حديث حسن صحيح غريب من هذا الوجه. وقال الشيخ الألباني: صحيح.
 
ኢብኑ ዑመር (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት፣ ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል፦
"አላህ ሆይ! በሻማችን ላይ በረከትን አውርድልን። አላህ ሆይ! በየመናችን ላይ በረከትን አውርድልን።" (ቡኻሪ ዘግበውታል)
ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) ለሻምና ለየመን በረከትን ሲጠይቁ ባልደረቦቻቸው “በነጅዳችንስ (የመካና የመዲና መካከለኛ የምስራቅ ክፍል)?” ብለው በጠየቋቸው ጊዜ
"አላህ ሆይ! በሻማችን ላይ በረከትን አውርድልን፣ በየመናችንም ላይ በረከትን አውርድልን።" ሲሉ ደግመው መለሱ።
በድጋሚ ሲጠየቁም እንዲህ አሉ፦ "እዚያ የመሬት መንቀጥቀጦችና ፈተናዎች አሉ፣ የሰይጣን ቀንዶችም የሚወጡት ከዚያ ነው።" (ቲርሚዚይ ዘግበውታል
وعن أبي الدرداء قال: قال رسول الله صلى الله عليه وسلم: بينا أنا نائم إذ رأيت عمود الكتاب احتمل من تحت رأسي، فظننت أنه مذهوب به فأتبعته بصري، فعمد به إلى الشام، ألا وإن الإيمان حين تقع الفتن بالشام. رواه أحمد والطبراني وقال الهيثمي ورجال أحمد رجال الصحيح.
አቡ ደርዳእ (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል:-
"ተኝቼ ሳለሁ የኪታቡ(የእስልምና) ምሰሶ ከራሴ ስር ሲነሳ አየሁ። ተወስዶብኛል ብዬ አሰብኩና በዓይኖቼ ተከተልኩት።ሲሄድም ወደ ሻም አመራ። ንቁ!ፈተናዎች በሚከሰቱ ጊዜ እምነት የሚኖረው በሻም ውስጥ ነው!”(አሕመድና ጠበራኒ ዘግበውታል)
 
وعن عبد الله بن عمر قال: سمعت رسول الله صلى الله عليه وسلم يقول: تخرج نار من نحو حضرموت -أو من حضرموت- تسوق الناس. قلنا: يا رسول الله فما تأمرنا، قال: عليكم بالشام. رواه أبو يعلى وقال الهيثمي رجاله رجال الصحيح.
 
ዐብዱላህ ኢብኑ ዑመር (ረ.ዐ) የአሏህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ)የሚከተለውን መናገራቸውን አስተላልፈዋል:-
“ከሰዎች ሁሉ ወደ ሐድረመውት (የየመን ክፍል) አቅጣጫ - ወይንም ከሐድረመውት - ሰዎችን የምትነዳ እሳት ትወጣለች!”
እኛም“የአሏህ መልእክተኛ ሆይ!(በዚያን ጊዜ)ምን እንድናደርግ ታዘናለህ?”ብለን ጠየቅን።
እርሳቸውም፦“ሻምን አጥብቃችሁ ያዙ!” አሉን።(አቡየዕላ ዘግበውታል)
 
وعن أبي هريرة عن النبي صلى الله عليه وسلم قال: لا تزال عصابة من أمتي يقاتلون على أبواب دمشق وما حوله، وعلى أبواب بيت المقدس وما حوله، لا يضرهم خذلان من خذلهم، ظاهرين على الحق إلى أن تقوم الساعة. رواه أبو يعلى وقال الهيثمي رجاله ثقات.
 
አቡ ሁረይራህ (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት፣ ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ)እንድህ ብለዋል:-
"ከኡመቴ(ከሕዝቦቼ)የሆነ ቡድን በደማስቆ ደጆችና በዙሪያዋ፣ እንዲሁም በይተል መቅዲስ ደጆችና በዙሪያዋ ላይ ሆነው ከመዋጋት አይወገዱም።የተዋቸው ሰው መተው ምንም አይጎዳቸውም፤እስከ ትንሣኤ ቀን ድረስ በሐቅ ላይ ግልጽ ሆነው ይቀጥላሉ!”
(አቡየዕላ ዘግበውታል)
✍️ Seyfel Islam AlHabeshi
https://t.me/Seyfel_Islam
Telegram: View @Seyfel_Islam

Telegram: View @Seyfel_Islam

قال ابن تيمية -رحمه الله-: {قوام الدين كتاب يهدي وسيف ينصر وكفى بربك هادياونصيرا} مجموع الفتاوى [10/13] ሙስሊሞችን ለሚመለከቱ ወቅታዊ መረጃዎች ቤተሰብ ይሁኑን
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.
#አስደሳች_ሰበር_ዜና፡-
#بشرى_سارة
የተከበሩ ሸይኽ ዶ/ር #ሷሊህ_ቢን_ፈውዛን_ቢን_ዐብዱሏህ_ቢን_አልፈውዛን የሳዑዲ ዓረቢያ #ታላቅ_ሙፍቲ፤የከፍተኛ ዑለማኦች ምክር ቤት #ፕሬዝዳንት እና #በሚኒስተር ማዕረግ የምሁራን ጥናትና ምርምር #ሀላፊ ሆነው #ተሹመዋል!
አሏሁ አክበር!!
https://t.me/TewhidFirstAlways
image
Send as a message
Share on my page
Share in the group