UMMA TOKEN INVESTOR

Translation is not possible.
شهر رمضان هو شهر مبارك، وفيه فرصة عظيمة للتزود بالطاعات والتقرب إلى الله. إليك بعض النصائح التي يمكن أن تساعدك على الاستعداد لدخول رمضان بشكل جيد:
1. **التوبة الصادقة**: استقبل رمضان بتوبة صادقة من جميع الذنوب والمعاصي، واعزم على عدم العودة إليها.
2. **الاستعداد النفسي**: هيئ نفسك لاستقبال الشهر الكريم بالفرح والسرور، وتذكر فضائله العظيمة.
3. **تنظيم الوقت**: خطط لوقتك في رمضان بحيث تحافظ على الصلوات، وتلاوة القرآن، والدعاء، والأعمال الصالحة الأخرى.
4. **قراءة القرآن**: ابدأ بتلاوة القرآن بانتظام، وحاول أن تختمه خلال الشهر إن استطعت.
5. **الصيام التطوعي**: يمكنك أن تصوم بعض الأيام في شعبان لتتهيأ لصيام رمضان.
6. **التدريب على القيام**: حاول أن تعتاد على قيام الليل من الآن، حتى تستطيع المحافظة على صلاة التراويح في رمضان.
7. **التصدق**: أكثر من الصدقات، ومساعدة المحتاجين، ففي رمضان تزداد الحسنات.
8. **الدعاء**: ادع الله أن يبلغك رمضان وأنت في صحة وعافية، وأن يتقبل منا ومنك الصيام والقيام.
9. **التعرف على أحكام الصيام**: تعلم أحكام الصيام وما يتعلق به من أمور فقهية حتى تصوم بشكل صحيح.
10. **التواصل مع الأهل والأصدقاء**: حاول أن تجعل رمضان فرصة لتقوية العلاقات مع الأهل والأصدقاء، وتشجيعهم على الطاعة.
11. **التقليل من المشتتات**: قلل من الوقت الذي تقضيه في الأمور التي لا تفيد، مثل مشاهدة التلفاز أو استخدام الهاتف لفترات طويلة.
12. **الاستعداد الصحي**: حاول أن تعد جسمك للصيام بتناول الطعام الصحي، وتقليل الكافيين والسكريات قبل رمضان.
أسأل الله أن يبلغنا وإياكم رمضان، وأن يتقبل منا الصيام والقيام، وأن يجعلنا من عتقائه من النار.
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.
━━━━━━✦✿✦━━━━━━
#ከጀግኖቹ ጀርባ እነማን ነበሩ? 1
━━━━━━✦✿✦━━━━━━
#የሙሐመድ_አልፋቲህ እናት ዘወትር ማለዳ እጁን አጥብቃ ጨብጣ ረዥም ርቀቶችን ተጉዛ የቆስጠንጢኒያን አጥሮች እያሳየችው "ልጄ ሆይ! የቆስጠንጢኒያ አጥር ይታይሀል ያ እሱ ነው አዎ ያ የቆስጠንጢኒያ አጥር ነው ድል አድርገህ የምትከፍተውም አንተ ነህ" እያለች ግብና ዓላማውን ከፍ አድርጎ እንዲያስብ አድርጋ ኮትኩታ አሳደገችው።
እሱም አላሳፈራትም።
ይህቺን ከተማ ለመክፈት 23 ጊዜ የሙስሊሞች ሠራዊት ዘመተ። ግና እጅግ ጠንካራ በሆኑ ግንቦች እና በጣም በሰለጠኑ የሮም ባይዛንታይን ወታደሮች የምትጠበቀውን የምስራቅ ሮማ ዋና ከተማ ኮንስታንትኖፕልን መክፈት አንዳቸውም አልተሳካላቸውም ነበር።
#በ12 ዓመቱ የዑስማኒያን ኺላፋ ሥልጣን የተረከበው ተዓምረኛው ሙሐመድ አልፋቲህ ባይዛንታይኖች ቆስጠንጢኒያን ለመከላከል ባህሩን በሰንሰለት ባጠሩት ጊዜ 70 መርከቦች ተሰርተው በየብስ ተጎትተው #golden Hore ወደተሰኘው ከተማ እንዲገቡ አዘዘ። በዚህ ጊዜ እንዴት ይህ ይቻላል እንዴት መርከብ በየብስ ላይ ይጓዛል?! በማለት የጦር መሪዎቹ ጥያቄ አነሱ። ሙሐመድ አልፋቲህም እንዲህ አለ:- "#የመቻል_ጥግ_እስከየት_እንደሆነ_ለማየት_የማይቻለውን_መሞከር_አለባችሁ_እናቴ_በዓላማ_ፅናት_ላይ_አንፃ_አሳድጋኛለችና\\"
#በአልፋቲህ ድል አድራጊነት ቆስጠንጢኒያ ተከፍታ የዓለም ኃያልነት በሙስሊሞቹ ኺላፋ በኦቶማን እጅ ሙሉ ለሙሉ ገባ። ከዚያ በኋላ ምስራቅ እና ደቡብ አውሮፓ በሙሉ በሙስሊሞች ቁጥጥር ስር ዋሉ።
#ሙሐመድ አልፋቲህ ይህን ሁሉ ገድል ሲፈፅም #ዕድሜው 21 ነበር። እርሱ በዚያ ለጋ እድሜው ከዓለማችን የምንጊዜም ኃያል መሪዎች ውስጥ
አንዱ ለመሆን በቃ።
አላህ ይተካቸው
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.
የታሉ እነዛ ሙስሊሞች
━━━━━━✦✿✦━━━━━━
#አስራ_አምስት_ሺ_ከፈን_የለበሱ_ሰራዊቶች
━━━━━━✦✿✦━━━━━━
ዘመኑ እንደ ሂጅራ አቆጣጠር በ463 ዓመት የተከሰተ ነው። የምስራቅ ሮማ ባይዛንታይን ኢምፓየር የሙስሊም ግዛቶችን ለመቆጣጠር በተደጋጋሚ የፈፀመው ወረራ በሰልጁቅ ቱርኮች እየተደመሰሰ ግዛቱን መነጠቅ ጀመረ። ሮማኖስ ዳዮጌኔስ ወደ ስልጣን መጣ። ሮማኖስ ከሙስሊሞች ጋር የገባውን የሰላም ስምምነትን ለማደስ ለሙሐመድ አልብ አርስላን ልዑካንን ላከ። ሮማኖስ ይህን ያደረገው የሙስሊሞቹን የሰልጁቅ ቱርክ ጦር ለማዘናጋት ነበር።
ይህንን የሰላም ስምምነት በማድረጉ አልብ አርሰላን ፊቱን ወደ ግብፅ አዞረ። የሺዓ ኸላፋ የነበረውን የግብፁን ፋጢሚድ ዳይናስቲ ለመደምሰስ ጦሩን ይዞ ጉዞውን ወደ ሶሪያ አቅጣጫ አመራ። በሺዓው ፋጢሚድ ስር የነበረችውን ሐለብን ነፃ አወጥቶ በሐለብ ጦሩን አሳረፈ።
ሮማኖስ ባይዛንታይን 300,000 (ሶስት መቶ ሺህ) ጦሩን አስከትሎ የሙስሊሞችን ሀገር ኢራቅን፣ ኢራንንና ሶሪያን ጨምሮ አብዛኛውን የሙስሊም ግዛት ለመቆጣጠር ወደ ምስራቅ ተመመ። የባይዛንታይ የዘመቻ እንቅስቃሴ ለአልብ አርሰላን ደረሰው። ከፋጢሚዮች ጋር ሊያደርግ የነበረውን ጦርነት ትቶ ወደ ምስራቅ ኢፍራጠስ ወንዝ ጦሩን አዞረ።
ታላቁ የሙጃሒዶች መሪ አልብ አርስላን ጥቂት ቁጥር ያለውን ጦሩን ከ300,000 የባይዛንታይን ሮም ሰራዊት ጋር ይዋጋ ዘንድ ለጂሃድ አዘጋጀ።
ቀኑ ጁሙዐ ነበር። ታላቁ ኢማም አቡነስር ሙሀመድ ኢብን አብዱልመሊክ አልቡኻሪ ከሚንበር ላይ ወጡ ስለ ጂሃድ ኹጥባ አደረጉ። ሙጃሒድ አላህ ዘንድ ያለውን ደረጃ፣ ሸሂዶች ከአላህ ዘንድ ያላቸውን ምንዳ አወሱ። ስለኢስላም ተጋደሉ አላህም ሊረዳችሁ ቃል ገብቷል አሏቸው። አላህ የድል ባለቤት እንዲያደርጋቸውም ዱዓ አደረጉላቸው። ሁኔታው ሁሉ የሰሐቦች ዘመን ይመስላል። እነዚያ 15,000 የአላህ ሙጃሂዶች በእርሱ መንገድ ሸሂድ ሊሆኑ ጓጉተዋል።
ሱልጣን ሙሐመድ አልብ አርስላን ከፈኑን ለብሶ ወጣ። ወደ እነዚያ የአላህ ሙጃሂዶች ፊቱን አዙሮ "ዋ ኢስላማ! ዛሬ እስልምና አደጋ ላይ ወድቋል! ላኢላሀኢለሏህ ከምድር ገፅ ላይ እንዳትጠፋ እፈራለሁ እኔን የሚመስል ይከተለኝ" አላቸውና ስቅስቅ ብሎ አለቀሰ። ሁሉም በእንባ ተራጩ
"በአላህ መንገድ ሸሂድ መሆን የፈለገ ብቻ ይከተለኝ" አላቸው እኔ ዛሬ የእናንተ አዛዥ አይደለሁም። ስለአላህ ዲን መዋጋት ግዴታ የተደረገው በኔ ላይ ብቻ አይደለም በሁላችንም እንጂ ስለአላህ ዲን በማገልገል ላይ ሁላችንም እኩል ነን። ለህይወቱ ቅንጣት ታክል የሚፈራ ካለ አይከተለኝ። ነፃነቱን ሰጥቼዋለሁና መመለስ ይችላል። እኔ ሸሂድነትን ናፍቄያለሁ ከሞትኩ በዚህ በያዝኩት ከፈን ቅበሩኝና በአላህ መንገድ መዋጋታችሁን ቀጥሉ። እኔ በጦርነቱ ስሰዋ ልጄ መሊክሻህ የጦር አመራርነቱን ይረከብ" አላቸው። ሁሉም በእንባ ተራጩ በተክቢራ ድምፅ ምድር ተናወጠች።
አስራ አምስር ሺህ ሰራዊት ከፈኑን ለበሰ። ከ300,000 መስቀላዊያንን ሊገጥም ወደ ማንዚከርት (መላዝከርድ) መ ዳ ተጓዘ።
300,000 የሚሆነው የሮም ሰራዊት የተውጣጣው ከሩሲያ፣ ከኡጉዝ፣ ከካውካሰስ፣ ከኻዛርስ፣ ፈረንሳይና ከአርሜኒያ ሲሆን የአልብ አርስላን ጦር ግን 4,000 ልዩ ጦር እና 11,000 ተራ ጦር ሲሆን ሁሉም ቱርካዊያን ናቸው ።
#የጦርነቱ_ፍልሚያ
የሱልጣኑ ሰላዮች የሮማኖስ ጦር ያለበትን ቦታ ብዛቱን አጠቃላይ እንቅስቃሴውን በሚገባ አውቀዋል። ሮማኖስ ጦሩን በአህላድ እና ማንዚክርት መካከል በሚገኝ አል-ራህዋ በሚባል ቦታ አሰፈረ። የሱልጣኑ ጦር ወደ እርሱ እያመራ መሆኑን አላወቀም።
ሮማኖስ በ ጄኔራሉ የሚመራ 60,000 ጦር ቀድሞ ያጠቃ ዘንድ አዘዘ። ሱልጣን አልብ አርስላን ይህንን ያውቅ ነበርና ለጄነራሉ ወጥመድ አዘጋጅቶ ጠበቀው። ከዚያ በኋላ ስልሳ ሺህ ጦር በተዘጋለት ወጥመድ ገብቶ ሁሉም አለቁ። ጄኔራሉም ተማረከ። ይህ ሁሉ ሲሆን ንጉስ ሮማኖስ ምንም የደረሰው መረጃ አልነበረም።
ቀሪ 240,000 ሰራዊቱን ይዞ በማንዚክሪት 15,000 ከያዘው የአልብ አርስላን ጦር ጋር ተጋጠመ። አልብ አርስላንም ጦሩን ከፊት እየመራ በጀግንነት ተጋደለ። ሰልጁቆች እጅግ የሚታወቁበትን የቱርክ የጦር ስልት መጠቀም ጀመሩ።
የተወሰኑ የቱርክ ተዋጊዎች ወደ ጦርነቱ ይዘልቁና ከዚያ ወደኋላ ያፈገፍጋሉ በዚህ ጊዜ ባይዛንታይኖች ቱርኮቹ አፈገፈጉ ብለው ስለሚያስቡ ይከተሏቸዋል። ነገር ግን ቱርኮቹ አብዛኛውን ጦራቸውን ከጦር ሜዳው ቅርብ ላይ ነው ደብቀው የሚያስቀምጡት። የሮም ባይዛንታይን ጦር ግዙፍና በመሳሪያም የተደራጀ ስለሆነ በፍጥነት ደርሶ የሚያፈገፍጉትን ሙስሊሞች ሊወጋቸው ይቸገራል። በዚህ መሀል የተደበቀው የሙስሊም ጦር ይወጣና በቀስትና በጦር ግዙፉን የሮም ጦር ደመሰሰው።
እንደዚህ እያደረጉ 15,000 ሰራዊቶች 300,000 የሚሆነው የሮም ክርስቲያን ሰራዊት ደመሰሱት ። ሙስሊሞችን ከምድር ገፅ ሊያጠፋ የዛተው ሮማኖስም ተማረከ።
ላኢላሀ ኢለላህን ለመታደግ ከፈኑን ለብሶ የወጣው እጅግ አነስተኛ ቁጥር ያለው ሰራዊት ከእርሱ በ20 እጥፍ የሚበልጠውን የጠላት ሰራዊት ደመሰሰ።
ከድሉ በኋላ የሙስሊሞች ታላቁ ኸላፋ ለአልብ አርስላን "የዐረቡም የአጀሙም ታላቁ ሱልጣን" ሲል አድናቆቱንና ለኢስላምም ለሰራው ገድል ምስጋናውን ላከለት።
ኢምፔሬር ሮማኖስ ተማርኮ ከሱልጣኑ ፊት ቀረበ። ሱልጣን አልብ አርስላን ለሮማኖስ "የተማረኩት እኔ የማረከኝ ደግሞ አንተ ሆነህ ቢሆን ምን ታደርገኝ ነበር?" ሲል ጠየቀው።
ሮማኖስም "ወይ እገድልሀለሁ ያ ካልሆነ እየጎተትኩህ በኮንስታንትኖፕል ጎዳናዎች ላይ እያስዞርኩ መሳቂያ መሳለቂያ አደርግሃለሁ" አለው። በዚህ ጊዜ ሱልጣኑ ለሮማኖስ "አሁን እኔን ምን ያደርገኛል ብለህ ታስባለህ?" ሲል ዳግም ጠየቀው። ሮማኖስም "ሶስት አማራጮች አሉህ አንደኛው ትገድለኛለህ ሁለተኛው ደግሞ በሀገርህ እያዞርክ የድልህ ማንፀባረቂያ ታደርገኛለህ። ሶስተኛውን ይቅር ብለከኝ ካሳዬንም ትቀበለኛለህ" አለው።
ሱልጧን አልብ አርስላን ሶስተኛውን ይቅር ብዬሀለሁ አለው።
1.5 ሚሊዮን ዲናር ካሳ ሊከፍል ተስማምተው ሮማኖስ ወደ ኮንስታንትኖፕል ተመለሰ። እዚያ ሲደርስ የባይዛንታይን መሪዎች ከስልጣኑ አውርደው ዓይኑን አጠፉት። ሮማኖስ የእስልምናን መሀሪነት አዛኝነት እና ይቅር ባይነት ይዞ ለሮሞችም ሊነግራቸው ቢቋምጥም አልፈቀዱለትም።
ሮማኖስ ያን የተስማማውን የካሳ ክፍያ ማግኘትም አልቻለም። ለአልብ አርስላንም ደብዳቤ ላከለት "ኢምፔሬር በነበርኩበት ጊዜ የ 1.5 ሚሊዮን ዲናር ካሳ ተስማምቼ ነበር። ግና ከስልጣኔ ተባረርኩ። የሌሎች ጥገኛም ሆንኩ። ለምስጋና ያክል ብቻ እንደምንም ያሰባሰብኳትን ልኬልሃለሁ" በማለት።
ሮማኖስ በጊዜው ለካሳ የላከው 300,000 ዲናር ብቻ ነበር።
━━━━━✦✿✦━━━━━
💎💎አላማችን 💎💎
#የላኢላሃ_ኢለሏህ_ባንዲራን_ከፍ_ማድረግ_ነው።
#ሼር_በማድረግ_ለወዳጅ_ዘመድዎ_ያዳርሱ።
ከማይቋረጠው አጅር ተካፋይ ይሁኑ
የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ።
#ኢኽላስ - #ታማኝነት - #ትጋት - #ስኬት
#zubeyr379
Send as a message
Share on my page
Share in the group
zubeyr378 Сhanged his profile picture
1 years
Translation is not possible.
image
Send as a message
Share on my page
Share in the group