UMMA TOKEN INVESTOR

Хьо дакъа дацанаш махь йоьтта.

ሰለዋት እንድናበዛበት የታዘዝነው ነብይ ጀግንነቱ ሲወሳ

❀በአንድ ለሊት ላይ መዲና በጩኸት ተናወጠች። ሰሓባው ሁሉ ወደዚያ ድምፅ እየተንጋጋ አመራ። መጀመሪያ በቦታው ላይ ደርሶ አረጋግቶ እየተመለሰ ያገኙት ረሱልን ﷺነበር። አነስ (ረዐ) ይህን ሲተርክ እንዲህ ይላል፦

«የአላህ መልእክተኛ ﷺ ከሰዎች ሁሉ መልካሙና ጀግናው ነበር ።የመዲና ነዋሪዎች የሆነች ለሊት ላይ ደነገጡ። ወደ (ረብሻው) ድምፅም ወጡ።የአላህ መልእክተኛም ዜናውን አረጋግጠው (አብርደው) አገኟቸው። በአቡ ጠልሓ ፈረስ ላይ ነበሩ።እርሱም ኮርቻ ያልተገጠመለት ነበር። ሰይፋቸውን ከፍ አድርገው «አትፍሩ ፤አትደንግጡ!» አሉ»

(ቡኻሪይ 3040)

ሰሃቦች ወደ ድምፁ እየሄዱ ነው። ረሱልﷺ ግን ከድምፁ ቦታ እየተመለሱ!የህዝብ መሪ እንዲህ ነዋ!

አነስ (ረዐ) ኮርቻ ያልተገጠመለት ሲል ማለት የፈለገው በአደጋ ጊዜ ፕሮቶኮል ሳያበዛ ራስን ለመፍትሄ አቻኩሎ መብረርን ለመግለፅ ነው። ልክ በአስቸኳይ ችግር ጊዜ ሄልሜት ምናምን ሳትፈልግ ሞተር አስነስቶ እንደ መክነፍ።

❀በታላላቅ ፍልሚያዎች ላይ ረሱል ﷺ የጠላት ታርጌት ቢሆኑም እርሳቸው ግን ማንነታቸውን ሳይደብቁ ስማቸውን ሁሉ በግልፅ እየተናገሩ ወደፊት ይገሰግሱ ነበር።ከነዚህ ማሳያዎች አንዱ የሑነይን ዘመቻ ነው።

በዚህ ዘመቻ የሀዋዚን ጎሳ ቀስቶች ከባድ ስለነበሩ ሰሃባዎች ሸሽተዋል።

«ለበራእ ኢብኑ ዓዚብ (ረዐ) «የሑነይን እለት ሸሽታችኋል?» ተብሎ ተጠየቀ።እርሱም «የአላህ መልእክተኛﷺ በጭራሽ አልሸሹም ነበር። አቡሱፍያን ኢብኑል ሓሪስ የበቅሏቸውን ልጓም ይዞላቸው ነበር። ሙሽሪኮች ሲከቧቸው ወረዱና «እኔ ነብዩ ነኝ ውሸት አይደለም! እኔ የዐብደል ሙጠሊብ ነኝ!» አሏቸው። የዚያን ቀን  ከርሳቸው የበለጠ ብርቱ (ጀግና) ሰው አልታየም»

(ቡኻሪይ 3042)

❀100% ሞት በሚጠረጠርበት ቦታ ላይ ጀግንነትን እና በአላህ ላይ እርግጠኝነትን አረጋግጠዋል!

ጃቢር (ረዐ) ይተርካል ፦

« ከአላህ መልእክተኛ ﷺ ጋር የነጅድን ዘመቻ ተካፈልን። የቀትር እንቅልፍ ሰአት ላይ ሲደርሱ ዛፋማ በሆነ ደን ውስጥ ሳሉ ከአንዲት ዛፍ ጥላ ስር አረፉ።

ሰይፋቸውንም አንጠለጠሉና በጥላዋ ተጠለሉ። ሰዎችም በየዛፉ ስር ተለያይተው ተጠለሉ። በዚህ ሁኔታ ሳለን ድንገት የአላህ መልእክተኛ ﷺ ጠሩንና ሄድን።አንድ ገጠሬ ከፊት ለፊታቸው ተቀምጧል። እንዲህ አሉን፦

«ይህ ሰው ተኝቼ ሳለሁ መጥቶ ሰይፌን መዘዘ። ስነቃም በስለቱ በኩል ይዞት ጭንቅላቴ ላይ ቆሟል። «ከኔ ማን ያድንሃል?» አለኝ። እኔም «አላህ!» አልኩት ።ሰይፉን ወደሰገባው አስገባውና ተቀመጠ ፤ እርሱም ይሄ ነው» አሉ። »   (ቡኻሪይ 4139)

ሰይፉን በስለቱ (በፍላፃው) በኩል መያዙን የገለፁት ሰውዬው ከምላሻቸው በኋላ መግደል የሚችልበት አቋም ላይ መሆኑን የሚያሳይ ነው። የተቀባበለ ሽጉጥ ላይ ጣቱን ምላጩ  ላይ ያደረገ ሽፍታ ፊት በየመን ደን ውስጥ ሆነህ ምን ልትመልስ እንደምትችል መሳል ነው።

ይህ የጀግንነትና የየቂን ጥግ ካልሆነ እዚህ ምድር ላይ ጀግንነት የለም!

❀በጦርነት መሃል የመሳሪያ ነውጥ ድብልቅልቅ ሲል ሰዎች ካጠገቡ የሚሸሸጉበት ነብይ፦

ዐሊይ ኢብኑ አቢ ጣሊብ (ረዐ) እንዲህ ይላል፦

«ጦርነት ሲጋጋምና ሰው ለሰው ሲተላለቅ በአላህ መልእክተኛ ﷺ እንሸሸግ ነበር።ከኛ አንድም ሰው ወደ ጠላት ቅርብ የሚሆን የለም እርሳቸው ቢሆኑ እንጂ።»

(ሙስነዱ አሕመድ 1347)

ሰሃባዎች ከጀርባው የሚከለሉ ከሆነ አስከላዩ  ከጠላት ፊት ለፊት እየተጋፈጠ ነው ማለት ነው። እርሱ የዐብደላህ ልጅ ሙሐመድ ነው!  ሰለዋቱ ረቢ ወሰላሙሁ ዐለይሂ! 

❀በመካው ዘመን ቢሆንም አዛዎችን ሁሉ ታግሰው ያሳለፉት እንዲታገሱ ስለታዘዙ እንጅ የፍርሃት አልነበረም ።የዚህም ማረጋገጫው ፦

«የአላህ መልእክተኛ ﷺ ከመስጅድ (ሐረም) እየወጡ ሳለ አቡ ጀህል ከፊት ለፊታቸው መጣ ። መልእክተኛውﷺ እጁን ያዙትና አንድ ወይም ሁለት ጊዜ ወዘወዙት፤  ወየውልህ ከዚያም ወየውልህ! አሉት። እርሱም «ታስፈራራኛለህ? እኔኮ የዚህ(የመካ) ሸለቆ ሊቅና የተከበርኩ ሰው ነኝ»  አላቸው ።

(ተፍሲሩል ቁርጡቢይ) 

የቱ ጀግና ነው? አንድም የሚጠጋበት ሃይል ሳይኖረው የሀገር አስተዳዳሪን ወዝውዞ የሚዝትበት? !

❀ጠላት ህዝብን ብቻውን የተጋፈጠ ነብይ ፦

ረሱልﷺ የመካን ህዝብ በብቸኛነት የዳዕዋ ስራ ተጋፍጠዋል።ጥሪያቸውን የሚጠሉ መሪዎች ፊት ለአላህ ሱጁድ ያደርጉና ይሰግዱ ነበር።ይህ የድፍረትና የጀግንነት ጥግ እንጂ ሌላ አይደለም።

አነስ (ረዐ) ይተርካል ፦

«የአላህ መልእክተኛን ﷺአንድ ቀን (ሙሽሪኮች) ደበደቧቸው ራሳቸውን እስኪስቱ ድረስ።አቡበክርም ቆመና እየተጣራ መጣ፤ ወየውላችሁ አንድን ሰው ጌታዬ አላህ ነው ስላለ ትገድሉታላችሁ??!» አላቸው።ማነው ይሄ ደግሞ ? በማለት ተጠያየቁ። እብዱ አቡበክር ነው ተባባሉ»

(ዘዋኢዱ ፈዳኢሉ ሰሃባህ 218)

የረሱል ﷺጀግንነት ብቻቸውን ሆነው የከተማን ህዝብ ነው የተጋፈጡት! ይህ የድፍረት ውሃ ልክ እንጅ ሌላ አይደለም።አቡበክርን ተማምነው ነው እንዳይባል አቡበክር ራሱ የደረሰላቸው ራሳቸውን ስተው ነው።

ይህ ማለት ረሱል ﷺ የተጋፈጡት ብቻቸውን ነው! በመካው ህይወታቸው ትእግስት ያየለው በአላህ ትእዛዝ መሰረት እንጅ ከፍርሃት አለመሆኑን ማረጋገጫም ነው።

በዚህ ክስተት አቡበክር ለረሱል ﷺአግዞ  እስከመጨረሻው ከህዝብ ጋር ተፋልሟል።አቡከክር ሙሽሪኮች ፀጉሩን እስኪነጫጩት ድረስ ታግሉ ራሱን ስቷል።

ከነዚህ ውጭ የረሱል ጀግንነት የተገለጡባቸው ክስተቶችም አሉ። አላህ በጀነት የርሳቸው ጎረቤት ያድርገን!

❀በእናታችን ዓኢሻህ ንግግር እንጨርስ። እናታችን (ረዐ) እንዲህ ትላለች፦

«የአላህ መልእክተኛ ﷺ አገልጋያቸውን ወይም ሴትን ወይም ሌላን ነገር በጭራሽ መትተው አያውቁም።በአላህ መንገድ ትግል ላይ ካልሆነ በቀር።ከርሳቸውም በክብራቸው ተመጥቶባቸው ተበቅለው አያውቁም።የአላህ ድንበር ከተጣሰ ሲቀር (ያኔ) ለአላህ ዐዝዘ ወጀል ይበቀላሉ»

(ሙስሊም 2328)

የረሱልን ባህሪ በከፊሉ አምነህ በከፊሉ አትካድ! ረሱል ለሚታዘንለት አዛኝ ለሚቀላው ደግሞ ሰያፍ ነበሩ!

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Хьо дакъа дацанаш махь йоьтта.

የአልቃሳም ብርጌዶች ቃል አቀባይ አቡ ዑበይዳ ከተናገሩት ዋና ዋና ነገሮች፡-

⭕️ ሙጃሂዶቻችን በአስር ግንባሮች ከጽዮናውያን ጦር ጋር እየተፋለሙ ይገኛል።

⭕️ ታንኮችን አውድመናል የጦር መሪዎችን ማርከናል የበዙ የጠላት ወታደሮችን ገድለናል አቁስለናልም።

⭕️ ከጠላት ኋላ ተነስተን ከመከላከል ወደ ማጥቃት ተሸጋግረናል።

⭕️ ዛሬ ማምሻውን ከጋዛ ከተማ በስተሰሜንና በስተምዕራብ በኩል የመልሶ ማጥቃት ዘመቻ ከፍተን 6 ታንኮችንና ሁለት የሰው ኃይል አጓጓዥ መኪናዎችን አውድመናል።

⭕️ የሟቾች ቁጥር የጽዮናዊያኑ ሚዲያ ከጠቀሰው እጅግ የላቀ ነው።

⭕️ "ነብር" የተሰኘውን የጠላት የሰው ኃይል ተሸካሚ ጦር ለማውደም በሚሳኤሎቻችን ባደረግነው የመጀመሪያ ሙከራ ዶግ አመድ ማድረግ ችለናል።

⭕️ በርካታ ወታደሮቻችሁ በጥቁር ከረጢት ተሸፍነው ሲመለሱ ጋዛን በጽዮናዊያኑ ላይ የታሪክ እርግማን እናደርግባቸዋለን የሚለው ንግግራችንን በሚገባ ታስታውሱታላችሁ።

⭕️ በሺዎች የሚቆጠሩ ወገኖቻችንን በሞት ማጣታችንና በሰማዕትነት መገደላቸው ህመማችንን ዋጥ አድርገን ለከባድ መስዋዕትነት እንድንዘጋጅ ጉልበት ሆኖናል።

የሃማስ ንቅናቄ ኦፊሴላዊ ድህረ-ገጽ

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Хьо дакъа дацанаш махь йоьтта.

መህዲ ማነው?

‹‹መህዲ›› በመጨረሻው ዘመን ከደጃልና ዒሳ መምጣት አስቀድሞ የሚነሳ ታላቅ ‹‹ኸሊፋ›› ነው። ‹‹መህዲ›› የማዕረግ ስሙ ሲሆን ‹‹ሁዳ›› ከሚለው ቃል የተገኘና ‹‹የተመራ ቅን ኸሊፋ›› ማለት ነው። መጠሪያ ሙሉ ስሙ ደግሞ ‹‹ሙሐመድ ኢብን አብዱላህ አል-መህዲ›› ነው።

ስለ መህዲ በቁርኣን የተነገረ ምንም ነገር አናገኝም። መረጃዎቹ በሙሉ ከሐዲስ የተገኙ ሲሆን ከሃያ በላይ የተረጋገጡ ዘገባዎች ይገኛሉ። ብዙ የሱንና ዑለማዎች ስለ መህዲ የፃፉ ሲሆን ቲርሚዚና አቡ-ዳውድ ራሱን የቻለ ምዕራፍ ሰጥተውታል።

ከሁሉም ታዋቂው ሐዲስ አቡ-ዳውድ የዘገቡት ሲሆን ነቢዩ (ዐሰወ) እንዲህ ብለዋል፡-

‹‹ትንሳኤ ሊቆም አንድ ቀን ቢቀረው እንኳን አላህ ከቤተሰቤ የሆነን፤ ስሙ ከእኔና ከአባቴ ጋር የሚመሳሰል መሪን ሳያስነሳና በበደል የተዋጠችውን ምድር በፍትህ ሳይሞላት አይተዋትም።››

(አቡ-ዳውድ 4282)

ከዚህ ሐዲስ እንደምንረዳው መህዲ የነቢዩ (ዐሰወ) ቤተሰብ ነው። ስሙም የነቢዩን (ዐሰወ) እና አባታቸውን የያዘ ሲሆን ‹‹ሙሐመድ ኢብን አብዱላህ›› ወይም ‹‹አህመድ ኢብን አብዱላህ›› ነው። የሚመጣውም ዓለም በዙልም በተዋጠችበት በመጨረሻው ዘመን ሲሆን የአላህን ቃል ከፍ በማድረግ ፍትህን ያነግሳል።

ኡሙ ሰላማ (ረዐ) እንደተናገረችው ነቢዩ (ዐሰወ) ‹‹መህዲ በፋጡማ በኩል የሚገኝ ቤተሰቤ ነው።›› ብለዋል። ኢብኑል ቀይም ይሄንን ሐዲስ ሲያብራሩ ‹‹መህዲ የሐሰን ዘር ሲሆን አል-ሐሰን ለሙስሊሙ አንድነት ሲሉ ኸሊፋነታቸውን አሳልፈው በመስጠታቸው ምክንያት አላህም በመጨረሻው ዘመን ከቤተሰባቸው ታላቅ ኸሊፋ በማስነሳት ክሷቸዋል።›› ሲሉ ፅፈዋል።

(አቡ-ዳወድ 11/373)

አቡ-ሰዓድ አልኩድሪ በዘገቡት ሐዲስ ነቢዩ (ዐሰወ) ስለ መህዲ ገፅታ ሲናገሩ ‹‹ቁመቱ ረጂም፣ ትከሻው ሰፊ፣ አፍንጫው አጠፍ ያለ ነው።›› ብለዋል።

(አቡ-ዳውድ 4265)

መህዲ የሚነሳበትን ቦታ በተመለከተ የተለያዩ ዘገባዎች አሉ። ከፊሎቹ ከሻም ከፊሉ ከኹራሳን ሌላው ደግሞ ከመዲና እንደሆነ ይናገራሉ። ኢብን ከሲር የሁሉንም ሐዲሶች ጥቅል ሀሳብ ሲያስቀምጡ ‹‹የሚነሳው ከምስራቅ ነው። ከዚያም ወደ መካ ይሄዳል። ሰዎችም በከዓባ ዙሪያ ቃልኪዳን ይገቡለታል።›› ብለዋል። እንዲሁም በሌላ መጽሐፋቸው ‹‹በሐዲስ በተጠቀሰው መሰረት ባንዲራው ጥቁር ነው።›› በማለት አብራርተዋል።

(አልቢዳያህ ወልኒያህ 19/63፤ አልፊታን ወልመላሂም 1/49)

ኢማም አህመድ እንደዘገቡት መህዲ መሪነት ሲመረጥ ፍላጎቱም ክህሎቱም አልነበረውም። እናም ‹‹አላህ በአንድ ሌሊት ይመራዋል።›› ብለዋል (ዐሰወ)። ኢብን ከሲር ሐዲሱን ሲያብራሩ፡- ‹‹ይህ ማለት አላህ ይረዳዋል፣ ከዚህ በፊት ያልነበረውን ችሎታም ይሰጠዋል ማለት ነው።›› ብለዋል።

(አህመድ 2/58/ አልፊታን ወልመላሂም 1/29)

መህዲ ኸሊፋነትን ከተረከበ በኋላ ሙስሊም አገራትን በአንድ በማፅናት በቀደመው ኢስላማዊ አስተዳደር ስር ያስገባቸዋል። ከዚያም በቡኻሪ እና ሙስሊም (2897) እንደተዘገበው ከሮማውያን ጋር የመጨረሻው ታላቁ ጦርነት ‹‹አል-መልሃማ አል-ኩብራ›› ይካሄዳል። ሙስሊሞችም ዳቢቅ ላይ ድል ደርጋሉ። ከዚህ በፊት ያልተከፈቱ አገራትንም ይከፍታሉ። ከዚያ በኋላ ሙስሊሞች በየትኛውም ኃይል አይሸነፉም። አላህ አማኞችን ከፍተኛ የሀብት መትረፍረፍ ይባርካቸዋል።

ሸይህ ዑመር ሱለይማን አል-አሽቀር ሐዲሱን መሰረት በማድረግ እንደተናገሩት ‹‹ይህ ጦርነት ከባድ ውድመትን ስለሚያስከትል ዓለም አሁን ካለችው ስልጣኔ ወደኋላ በመመለስ እንደ ጥንቱ በጦር በጋሻ በፈረስ መጠቀም ይጀምራሉ።›› ብለዋል።

(አል-ቂያማህ አስ-

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Хьо дакъа дацанаш махь йоьтта.

«ሃማስ በእስራኤል ላይ ያደረሰው ጥቃት ያለምክንያት አይደለም❗❗ ፍልስጤማውያን ለ56 አመታት የታፈነ ወረራራ ገጥሟቸው ነው!!»

የተባበሩት መንግስታት ዋና ፀሐፊ:አንቶኒዮ ጉቴሬዝ:

"ሃማስ በእስራኤል ላይ ያደረሰው ጥቃት ያለምክንያት አይደለም ፍልስጤማውያን ለ56 አመታት የታፈነ ወረራራ ገጥሟቸው ነው።" ሲሉ ገልፀውታል። የእስራኤል መንግስት በበኩሉ ፈጥኖ ባወጣው መግለጫ ጉተሬዝ ስልጣናቸውን በአስቸኳይ ይልቀቁ ፀብ-አጫሪ ንግግር ነው የተናገሩት ሲል ከሷል።

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Хьо дакъа дацанаш махь йоьтта.

''ኔታናሁ ቁጥር አንድ አሸባሪ ነው ። ዓለም ይህን አሸባሪ መታገል አለበት '' ጁሊየስ ማሌማ

የደቡብ አፍሪካ ተቃዋሚ ፓርቲ መሪ ጁሊየስ ማሌማ በትላትናው እለት ፓርቲያቸው በኤስራኤል ኢምባሲ በጠራውው ሰልፍ ላይ ጠንከር ያለ መልእክት አስተላልፈዋል

''እኛ ገልለተኛ አይደለንም እኛ ከፍልስጤም ጎን የምንቆም ነን ። የፍልስጤም ህጻናት ግፍ እየተፈጸመባቸው ነው ። ማንዴላ ለነጻነት እንደታገለው ሃማስም ለነጻነት ነው እየታገለ ያለው ። ጠላትህ ሲገድልህ ትከላከላለህንጅ አትስመውም ።

የኤስራኤል ኢምባሲ በደቡብ አፍሪካ እንዲዘጋ እንፈልጋለን ። ከገዳዮች ጋር የምንጋራው ነገር የለም ። የኤስራኤል ምርቶችም ከሱቆች መወገድ አለባቸው

ኔታናሁ ቁጥር አንድ አሸባሪ ነው ። ዓለም ይህን አሸባሪ መታገል አለበት '' ሲሉ ተናግረዋል ።

image
image
Send as a message
Share on my page
Share in the group