Girma Redwan Profile Picture
UMMA TOKEN INVESTOR

Girma Redwan shared a
Табасаранан алхьа кха дац.

እደለኛ ሰው ማለት.....!👌

በሌሊቱ ወቅት የሱረቱል በቀራን የመጨረሻ ሁለት አንቀጾች ያነበበ ሰው በአላህ ፍቃድ ሌሊቱን ከመጥፎ ነገር ሁሉ እንደሚጠበቅ ተረድቶ ሲያበቃ አንቀፆቹን አዘወትሮ ያነበባቸው ሰው ነው።

እደለኛ ሰው ማለት.....!👌

ፈርድ የሆኑ ስላቶችን ከሰገደ በኋላ አያተል ኩርሲይን ካነበበ ጀነትን መግባት ሞት እንጂ ምንም እንደ ማይከለክለው ተረድቶ አዘወትሮ አያተል ኩርሲይን ያነበበ ሰው ነው።

እደለኛ ሰው ማለት.....!👌

ከመተኛቱ በፊት አያተል ኩርሲይን ያነበበ ሰው ለሊቱን ሙሉ እስኪያነጋ ከአላህ የተመደበ ጠባቂ እንደሚጠብቀውና ሸይጣንም እንደማይቀርበው አውቆ ከመተኛቱ በፊት አያተል ኩርሲይን አዘወትሮ ያነበበ ሰው ነው።

እደለኛ ሰው ማለት.....!👌

ሱረቱል ኢኽላስን ሶስት ጊዜ ማንበብ ሙሉ ቁርዓንን ከማኽተም ጋር እንደሚስተካከል ተረድቶ ይህችን ሱራ አብዝቶ ያነበበ ሰው ነው።

እደለኛ ሰው ማለት.....!👌

ለሴትና ለወንድ አማኞች ሁሉ ዱዓዕ ያደረገ ሰው በአያንዳንዱ አማኝ አላህ ዘንድ አጅር እንደሚመዘገብለት ተረድቶ ለሙዕሚኖች ሁሉ አብዝቶ ዱዓዕ ያደረገ ሰው ነው።

እደለኛ ሰው ማለት.....!👌

ሱብሃነሏህ

ወል ሀምዱ ሊላህ

ወላ ኢላሃ ኢለሏህ

ወሏሁ አክበር

ማለት ፀሀይ ከወጣችበት ሁሉ የተሻለና የበለጠ መሆኑን ተረድቶ እነዚህን ውድ ቃላት አብዝቶና ደጋግሞ ያላቸው ሰው ነው።

እደለኛ ሰው ማለት.....!👌

ይህንን ካወቀ በኋላ የሰራበትና ሌሌሎችም እንዲያውቁና እንዲተገብሩ በማሰታወስና በማካፈል የአጅሩ ተካፋይ የሆነ ሰው ነው።

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Girma Redwan shared a
Табасаранан алхьа кха дац.

በጨለማ ተጓዦችን… አበስራቸው‼

========================

✍ ምናልባትም ቀን ላይ ላብ ጠብ በሚያደርግ የጉልበት ሥራ ላይ አሳልፈህ ይሆናል፣ ናላን በሚያዞር የጭንቅላት ሥራ ተወጥረህ ይሆናል፣ በጠዋት የወጣህ ወደ ቤትህ የምትገባው አምሽተህ ይሆናል፣ ርቦህ ደክሞህ መጥተህ ትንሽ አረፍ እንዳልክ የፈጅር ሶላት ይደርስና በዙሪያህ ባሉ መስጂዶች «ሶላት ከእንቅልፍ በላጭ ነው፣ ኑ ወደ ሶላት፣ ኑ ፈላሕ ወደምትወጡበት መንገድ…» የሚል የጌታህን ጥሪ በአላህ ባሮች አንደበት ትሰማለህ።

ያኔ ነፍስህ በእንቅልፍ ሰመመን ውስጥ ሆና ከላይህ ላይ ያለውን ብርድልብስ አሽቀንጥረህ፣ ያንን ጣፋጭ እንቅልፍ ትተህ ለጌታህ ትዕዛዝ ምላሽ ለመስጠት ትነሳለህ ወይንስ «ቆይ ትንሽ እንቅልፌ ይውጣልኝና እነሳለሁ!» በሚል ሽንገላ ባልሰማ ጸጥ ብለህ ጸሐይ ሲወጣ መስገድ?  መቼም ከናካቴው አለመስገድ ይኖራል ብዬ አላስብም። አላህ ይጠብቀንና!

ፈጅር ላይ ከዚያ ደክሞህ ካገኘኸው ጣፋጭ እንቅልፍ ለመነሳት እነዚህ 3 ሐዲሦች በቂ ናቸውና ላስታውስህ ወደድኩ።

①ኛ) ለአንተ ገና ሳያዩህ በትካዜ የናፈቁህና  ሁሌም የሚቆረቆሩልህ አዛኙ ነቢይ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦

(بشرِّ المشائينَ في الظلمِ إلى المساجدِ، بالنورِ التامِّ يومَ القيامةِ)

«በጨለማ ወደ መስጂድ ተጓዦችን የውመ-ል-ቂያማህ በሙሉ ኑር (ብርሃን) አበስራቸው።»

[ጃሚዑ-ስ'ሶጚር: 2129፣ ሶሒሕ አቡ ዳውድ: 561]

√ ያኔ የውመል ቂያማህ ሁሉም ሰው በጭንቅ ውስጥ ሆኖ፣ ታላላቅ ነቢያትና የአላህ መልዕክተኞች ﷺ ሳይቀሩ «ነፍሴ ነፍሴ» በሚሉበት ቀን፣ ከፊሉ ሰው በጸሐይዋ ንዳድ ላቡ እስከ አፍንጫው ድረስ ሲያሰምጠው፣ ወደየት ልሽሽ፥ ወደየት ልግባ በሚልበት የጭንቅ ቀን… «ሙሉ በሆነ ኑር» ከመበሰር የበለጠ ምን መታደል አለና ነው ፈጅር ሶላት ላይ የምትዘናጋው?

ይሄን ብስራት የነገረህ እኮ ተራ ሰው ሳይሆን የሁሉም ፈጣሪና ባለቤት የሆነው አላህ የላካቸው ውድ ነቢይ ﷺ ናቸው። በል ተነስ!

*

②) ነቢይህ ﷺ እንዲህም ብለዋል፦

(مَن صَلَّى الصُّبحَ فَهُوَ فِي ذِمَّةِ اللَّهِ…)

«ሱብሒን (የፈጅር ሶላትን) የሰገደ ሰው በአላህ ጥበቃ ስር ነው።»

[ሙስሊም: 657]

√ እና እንደ ሙስሊም በአላህ ጥበቃ ስር ከመዋል የበለጠ ምን መታደል አለና ነው የምንዘናጋው? አላህ በጥላው ስር ካዋለህ አንተን የሚዳፈር ሁሉ ጥላውን እንደተዳፈረ ነውና የሚከላከልልህ አላህ ነው። ምክንያቱም ራስህን ለርሱ ሰጥተሃልና! ያ ሊጎዳህ ያለ ሁሉ ከአላህ በታች የሆነ አንድ ተራ ፍጡር ነውና በጥበቡ አደብ ያሲዘዋል።

√ አዕመሽ እንዳስተላለፈው በአንድ ወቅት ሳሊም (የዐብደ-ል'ሏህ ኢብኑ ዑመር ልጅ) ከሐጃጅ አጠገብ ቆሞ ነበርና (ያው ሐጃጅ ኢብኑ ዩሱፍ እንደምታውቁት…) አንዱ በአጠገቡ ሲያልፍ አየና ሐጃጅ ለሳሊም "የዚህን ሰው አንገት በሰይፍ ቅላው!" ብሎ አዘዘው። ሳሊምም የታዘዘውን ለመፈጸም ሰይፉን እንዳነሳ… ለሰውየው «ፈጅርን ሰግደሃል?» አለው። አንገቱ ሊቀ'ላ የነበረው ሰውየም «አዎ» ሲል መለሰ። ሳሊምም «በል! እንዳሻህ ጉዞህን ቀጥል!» አለውና ወደ ሐጃጅ ተመልሶ ይዞት የነበረውን ሰይፍ ጣለው። ሐጃጅም ለሳሊም «አንገቱን ቀላኸው?» ብሎ ጠየቀው። ሳሊምም «በጭራሽ» አለው። ሐጃጅም «ለምን?» አለው። ሳሊምም «እኔ አባቴ (ዐብደ-ል'ሏህን ማለቱ ነው) ነቢዩ ﷺ "የጠዋትን (የፈጅርን ሶላት) የሰገደ ሰው እስከ ምሽት ድረስ በአላህ ጥበቃ ስር ነው!" ብለዋል ሲል ሰምቸዋለሁ።» ብሎ መለሰለት። «በአላህ ጥበቃ ስር ያለን ሰው አልዳፈርም!» ማለቱ ነው።

√ ታላቁ የዘመናችን ዐሊም ኢብኑ ዑሠይሚንም ይሄን ሐዲሥ አስመልክተው በሪያዽ ሸርሓቸው ላይ ትንታኔያቸውን ሲያሰፍሩ እንዲህ ብለዋል፦

" في هذا دليل على أنه يجب احترام المسلمين الذي صدَّقوا إسلامهم بصلاة الفجر ؛ لأن صلاة الفجر لا يصليها إلا مؤمن ، وأنه لا يجوز لأحد أن يعتدي عليهم)

«ይህ እነዚያን በፈጅር ሶላት እስልምናቸውን ያረጋገጡ ሙስሊሞችን ማክበር እንደሚገባ ማሳያ ነው። ምክንያቱም የፈጅር ሶላትን ሙእሚን እንጂ አይሰግዳትም። ስለሆነም ማንኛውም ሰው ድንበር ሊያልፍባቸው አይገባም።»

[ሸርሕ ሪያዹ-ስ'ሷሊሒን: 1/591]

ምንም እንኳ እስልምናችን በማንም ንጹሐን ላይ ድንበር ማለፍን ቢከለክልም፤ ጭራሽ በእንዲህ አይነት ባሮቹ ላይ ድንበር ማለፍን ደግሞ የክልከላ ጥግን ከልክሏል።

*

③ኛ) ሐቢቢ! የፈጅርን ሶላት ፈርዱን መስጂድ ሂዶ መስገድ፤ አይደለም ፈርዱን መስገድ ሱን'ናውን መስገድ ብቻውን ያለውን ደረጃ አልሰማህም? ወይንስ ሰምተህ መተግበር ተሳነህ?

ውዱ ነቢያችን ﷺ ምን እንዳሉ ልንገርህ፦

ሐዲሡን ያስተላለፈችው ራሷ ባለቤታቸው እናታችን ዓኢሻህ (እውተኛዋ የእውነተኛ ልጅ) ናት - አላህ መልካም ሥራዋን ይውደድላትና። ውዱ ነቢይ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦

(ركعتَا الفجرِ خيرٌ من الدُّنيا وما فيها))،

«የፈጅር 2 ረከዓዎች (ሱንናዎቹ)፤ ከዱንያና በውስጧ ካለው ይበልጣሉ።»

[ሙስሊም: 725]

وقال أيضًا እንዲህም ብለዋል ﷺ፦

 ((لهُما أحبُّ إليَّ من الدُّنيا جميعًا)

«እነርሱ ለኔ ከዱንያ ሁሉ የተወደዱ ናቸው።»

አስበው! ዱንያ ላይ ስንት ገንዘብና ስንት ስልጣን አለ?

በየሃገራቱ ያሉ ውብና ሃብታም መንደሮችን፣ ዘመናዊ መኪኖችንና መኖሪያ ቤቶችን፣ የቅንጦት መዝናኛዎችን… ስንቱን ልዘርዝርልህ። ስታየው የሚያስቀና ስንትና ስንት ነገር አለ። «እኛም ከነዚህ ጋር እኩል እዚህች ዓለም ላይ እየኖርን ነው?» የሚያስብሉ ስንትና ስንት ቅንጡ ኑሮዎች አሉ?

ግን ምን ዋጋ አለው? የፈጅርን እንኳን ፈርዱን ሱ-ን'ናውን መስገድህ ብቻ ከዚህ ሁሉ ይበልጣል። የሱን'ናው ትሩፋት እንዲህ ከሆነ ፈርዱ ምን ቢሆን ነው በአላህ!

ኧረ! ያ አኺ! ተነስ እንነሳና ፈጅርን እንስገድ! ደግሞ ለዚህች ለማትሞላና ብትሞላ እንኳ ነገ ጥለናት ለምንሄዳት ዱንያ ብለን ይሄን ሁሉ ትሩፋት እናስመልጥ እንደ?  ትንሽ ደቂቃ እኮ ናት ሐቢቢ! 24 ደቂቃ እንኳ ላትሞላ ትችላለች! ታዲያ እንደት ከ24 ሰዓቱ ውስጥ 24 ደቂቃ ለጌታህ ትዕዛዝ ምላሽ ለመስጠት አጣህ? የተፈጠርከው እርሱን ለመገዛት ሆኖ ሳለ ሙሉ ጊዜህን መስጠት ባትችል እንኳ 24 ደቂቃ መስጠት ተሳነህ? አስበው!

24 ደቂቃ በስንት እንደምታልፍ! ከጓደኛህ ጋ ሻይ ቡና እንበል ብለህ ስንት ሰዓታት ነው የምታሳልፈው? ማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ስንት ሰዓት ነው የምታሳልፈው? ኳስ… ገለመሌ እያልክ ምን ያክል ሰዓት ነው የምታሳልፈው? ታዲያ የባለዚሁ ሰው እንደት ይህቺን ታክል ደቂቃ ለሶላት መስጠት ከበደህ? ኧረ! ተው ሐቢቢ ተው! ብልጥ ሁን!

የላ! ፈጅር አዛን ሲል ወደ መስጂድ! የምን እየሰሙ መሟዘዝ! የምን አላርም አለመቅጠር ወይም የቀጠሩትን ማጥፋት!

አላህ ያግራልን! ውዶች አንዘናጋ! የፈጅርና የዒሻእ ሶላት ለሙናፊቆች ለማስመሰል እንኳ የማይመቹ የአማኝነት ማረጋገጫ ናቸውና እንበርታ። 

*

ለሌሎችም የፈጅር መስገድ መነሳሳት ሰበብ ከሆንን (ለአንድም ሰው ቢሆን) መልዕክቱን እናድርሳቸው።

ሙራድ ታደሰ

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Girma Redwan shared a
Табасаранан алхьа кха дац.

"የፍልስጤም ጀግኖች! የጋዛ ሙጃሂዶች ሆይ! የአለም ሙዚየሞች የተዋጋችሁበትን ጫማ አንድ ቀን ይፈልጉታልና በጥንቃቄ አስቀምጡት አደራ"

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Girma Redwan shared a
Табасаранан алхьа кха дац.

በሰሜን ጋዛ ሰርጥ በአት-ቱዋምና በበይት ሐኑን አካባቢዎችን የቀሳም ሙጃሂዶች የወራሪዋን ተሸከርካሪዎች ሲያወድሙ የሚያሳይ ተንቀሳቃሽ ምስል ይፋ አድርገዋል። አይታችሁ ተገረሙ እናንተን ያስገረመው ጀግንነታቸው ሌሎችንም ያስገርም ዘንድ ሼር አድርጉ።

መረጃው ለሌሎችም እንድደርስ ሸር ያድርጉት🙏

📢ሌሎች ፈጣን እና የተለያዩ መረጃዎች እንድደርስዎ ቻናላችንን ይቀላቀሉ

👇👇👇

ቴሌግራም: ► https://t.me/Nejashimedia888

1 view
1 view
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Girma Redwan shared a
Табасаранан алхьа кха дац.

#በድል_ምእራፍ_ላይ_የሚገኘው_ሀማስ !

ጦርነቱ ተፋፍሞ እንደቀጠለ ቢሆንም ከእስራኤል በኩል መተንፈስ ይታያል ። ያበጠው ትእቢቷ እየሞሸሸ ይመስላል ። በቀናት አሳካዋለሁ ያለቺው በወራት ቢረዝምባትም እያሳካቺው ያለው ግን ድልን ሳይሆን ውርደትን ሽንፈትን ነው ።

ከአንድ ወር በላይ በተሻገረው የሀማስና የእስራኤል ትንቅንቅ እስካሁን ሀማስ ከ 136 በላይ ታንክና ወታደራዊ ተሽከርካሪዎቿን እምሽክ አድርጎላታል ። ከ 500 በላይ ወታደሮቿንም ወደዚያ ወደሚጠብቃቸው አለም አሰናብቷቸዋል ። ሌሎች በመቶዎች የሚቆጠሩ የእስራኤል ወታደሮች ደግሞ ቁስለኛ ሆነው የእስራኤል ሆስፒታሎችን አጠናንቀዋል ። የእስራኤል ወታደሮች አስክሬን በሰአታት ልዩነት ውስጥ እየገማ ለገናዥ ለቀባሪም አስቸግሯል ። ሄሊኮፕተሮች አስክሬን እና ቁስለኛ በማመላለስ ተጠምደዋል ።

ይህ ሁሉ ከባድ ምት ይህ ሁሉ ድቆሳ የደረሰባት አንድም የአየር ሀይል አንድ ሜካናይዝድ ሀይል አንድም የተራቀቀ የሚሳኤልና የሮኬት ሀይል በሌለው ጀግንነት ኢማንን ፅናትን ስንቅና ትጥቁ ባደሰረገው ሀማስ ነው ። እስራኤል ከተመሰረተች ጀምሮ እንደዚህ አይነት ውርደትም ሽንፈትም ውድመትም ደርሶባት አይታወቅም !

ልብ በሉ !

እስራኤል ከመካከለኛው ምስራቅ ተወዳዳሪ የሌላት የጦር ሀይል እንድትሆን ከ 600 በላይ የጦር ጄቶችን ከአሜሪካና አጋሮቿ የታጠቀች ፤ ሮኬት ተወንጭፎ እንዳይመታት Iron dome ን የመሳሰለ ቴክኖሎጂ ከአሜሪካ የተሰጣት ፤ የኑክሌር ቦንብን እንድትታጠቅ በምእራባውያን የተደገፈች ፤ ይህ ሁሉ አልበቃ ብሎ በየአመቱ ረብጣ ቢሊዮን ዶላሮች ለጦሯ ማጠናከሪያ ወደ ካዝናዋ የሚንቆረቆርላት ሀገር ነች ። ይሄም ሁሉ አልበቃ ብሎ አሜሪካ የጦር ሀይሏን ጭምር ወደ መካከለኛው ምስራቅ ልካ " ምናልባትም ኢራን ብትመታትስ " በሚል የምትጠብቃት ሀገር ናት ። ታዲያ እስራኤል በዚህ ሁሉ መሀል ከ 400,000 በላይ ጠንካራ ሰራዊትን ገንብታለች ።

ግና ይሄ ሁሉ ነገር ሀማስን እንድታሸንፍ አለማስቻሉ ነው እንቆቅልሹ ። እናንተየ እንደት ከአለም ሁሉ ተነጥሎ አንድት ትንሽየ ግዛት ውስጥ የራሱን ርኬቶች በራሱ እጅ እየሰራ የሚታገል ድርጅት ይህን ሁሉ የሆነች ሀገርን ማርበድበድ ተቻለው ? ግሩም ድንቅ ነው ! የነርሱስ ይለያል !!

አሁን እስራኤል ወደ ጋዛ ከተማ ለመግባት የምታደርገው መንገድ የጀሀነም መንገድ ሆኖባታል ። የእስራኤሉ መከላከያ ሚኒስትር ቃል አቀባይ ቃል በቃል የተናገረውን ልንገራችሁ " ከጋኔሎች (ጅኖች ) ጋር ነው እየተዋጋን ያለነው " አለ ። ለምን ተብሎ ሲጠየቅ " ከጋኔል ጋር ስትዋጋ ከየት መጥቶ ፊትህን እንደሚደረግመው አታውቀውም በጎዳናው እየሄድክ ድንገት ሊያነድብህ ይችላል እንድህ አይነት ጦርነት ነው እያደረግን ያለነው " አለ ። ወዳጅ ቢመስክር ምን ይደንቃል ? እንደዚህ ጠላት ሲመሰክር ግን አቤት ልእልና !! አቤት ጀብደኝነት !!

ቤኒያሚን ኔታኒያሁ ደግሞ እንደዚህ ሲል ሀማስን ወቀሰ " ሀማሶች በደፈጣ አጥቅተው እየሸሹ እየተዋጉ ነው ያሉት " አለ ። እና ለአየር ሀይሉ እዚህ ነን እያሉ መጣራት ነበረባቸው 🤔

አንድ ነገር ግን ልንገራችሁ !

አሁን ሀማስ ሀይሉን ቆጥቦ ነው እየተዋጋ ያለው ። ወታደራዊ እንቅቃሴዎቿን ወታደርና ተሽከርካሪዎቿን እያጠመደ መደምሰስ ላይ ብቻ ነው የተወሰነው ። ምክንያቱም ጦርነቱ እስከሚን ሊቀጥል እንደሚችል ሶለማይታወቅ እስራኤልንም በረጅም ጊዜ ፍልሚያ የማዳከም አላማ ስላለው አሪፍ አድርጎ እየገባላት ነው ።

እና አሁን እስራኤል ነገሮች እንዳሰበቺው እየሄዱላት አይደለም ። ለዚያም ዛሬ በየቀኑ የተወሰነ ሰአታት ተኩስ አቁም አሳውቃለች ።

Send as a message
Share on my page
Share in the group