UMMA TOKEN INVESTOR

Ман пирки

كن محب الخير الغير

7 уйӑх Куҫарас
Çĕнĕ çулахне йывăçлăх

🟥 ድግምት ( ሲህር) የሚከሰትበት ትክክለኛ ምንነት እና ህክምናው🟥

ታላቁ ሼይኽ ኢብኑ ባዝ አላህ ይዘንላቸው እና እንዲህ አሉ:—ሲህር ድግምት እውነት ለመሆኑ ጥርጥር የለውም በአላህም ፍቃድ ተፅኖ ያደርሳል አላህም ስለ ድግምተኞች እንዲህ ብሏል

 ﴿وَمَا يُعَلِّمَانِ مِنْ أَحَدٍ﴾ [البقرة:١٠٢].

يعني: الملكين: ﴿حَتَّى يَقُولا إِنَّمَا نَحْنُ فِتْنَةٌ فَلا تَكْفُرْ فَيَتَعَلَّمُونَ مِنْهُمَا مَا يُفَرِّقُونَ بِهِ بَيْنَ الْمَرْءِ وَزَوْجِهِ وَمَا هُمْ بِضَارِّينَ بِهِ مِنْ أَحَدٍ إِلَّا بِإِذْنِ اللَّهِ﴾. [البقرة:١٠٢]

ያንንም በባቢል በሁለቱ መላእክት በሃሩትና ማሩት ላይ የተወረደውን ነገር (ያስተምሩዋቸዋል)፡፡ «እኛ መፈተኛ ነንና አትካድ» እስከሚሉም ድረስ አንድንም አያስተምሩም፡፡ ከእነሱም በሰውየውና በሚስቱ መካከል በርሱ የሚለዩበትን ነገር ይማራሉ፡፡ እነርሱም በአላህ ፈቃድ ካልኾነ በርሱ አንድንም ጎጂዎች አይደሉም፡፡

♦️ ( ሲህር) ተፅኖ አለው ነገር ግን በአላህ ይሁንታዊ ፍቃድ ነው ይሁን እንጂ ይህ ሲህር ህክምና እንዲሁም መድሃኒት አለው። በእርግጥም በነብዮ، ﷺ ላይ ተከስቷል ቢሆንም አላህ አጥርቷቸዋል። ከሲህርም ሸር አውጥቷቸዋል። ድግምተኛ የሰራውን አግኝተው አበላሽተውታል። ስለሆነም ድግምተኞች የቋጠሩት ቋጠሮ ትብተባ ወዘተ ቢገኝ ማበላሸቱ ተገቢ ነው።

❐ ድግምተኞች ለሚያስቡት እኩይ እሳቤ በባህሪያቸው በገመድ ላይ ቱፍታን ያደርጋሉ በገመዱም ላይ ይመታሉ በእርግጥም ያሰቡት ነገር በአላህ ፍቃድ ይሳካላቸዋል። ቢሆንም ግን ይህ ድግምት ይወገዳል ጌታችን በሁሉ ነገር ቻይ ነውና።

አንድ አንዴ ድግምት በቁርኣን ይታከማል ታማሚው አእምሮው ጤነኛ ከሆነ እራሱ መቅራት ይችላል ካልሆነም ሌላ ሰው ቢቀራበትም ይሆናል በሚቀራበት ጊዜ በደረቱ ላይ ወይም ከአካሉ በአንደኛው ቦታ ቱፍታ ቢያደርግለት ችግር የለውም በታማሚው ላይ ሱረቱል ፋቲሃ አየተልኩርሲ ቁልሁወላሁ አሃድን ሙዓወዘተይን እንዲሁም አየተሲህር ይቅራበት።

አየተሲህር የሚከተሉት ናቸው

﴿وَأَوْحَيْنَا إِلَى مُوسَى أَنْ أَلْقِ عَصَاكَ فَإِذَا هِيَ تَلْقَفُ مَا يَأْفِكُونَ (١١٧) فَوَقَعَ الْحَقُّ وَبَطَلَ مَا كَانُوا يَعْمَلُونَ (١١٨) فَغُلِبُوا هُنَالِكَ وَانقَلَبُوا صَاغِرِينَ(١١٩)﴾. [الأعراف:١١٧-١١٩].

▪️ومن سورة يونس قوله سبحانه: ﴿وَقَالَ فِرْعَوْنُ ائْتُونِي بِكُلِّ سَاحِرٍ عَلِيمٍ (٧٩) فَلَمَّا جَاءَ السَّحَرَةُ قَالَ لَهُمْ مُوسَى أَلْقُوا مَا أَنْتُمْ مُلْقُونَ (٨٠) فَلَمَّا أَلْقَوْا قَالَ مُوسَى مَا جِئْتُمْ بِهِ السِّحْرُ إِنَّ اللَّهَ سَيُبْطِلُهُ إِنَّ اللَّهَ لا يُصْلِحُ عَمَلَ الْمُفْسِدِينَ (٨١) وَيُحِقُّ اللَّهُ الْحَقَّ بِكَلِمَاتِهِ وَلَوْ كَرِهَ الْمُجْرِمُونَ (٨٢)﴾.[يونس:٧٩-٨٢].

﴿قَالُوا يَا مُوسَى إِمَّا أَنْ تُلْقِيَ وَإِمَّا أَنْ نَكُونَ أَوَّلَ مَنْ أَلْقَى (٦٥) قَالَ بَلْ أَلْقُوا فَإِذَا حِبَالُهُمْ وَعِصِيُّهُمْ يُخَيَّلُ إِلَيْهِ مِنْ سِحْرِهِمْ أَنَّهَا تَسْعَى (٦٦) فَأَوْجَسَ فِي نَفْسِهِ خِيفَةً مُوسَى (٦٧) قُلْنَا لا تَخَفْ إِنَّكَ أَنْتَ الأَعْلَى (٦٨) وَأَلْقِ مَا فِي يَمِينِكَ تَلْقَفْ مَا صَنَعُوا إِنَّمَا صَنَعُوا كَيْدُ سَاحِرٍ وَلا يُفْلِحُ السَّاحِرُ حَيْثُ أَتَى(٦٩)﴾. [طه:٦٥-٦٩].

▪️እንዲሁም ሱረቱል ካፊሩንን ይቀራል .ቁልሁወላሁ አሃድን ሙዓወዘተይን ሦስት ሦስቴ ጊዜ ይቀራበታል።

ከዚያም አላህ አፍያ እንዲያደርገው ዱዓ ያደርግለታል ዱዓዎቹም የሚከተሉት ናቸው : –

(اللهم رب الناس أذهب البأس واشف أنت الشافي لا شفاء إلا شفاؤك شفاءً لا يغادر سقماً)، ሦስቴ ይደጋግመዋል

(رب الناس أذهب البأس واشف أنت الشافي لا شفاء إلا شفاؤك شفاءً لا يغادر سقماً)، يعني: مرضاً، وهكذا يرقيه بقوله: (باسم الله أرقيك، من كل شيء يؤذيك، ومن شر كل نفس أو عين حاسد الله يشفيك باسم الله أرق ويكررها ثلاثاً ويدعو له بالشفاء والعافية، وإن قال في رقيته: (أعيذك بكلمات الله التامات من شر ما خلق وكررها ثلاثاً فحسن)، كل هذا من الدواء المفيد، وإن قرأ هذه الآيات والدعاء في ماء ثم شرب منه المسحور واغتسل بباقيه وتروش به كان هذا أيضاً من أسباب الشفاء والعافية——————

አህሉል አስር አሩቅየቱ ሸርእያ

የቁርኣን ህክምና አገልግሎት መስጫ

አድራሻ አዲስ አበባ እና አካባቢዋ

@ahlulaserarukyeushereiya

@ahlulaserarukyeushereiya

ለበለጠ መረጃ ከታች ባሉት ስልክ ቁጥሮች ማናገር ትችላላችሁ

አቡ ሰሊም 09 13223722

አቡ ሑዘይፋ 09 33189431

በነዚህ አድራሻዎች ብትደውሉ በቂ መረጃ እና አገልግሎት ማግኘት ትችላላችሁ።

Хыпар пек ярас
Ман тетелӗ питра пайлас
Ушкӑнта пайлас
7 уйӑх Куҫарас
Çĕнĕ çулахне йывăçлăх

بسم الله الرحمن الرحيم الحمد لله وحده عالم الغيب والشهادة والصلاة والسلام علي من لانبي بعده

አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱህ አልሀምዱ ሊላሂ እስልምናን ከሌሎች ሀይማኖት አስበልጦ ለሰጠን ከዚያም በተውሂድ ላዘዘን እንዲሁም ከሽርክ ላስጠነቀُ۟ቀን። አላህ እንዲህ ይላል" ِ ۗ ٱلْيَوْمَ يَئِسَ ٱلَّذِينَ كَفَرُوا۟ مِن دِينِكُمْ فَلَا تَخْشَوْهُمْ وَٱخْشَوْنِ ۚ ٱلْيَوْمَ أَكْمَلْتُ لَكُمْ دِينَكُمْ وَأَتْمَمْتُ عَلَيْكُمْ نِعْمَتِى وَرَضِيتُ لَكُمُ ٱلْإِسْلَٰمَ دِينًۭاۚ ِمٌ ዛሬ እነዚያ የካዱት ከሃይማኖታችሁ ተስፋ ቆረጡ፡፡ ስለዚህ አትፍሩዋቸው፡፡ ፍሩኝም፡፡ ዛሬ ሃይማኖታችሁን ለናንተ ሞላሁላችሁ፡፡ ጸጋዬንም በናንተ ላይ ፈጸምኩ፡፡ ለእናንተም ኢስላምን ከሃይማኖት በኩል ወደድኩ። (ማኢዳ) وَمَن يَبْتَغِ غَيْرَ ٱلْإِسْلَٰمِ دِينًۭا فَلَن يُقْبَلَ مِنْهُ وَهُوَ فِى ٱلْـَٔاخِرَةِ مِنَ ٱلْخَٰسِرِينَ

ከኢስላም ሌላ ሃይማኖትን የሚፈልግ ሰው ፈጽሞ ከርሱ ተቀባይ የለውም፡፡ እርሱም በመጨረሻይቱ ዓለም ከከሳሪዎቹ ነው፡፡ ( አል ኢምራን) أَفَغَيْرَ دِينِ ٱللَّهِ يَبْغُونَ وَلَهُۥٓ أَسْلَمَ مَن فِى ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلْأَرْضِ طَوْعًۭا وَكَرْهًۭا وَإِلَيْهِ يُرْجَعُونَ

በሰማያትና በምድር ያሉ ሁሉ፤ በውድም በግድም ለርሱ የታዘዙ ወደርሱም የሚመለሱ ሲኾኑ (ከሓዲዎች) ከአላህ ሃይማኖት ሌላን ይፈልጋሉን አላህ የመረጠልን ሀይማኖት ኢስላም ተውሂድ ሆኖ ሳለ እኛ ግን "በተቃራኒው ኩፍር ወይም ሽርክ ላይ ተዘፍቀናል። ይህም ከዱንያ ሽንጋይ ነገሮች በአንዱ ተለክፈን ነው ከነዚህም መካከል የጠንቋይ ሽንገላ ይገኝበታል። ቀድሞውኑ ጠንቋይ ጋር መሄድ ሀራም ነው ነብያችን ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም እንዲህ ይላሉ"من أتي كاهنا فصدقه بما يقلو فقد كفر بما أنزل علي محمد صلي الله عليه وسلم"

"ጠንቋይን(የሩቅ ሚስጥር(ገይብ) አውቃለሁ የሚልን) የመጣ እንዲሁም ጠንቋዮ የነገረውን እውነት ብሎ የተቀበለ በርግጥ በሙሀመድ ላይ በተወረደው ክዷል"

በሌላሀዲሳቸው ደግሞ እንዲህ ይሉናል" من أتي عرافا فسأله عن شيء لم تقبل له صلاة أربعين يوما "አዋቂ ነኝ ብሎ የሚሞግትን(ሚስጥር ፣የጠፋነገር፣እንዲሁም ወደበፊት የሚከሰቱ ነገሮችን አውቃለሁ የሚል)ን የመጣ እንዲሁም ስላንዳች ነገር የጠየቀው(እውነት ብሎ ባይቀበልም) የአርባ ቀን ሰላቱ ተቀባይነት አይኖረውም"

{እንዴት ጠንቋዮች ሚስጥራችንን ሊያውቁ ይችላሉ???}

ከአላህ ሱብሀነሁ ወተአላ በቀር ገይብ( የሩቅ ሚስጥር) የሚያውቅ አለመኖሩ ጥርጥር የለውም እንደው ልባችን እንዲረጋጋ የተወሰኑ የቁርአን አንቀፆች እንመልከት አላህ እንዲህ ይላል" قُل لَّا يَعْلَمُ مَن فِى ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلْأَرْضِ ٱلْغَيْبَ إِلَّا ٱللَّهُ ۚ وَمَايَشْعُرُونَ أَيَّانَ يُبْعَثُونَ

«በሰማያትና በምድር ያለው ሁሉ ሩቅን ምስጢር አያውቅም፡፡ ግን አላህ (ያውቀዋል)፡፡ መቼ እንደሚቀሰቀሱም አያውቁም» በላቸው፡፡ ( አነምል) እንዲሁም በሌላ አንቀፅ እንዲህይለናል عَٰلِمُ ٱلْغَيْبِ فَلَا يُظْهِرُ عَلَىٰ غَيْبِهِۦٓ أَحَدًا

«(እርሱ) ሩቁን ምስጢር ዐዋቂ ነው፡፡ በምስጢሩም ላይ አንድንም አያሳውቅም።(አልጂን) መልካም ለአብነት ያህል እንዲህ ካልን መጀመርያ ገግይብ ምንድነው? ገይብን በሁለት መልኩ ማየት ይቻላል:

1ኛ ቋንቋዊ ፍቺው ገይብ ማለት ከሰዎች የራቀ ሁሉ ሲሆን ይህም ክስተቱ ሲከሰት በቦታው አለመገኘት ነገሩን በአንድ ወይም በሌላ መልኩ አለመስማትን ያካትታል።

2ኛ ሸሪዓዊ ፍቺው ነው ገይብ ማለት አላህ ሱብሀነሁ ወተአላ ለነብያቶች በወህይ አማካኝነት የገለፀላቸው ሲሆን ልክ እንደ ጀነት ጀሀነም አሉ ብሎ ማመን መላኢካዎች ጅኖች አሉ ብሎ ማመን ወዘተ ያካትታል። እንዲሁም ገይብ በቀልባችን የቋጠርነው፣ ሚስጥራችንንም ያካትታል።

ታድያ እንዴት ጠንቋዮች ሚስጥራችንን ያውቃሉ ? ነገሩ እንዲህ ነው ማንኛውም ሰው ከተፈጠረ ጀምሮ አብሮት ያለ ቁራኛ (ጅን) አለ። ለዚህም ከቁርአን ማስረጃ ስንመለከት አላህ እንዲህ ይላል" ۞ قَالَ قَرِينُهُۥ رَبَّنَا مَآ أَطْغَيْتُهُۥ وَلَٰكِن كَانَ فِى ضَلَٰلٍۭ بَعِيدٍۢ

ቁራኛው (ሰይጣን) «ጌታችን ሆይ! እኔ አላሳሳትኩትም፡፡ ግን (ራሱ) በሩቅ ስሕተት ውስጥ ነበር» ይላል፡፡( ቃፍ)

ይህ ቁራኛ አብሮን ሁሌም ስላለ እኛ የምናውቀውን ሁሉ ያውቃል በእያንዳንዱ እንቅስቃሴያችን አብሮን ስለሆነ ያለፈ ታሪካችን ይሁን አሁን ያለንበት ነባራዊ ሁኔታ ከሱ የተሰወረ አይደለም። ጠንቋዮች ደግሞ እንደሚታወቀው ከአላህ መንገድ በመውጣታቸው ምክንያት እንዲሁም ፀያፍና ሽርክያት የሆኑ ነገሮችን በመተገበራች ፣አኼራን ሽጠው ዱየንያን በመግዛታቸው የሚታዘዙዋቸው ጅኖች አሉዋቸው። በመሆኑም አንድ ግለሰብ ጠንቋይ ዘንድ በሚቀርብበት ጊዜ ይህ ከአላህ መንገድ ያፈነገጠው ጠንቋይ ታዛዥ ጅኑን የግለሰቡን ቁራኛ ን( ጅንን) ያለፈ ታሪኩን ወይም ስለ ራሱ እሱ ብቻ የሚያውቀን ሚስጥር እንዲጠይቅለት ያዘዋል የግለሰቡ ቁራኛ ከላይ እንዳሳለፍነው ሙሉ መረጃ ስላለው ለጠንቋዮ ታዛዥ ጅን መረጃ ይነግረዋغል ታዛዥ ጅኑ ደግሞ ለጠንቋዮ እንግዲህ እንዲህ ነው ሚስጥር ሊያውቁ የሚችሉት። በመሆኑም ጠንቋይ ጋር የቀረበው ግለ ሰብ ወደሱ ዘንድ ሲሄድ ያጋጠመውን ፣እኩይ ይሁን ሰናይ ሚስጥሩን ይነገረዋል 'በዚህ ጊዜ ይህ ግለ ሰብ ይደነግጥና ልቡን ይሰጠዋል በሱላይ እምነትም ይኖረዋል። ከዝያማ ከአላህ መንገድ አስወጥቶ ወደ ሽርክ ይመራዋል። ስለዚህ ይህ ጠንቋይ ገይብ አወቀ ማለት ነው? በጭራሽ ከተነገረው ማንም ያውቃል እነዚህ ጠንቋዮች

ህዝባችንን እንዲህ እያታለሉ ከአላህ መንገድ አስወጥተው ዱንያም አኼራውንም አበላሽተዋል። ስለዚህ ወንድም እህቶች ለማያውቁ ወንድምና እህቶች በማሳወቅ ከሽርክ እንዲድኑ ሰበብ እንሁን አበቃሁ ወንድማችሁ abu selim✍

አህሉል አስር አሩቅየቱ ሸርእያ

የቁርኣን ህክምና አገልግሎት መስጫ

አድራሻ አዲስ አበባ እና አካባቢዋ

@ahlulaserarukyeushereiya

@ahlulaserarukyeushereiya

ለበለጠ መረጃ ከታች ባሉት ስልክ ቁጥሮች ማናገር ትችላላችሁ

አቡ ሰሊም 09 13223722

አቡ ሑዘይፋ 09 33189431

በነዚህ አድራሻዎች ብትደውሉ በቂ መረጃ እና አገልግሎት ማግኘት ትችላላችሁ።

image
Хыпар пек ярас
Ман тетелӗ питра пайлас
Ушкӑнта пайлас
Amir sultan Хӑйӗн сӑнӳкерчӗкне улӑштарчӗ
7 уйӑх
Çĕнĕ çулахне йывăçлăх

image
Хыпар пек ярас
Ман тетелӗ питра пайлас
Ушкӑнта пайлас