UMMA TOKEN INVESTOR

Translation is not possible.

,

ደጋግ ቀደምቶችና ወላጆቻቸው

بسم الله الرحمن الرحيم

🔥 ታላቁ ሶሀቢይ አቡ ሁረይራ (رضي الله عنه) ዘወትር ከቤቱ ሊወጣ ሲል ደጃፍ ላይ ይቆምና "እናቴ ሆይ‼️ የአሏህ ሰላም ፣ እዘነትና በረከት ባንቺ ላይ ይስፈን" ይላታል። እርሷም ባማረ መልኩ አፀፋውን ስትመልስለት አስለጥቆ "እናቴ ሆይ‼️ በህፃንነቴ በርህራሄ እንዳሳደግሽኝ አሏህ ይራራልሽ" ብሎ ዱዓ ሲያደርግላት "በትልቅነቴ እንደተንከባከብከኝ አሏህ ይዘንልህ" ብላ ትመልስለታለች። ወደ መኖሪያቸው ሲመለስም ይህንን ያማረ ምልልስ ከእናቱ ጋር ያደርጋል። አሏሁ አክበር‼️ ምንኛ ያማረ ፍቅር🔥

👌 ከዐሊይ ኢብን ሁሰይን እንደተዘገበውም ከእናቱ ጋር በአንድ ገበታ መብላትን በእጅጉ ይፈራ ይጠነቀቅም ነበር። ለዚህም ምክንያቱ ምን እንደሆነ ሲጠየቅ የሚከተለውን ልብን ሰብሮ ዐይንን ሚያስነባ መልስ ነበር የመለሰው። ዐሊይ ይናገራል "እኔ ይህን ማድረግ ማልፈልገው ድንገት የእናቴ አይን ባረፈበት የገበታው ምግብ ላይ እጄ ቀድሞ አርፎ ሀቋን እንዳላጓድል ስለምፈራ ነው።" ላ ኢላሀ ኢለሏህ🔥 ምን አይነት ጥንቃቄ ⁉️ ምንስ አይነት የአሏህ ፍራቻ⁉️

🔥 እኚህ ደግሞ ታላቁ ዓሊም ሚስዐር ብን ሀቢብ አልጂርሚይ ናቸው!! ከእለታት በአንዱ ሌሊት እናታቸው በሌሊቱ እኩሌታ ተነስታ ውሀ ያጠጣት ዘንድ ጠየቀችው። ሚስዐርም ውሀውን ይዘው ሲመጡ እንቅልፍ እናታቸውን እንዳሸነፈና እንዳሸለቡ አስተዋለ። ከዚያም ውሀውን እንደያዘ መባነናቸውን ሲጠባበቅ የንጋት አብሳሪው ጎህ ፈነጠቀ። እናታቸውም ውሀውን ሳይጎነጩ እርሳቸውም ከቦታው ፈቀቅ ሳይሉ ሌሊቱ ነጋ‼️ አሏሁል ሙስተዓን‼️ ያ አሏሏሏሏሏሏሏህ!! ምን ነበር እኚህ ጀግኖች ሲሰሩ የነበረው⁉️

🔥 ይህ ደግሞ ዐውን ቢን ዐብደሏህ ነው! በዛ እዝነትና ርህራሄ በተሞላው አንደበቷ እናቱ ጠራችው። እርሱም በቅጽበት ነበር "ለበይኪ ያዑማህ " ብሎ የመለሰላት። ነገር ግን ድምፁ ከእናቱ ድምፅ በላይ ከፍ ማለቱን ዘግይቶ ነበር ያስተዋለው። በዚህም ተግባሩ እጅጉን ተፀፀተ!! ሀቋን የማጓደል ስሜትም ስለተሰማው የተግባሩ መካሻ ይሆን ዘንዳ ሁለት ባሮችን በአሏህ መንገድ ላይ ነጻ አደረገ‼️

ያ አሏህ!! ምን አይነት ትውልድ ይሁን ያለፈው⁉️ እስኪ እናስተንትን ውዶች🛎 ይህ ግለሰብ የነበረውንና እኛ ተላሎቹ ከወላጆቻችን ጋር ያለንን መስተጋብር 💔 ተውት ድምፅ ከፍ ማድረጉን እኛ ሙስሊሞቹ አይደለን እንዴ ወላጆቻችንን ማመናጨቅ መሳደብ የዘወትር መገለጫችን የሆነው⁉️ አለፍ ሲልም እስከ መደብደብና ግድያ ድረስ ያሉ ከተራራ የገዘፉ ሀጥያቶችን እየተገበርን ያለነው ⁉️ ያአሏህ አንተው ሁነን🤲

💔 ቀደምቶቻችንስ ቢሆኑ ከበስተኋላቸው በሚመጡት ላይ ጉዳዩን ምንኛ አከበዱት⁉️ እኛንስ አሁን ያለንበትን ሁኔታ ቢያዩ ምን ይሉ ይሆን⁉️ ... ነገር ግን አሏህ ሁሉንም አይቷል፤ ያያልም‼️

አሏህ የቀደምቶቻችንን ያህል ባይሆንኳ የወላጆቻችንን ሀቅ ለመጠበቅ የምንጥር ባሮች ያድርገን🤲🤲

رَبَّنَا ظَلَمۡنَآ أَنفُسَنَا وَإِن لَّمۡ تَغۡفِرۡ لَنَا وَتَرۡحَمۡنَا لَنَكُونَنَّ مِنَ ٱلۡخَٰسِرِينَ🤲🤲

✍ Abu remzan Asselefy

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

ዑሚ አሏህ ይጠብቅሽ

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

📵ከሰው ተሸሽጎ ሁሉን ቻዩን ማመጽ

بسم الله الرحمن الرحيم

"ከእለታት ባንዱ ቀን" ይላሉ ታላቁ የኢስላም ሊቅ ሸይኽ ዐብዱ-ረዛቅ አል-በድር የአሏህን እይታ ከሰዎች አሳንሰን በድብቅ ጌታችንን ለምናምጽ ደካማ ባሮች ምክራቸውን ሊለግሱ የአንድን ግለሰብ የታሪክ ክስተት ሲያስታውሱ። "አንድ ግለሰብ ብቻውን ሆኖ ያጋጠመውን ክስተት ይናገራል። ይህን ሰው ነብሱ በዘመናችን ወደ ተበራከተው ወንጀል ክልክል የሆኑ videosን ወደ መመልከት ጠራችው። ሰውዬውም ጥሪውን ተቀበለ። ክፍሉንም ዘጋግቶ ጎኑን አልጋው ላይ አሳረፈ። በዚያው ቅጽበት ነበር ማንም ሊያየው እንደማይችል በመገመት Mobile ከፍቶ ወደ social media የገባው(ያ በአግባቡ ካልተያዘ የከረፋው ስፍራ)።የአሏህን እይታ ችላ በማለትም በ Social media አጸያፊ ነገራትን መመልከቱን ተያያዘው። ከቆይታ በኋላም በር ላይ ድምጽ ሰማ!!!(ማን ይሆን!?) በከፍተኛ ድንጋጤ ውስጥ ሆኖም ሁሉንም ነገር አጠፋፋና ወደ በሩ አመራ። ዳሩ ግን በሩን ሲከፍት የተመለከተው ያ የፈራው የሰው ልጅ ሳይሆን ድመት ነበረች በሩ ስር የነበረችው። "

ኢናሊላሂ ወዒና ዒለይሂ ራጂዑን‼️‼️ ሁሉን ቻይ የሆነው ኻሊቅ እይታ ሳያስፈራው ከመኽሉቆቹ እይታ ተሰውሮ አሏህን ያምጻል‼️ አሏህን ትቶ ባሮቹን ያፍራል!!... እኛስ ወገኖቼ!? ከሰው ስንገለል ጉዟችን አሏህን ወደ ማመጽ ወይስ ወደ ዒባዳ ነው!? የእጅ ስልካችንስ ቢሆን ስንት ሙሀረማት ይሆን ከሰው ሸሽገን ያስቀመጥንበት!? እኛም ዐዚዙ ማየት ሚሳነው መስሎን ይሆን⁉️ ላ ወሏህ‼️ ታግሶን ቢሆን እንጂ እርሱ ሁሉንም ይታዘባል። ነገር ግን ሊቀጣን አይሻምና ወደርሱ እንድንመለስ ሌት ተቀን ይጠራናል። ሱብሀነከ ረበና👌

👌 እናም እስቲ ራሳችንን እንፈትሽ!! ይህ ጸያፍ ተግባር ላይ ወድቀን ከሆነም ያማረ መመለስን ወደ አሏህ እንመለስ!! እርሱ ረህማን ሁሉንም መሃሪ የሆነ ጌታ ነውና።

አሏህ የተውበቱን መንገድ ገር ያድርግልን🤲🤲

✍Abu remzan

for more 👇👇

https://ummalife.com/aburemzan

aburemzan | UmmaLife

aburemzan | UmmaLife

aburemzan: aburemzan. Nikname: @aburemzan | One Ummah — One Network - was created as a response to the Internet technology needs of Muslims and all adherents of traditional value
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group