Fedlu Mohammed Profile Picture
UMMA TOKEN INVESTOR

Fedlu Mohammed berbagi sebuah
Tidak bisa diterjemahkan.

ነብዩ ሰዐወ እንዲ ብለዋል:- «የተራበቡ ሰዎች በሰሃን ወደ ቀረበው ምግብ ሊበሉ አንደሚሰባሰቡት (እንደሚጠራሩት) ህዝቦች (ከሃዲዎች) በናንተም ላይ ይጠራሩባቹሃል!»

ከሶሃቦች መካከልም "የአላህ መልእክተኛ ሆይ እንዲህ የሚተባበሩብን ያን ግዜ እኛ በቁጥር አናሳ ስለሆንን ነውን? "

ረሱሉም «እንደውም ያኔ ብዙ ናችሁ ነገር ግን ጎርፍ ሰብስቦ እንደሚያመጣው የተበታተናችሁ ግሳንግስ (የጎርፍ ላይ አረፋ) ናችሁ! አላህም ጠላቶቻችሁ እናንተን የመፍራትን ግርማ ያነሳላቸዋል በናንተ ልብ ውስጥ "ወህን" ን ይጥልባቹሃል! አሉ

ሶሃቢዪም "የአላህ መልእክተኛ ሆይ ወህን ምንድነው? ብሎ ጠየቃቸው

ረሱሉም "ወህን ማለት ዱንያን መውደድና ሞትንም መጥላት ብለው መለሱ»

(صحيح أبي داود 4297)

image
Kirim sebagai pesan
Bagikan di halaman saya
Bagikan di grup
Fedlu Mohammed berbagi sebuah
Tidak bisa diterjemahkan.

⚔ ስለ መህዲ ምን ያውቃሉ??

📚 መህዲ  በመጨረሻው ዘመን ከደጃልና ዒሳ መምጣት አስቀድሞ የሚነሳ ታላቅ ‹‹ኸሊፋ›› ነው። ‹‹መህዲ›› የማዕረግ ስሙ ሲሆን ‹‹ሁዳ›› ከሚለው ቃል የተገኘና ‹‹የተመራ ቅን ኸሊፋ›› ማለት ነው። መጠሪያ ሙሉ ስሙ ደግሞ ‹‹ሙሐመድ ኢብን አብዱላህ አል-መህዲ›› ነው።   

  

ስለ መህዲ በቁርኣን የተነገረ ምንም ነገር አናገኝም። መረጃዎቹ በሙሉ ከሐዲስ የተገኙ ሲሆን ከሃያ በላይ የተረጋገጡ ዘገባዎች ይገኛሉ። ብዙ የሱንና ዑለማዎች ስለ መህዲ የፃፉ ሲሆን ቲርሚዚና አቡ-ዳውድ ራሱን የቻለ ምዕራፍ ሰጥተውታል።   

  

ከሁሉም ታዋቂው ሐዲስ አቡ-ዳውድ የዘገቡት ሲሆን ነቢዩ (ዐሰወ) እንዲህ ብለዋል፡-   

  

‹‹ትንሳኤ ሊቆም አንድ ቀን ቢቀረው እንኳን አላህ ከቤተሰቤ የሆነን፤ ስሙ ከእኔና ከአባቴ ጋር የሚመሳሰል መሪን ሳያስነሳና በበደል የተዋጠችውን ምድር በፍትህ ሳይሞላት አይተዋትም።››  

(አቡ-ዳውድ 4282)   

  

ከዚህ ሐዲስ እንደምንረዳው መህዲ የነቢዩ (ዐሰወ) ቤተሰብ ነው። ስሙም የነቢዩን (ዐሰወ) እና አባታቸውን የያዘ ሲሆን ‹‹ሙሐመድ ኢብን አብዱላህ›› ወይም ‹‹አህመድ ኢብን አብዱላህ›› ነው። የሚመጣውም ዓለም በዙልም በተዋጠችበት በመጨረሻው ዘመን ሲሆን የአላህን ቃል ከፍ በማድረግ ፍትህን ያነግሳል።   

  

ኡሙ ሰላማ (ረዐ) እንደተናገረችው ነቢዩ (ዐሰወ) ‹‹መህዲ በፋጡማ በኩል የሚገኝ ቤተሰቤ ነው።›› ብለዋል። ኢብኑል ቀይም ይሄንን ሐዲስ ሲያብራሩ ‹‹መህዲ የሐሰን ዘር ሲሆን አል-ሐሰን ለሙስሊሙ አንድነት ሲሉ ኸሊፋነታቸውን አሳልፈው በመስጠታቸው ምክንያት አላህም በመጨረሻው ዘመን ከቤተሰባቸው ታላቅ ኸሊፋ በማስነሳት ክሷቸዋል።›› ሲሉ ፅፈዋል።  

(አቡ-ዳወድ 11/373)   

  

አቡ-ሰዓድ አልኩድሪ በዘገቡት ሐዲስ ነቢዩ (ዐሰወ) ስለ መህዲ ገፅታ ሲናገሩ ‹‹ቁመቱ ረጂም፣ ትከሻው ሰፊ፣ አፍንጫው አጠፍ ያለ ነው።›› ብለዋል።   

(አቡ-ዳውድ 4265)   

  

መህዲ የሚነሳበትን ቦታ በተመለከተ የተለያዩ ዘገባዎች አሉ። ከፊሎቹ ከሻም ከፊሉ ከኹራሳን ሌላው ደግሞ ከመዲና እንደሆነ ይናገራሉ። ኢብን ከሲር የሁሉንም ሐዲሶች ጥቅል ሀሳብ ሲያስቀምጡ ‹‹የሚነሳው ከምስራቅ ነው። ከዚያም ወደ መካ ይሄዳል። ሰዎችም በከዓባ ዙሪያ ቃልኪዳን ይገቡለታል።›› ብለዋል። እንዲሁም በሌላ መጽሐፋቸው ‹‹በሐዲስ በተጠቀሰው መሰረት ባንዲራው ጥቁር ነው።›› በማለት አብራርተዋል።   

(አልቢዳያህ ወልኒያህ 19/63፤ አልፊታን ወልመላሂም 1/49)   

  

ኢማም አህመድ እንደዘገቡት መህዲ መሪነት ሲመረጥ ፍላጎቱም ክህሎቱም አልነበረውም። እናም ‹‹አላህ በአንድ ሌሊት ይመራዋል።›› ብለዋል (ዐሰወ)። ኢብን ከሲር ሐዲሱን ሲያብራሩ፡- ‹‹ይህ ማለት አላህ ይረዳዋል፣ ከዚህ በፊት ያልነበረውን ችሎታም ይሰጠዋል ማለት ነው።›› ብለዋል።  

(አህመድ 2/58/ አልፊታን ወልመላሂም 1/29)   

  

መህዲ ኸሊፋነትን ከተረከበ በኋላ ሙስሊም አገራትን በአንድ በማፅናት በቀደመው ኢስላማዊ አስተዳደር ስር ያስገባቸዋል። ከዚያም በቡኻሪ እና ሙስሊም (2897) እንደተዘገበው ከሮማውያን ጋር የመጨረሻው ታላቁ ጦርነት ‹‹አል-መልሃማ አል-ኩብራ›› ይካሄዳል። ሙስሊሞችም ዳቢቅ ላይ ድል ደርጋሉ። ከዚህ በፊት ያልተከፈቱ አገራትንም ይከፍታሉ። ከዚያ በኋላ ሙስሊሞች በየትኛውም ኃይል አይሸነፉም። አላህ አማኞችን ከፍተኛ የሀብት መትረፍረፍ ይባርካቸዋል።   

  

ሸይህ ዑመር ሱለይማን አል-አሽቀር ሐዲሱን መሰረት በማድረግ እንደተናገሩት ‹‹ይህ ጦርነት ከባድ ውድመትን ስለሚያስከትል ዓለም አሁን ካለችው ስልጣኔ ወደኋላ በመመለስ እንደ ጥንቱ በጦር በጋሻ በፈረስ መጠቀም ይጀምራሉ።›› ብለዋል።  

(አል-ቂያማህ አስ-ሱግራ 275)   

  

መህዲ ታላቅ ጦርነት አድርጎ ሙስሊሞችን የበላይ ቢያደርግም ጊዜው የቂያማህ ቀን መቃረቢያ በመሆኑ ከባባዶቹ ፊትናዎች ይከሰታሉ። ከእነዚህም መካከል ቀዳሚው የደጃል መነሳት ነው። እሱን ተከትለው የዕጁጅና መዕጁጆች ከጉድጓዳቸው ይወጣሉ። በዚህ ጊዜ አላህ ዒሳን (ዐሰ) ለእርዳታ ይልከዋል።   

  

በሐዲስ እንደተጠቀሰው ዒሳ (ዐሰ) ወደ ምድር የሚወርደው በፈጅር ሰላት ወቅት ነው። ነቢዩ (ዐሰወ) ስናገሩ ‹‹መህዲ ዒሳን አሰግደን ይለዋል። ዒሳም እናንተ መሪዎች መሆናችሁ ከቂያማህ ምልክቱ ነውና አንተ አሰግደን ይለዋል። ዒሳም ከመህዲ ኋላ ተከትሎ ይሰግዳል።›› ብለዋል።  

(ሙስሊም 225)   

  

ከዚያ በኋላ ዒሳ ከሙስሊሞች ጋር በመሆን የዕጁጆችንና ደጃልን በመጋደል በአላህ ዕርዳታ ያጠፋቸዋል። ነቢዩ (ዐሰወ) እንደተናገሩት ‹‹ሙስሊሞች ለሰባት ዓመታት ያህል የየዕጁጆችን አጥንት ቀስትና ጋሻ ለማገዶነት ይጠቀሙበታል።   

  

መህዲ በኸሊፋነት የሚቆይባቸው ዓመታት ‹‹ሰባት›› እንደሆኑ አብዛኛዎቹ የሐዲስ ምሁራን ይናገራሉ። ከእነሱ መካከል አንዱ የኢብኑ ማጃህ ሲሆኑ ነቢዩ (ዐሰወ) ‹‹መህዲ ሰባት አጭር ጊዜያትን ይቆያል።›› ማለታቸውን ዘግበዋል።  

(ኢብን ማጃህ 4039)   

  

አል-መህዲ እስኪመጣ ሙስሊሙ ጂሐድን በመተው መጠበቅ ይኖርበታል? ለሚለው ጥያቄ ሸይህ ሙሐመድ ሷሊህ አል-ሙነጂድ በፈትዋ ገፃቸው እንዲህ ብለዋል፡-   

  

‹‹ከጂሐድ መዘንጋት ከከባባድ ወንጀሎች አንዱ ነው። አላህ ያዘዘው ሁሉም የራሱን ግዴታ እንዲሞላ ነው። መህዲ የራሱ ጂሐድ አለው። ይሄም ህዝብ የራሱን ጂሐድ ማድረግ ግዴታው ነው።   

  

#አላህ በቁርኣኑ እንዲህ ይላል፡-   

  

وَقَاتِلُوهُمْ حَتَّىٰ لَا تَكُونَ فِتْنَةٌ وَيَكُونَ الدِّينُ كُلُّهُ لِلَّهِ ۚ فَإِنِ انتَهَوْا فَإِنَّ اللَّهَ بِمَا يَعْمَلُونَ بَصِيرٌ   

  

ሁከትም እስከማትገኝ ሃይማኖትም ሁሉ ለአላህ ብቻ እስከሚኾን ድረስ ተጋደሏቸው፡፡ ቢከለከሉም አላህ የሚሠሩትን ሁሉ ተመልካች ነው፡፡  

[ ሱረቱ አል-አንፋል - 39 ]

Kirim sebagai pesan
Bagikan di halaman saya
Bagikan di grup
Fedlu Mohammed berbagi sebuah

📌ቅርቢቱ ህይወትና ጌጧን የሚሹ የሆኑ ሰዎች እንሞላላቸዋለን

مَن كَانَ يُرِيدُ الْحَيَاةَ الدُّنْيَا وَزِينَتَهَا نُوَفِّ إِلَيْهِمْ أَعْمَالَهُمْ فِيهَا وَهُمْ فِيهَا لَا يُبْخَسُونَ

ቅርቢቱን ሕይወትና ጌጧን የሚሹ የሆኑትን ሰዎች ሥራዎቻቸውን (ምንዳዋን) በእርሷ ውስጥ ወደነሱ እንሞላላቸዋለን፡፡ እነሱም በርሷ ውስጥ ምንም አይጎድልባቸውም፤

أُولَٰئِكَ الَّذِينَ لَيْسَ لَهُمْ فِي الْآخِرَةِ إِلَّا النَّارُ ۖ وَحَبِطَ مَا صَنَعُوا فِيهَا وَبَاطِلٌ مَّا كَانُوا يَعْمَلُونَ

እነዚያ እነርሱ በመጨረሻይቱ ዓለም ለእነርሱ ከእሳት በቀር የሌላቸው ናቸው፡፡ የሠሩትም ሥራ በርሷ ውስጥ ተበላሸ፡፡ (በቅርቢቱ ዓለም) ይሠሩት የነበሩትም በጎ ሥራ ብልሹ ነው፡፡

አል ሁድ 15&16📚📚

Kirim sebagai pesan
Bagikan di halaman saya
Bagikan di grup
Tidak bisa diterjemahkan.

አቡሁረይራ ረ.ዐ እንዳስተላለፉት የአላህ መልክተኛ ሰ.ዐ.ወ ከስራዉ ሁሉ በላጩ የትኛዉ ነዉ የሚል ጥያቄ ቀረበላቸዉ በአላህና በመልክተኛዉ ማመን። አሉ ከዚያስ? ተባሉ በአላህ መንገድ ላይ መታገል (ጂሃድ ፊ ሰቢሊላህ )በማለት መለሱ።

Kirim sebagai pesan
Bagikan di halaman saya
Bagikan di grup
Fedlu Mohammed berbagi sebuah
Tidak bisa diterjemahkan.

"ሰሞኑን በጣም ስያስጨንቀኝ የነበረው ትልቁ ጉዳይ😱😱😱

ከቤት ወደ ሌላ ቤት መቀየር ካሰብኩኝ በጣም ቆይቷል

ነገርግን የስጨንቀኝ የነበረው ቁም ሳጢኑ ላይ 2ኪስ ውስጥ የማሂሬ ልብስ ነው ያለው ከእናቱስ እንዴት አርጌ ከቁም ሳጥኑ ላውጣው ግን ደሞ ግዴታዬ ሁኖ ዛሬ ሳወጣው ገዝቼለት ምንም ያለበሰው ልብስ አገኘው እናቱ ቁም ሳጥኑንን ተደግፋ ሙቶ ላልቀበረችው ልጅ አለቀሰች እኔንም በጣም ከፍቶኝ ነው የዋልኩት"😭😭አባቱ እንዲ ብሎ ፖስቶ ሳየዉ ወደናንተ ሼር አደረኩላቹ ምክኒያቱም ካገኛቹለት ጥሩ ካልሆነ ግን በዱአእ ከጎኑ እንድትሆኑ ለማስታወስ አላህ ሆይ እነዚ የተነፋፈቁ ቤተሰቦችን አገናኝልን🤲

እባካችሁ ሼር ሼር 0911334363/0913915460

image
Kirim sebagai pesan
Bagikan di halaman saya
Bagikan di grup