UMMA TOKEN INVESTOR

About me

ይህ የዳሩል አርቀም የበጎ አድራጎት ማህበር ይፋዊ የኡማ ላይፍ ገፃችን ነው በዚህ ፔጅ • የተለያዩ ከዳሩል አርቀም እንቅስቃሴዎች ጋር ተያያዥነት ያለው ስራ • ወቅታዊ ኢስላማዊ ጉዳዩች •ከሌላ ቦታዎች የተገኙ ኸይር ስራዎችን እንለቅበታለን ፔጃችንን ኮፒ ሊንክ በማድረግ ተደራሽነታችንን

🎉በበጎነት ወደ ጀነት መሄጃ መንገዱን በፅኑ አቋም አጥብቆ ከያዘ እነሆ ሶስት አመታት ተቆጠሩ። በአይታሞች ፈገግታ በአዛውንት ምርቃት በመሻኢኾች ዱዓ በእናንተ ቤተሰቦቻችን አለን ባይነት መስመር ውስጥ አልፎና ደምቆ ከዳዴ አንስቶ እነሆ በአላህ ፍቃድ በሶስት አመታት ውስጥ በሁለት እግሩ ቆሟል። ታድያ ይሄን ጉዞውን በጣም በተሻለ እና ከዚህም ከፍ ባለ ፣መጥቼበት በማላውቀው አዲስ ስራ፣ ያለፉት መንገዶቼን በወፍ በረር ሶስቱን አመት አብራችሁኝ ላሳስለፋችሁ በመድረክ አሳያችኋለው ሲል መድረኩን አሰናድቷል። የመልካምነት መንገድ እንኳን የተሳካው ውጣ ውረዱም ያጓጓልና ጥር በእሁድ ቀን ወርሀ ጥር 19/2016  በሀገር ፍቅር ቲያትር ከጠዋቱ 2:00 ሲል  የሚጀመር ስለሆነ፤ በመድረኩ ላይ በመገኘት የድግሳችን ድምቀት ሁኑ እንላለን ።

--------------------------------------------------------

መግቢያ : በነፃ

ስልክ :0939963771/0913219422 ላይ በማናገር ትኬት ይውሰዱ

ማርፈድ : በፍፁም አይቻልም 6 ሰዓት እንጨርስላችሁ ዘንዳ😉

በቴሌግራም ለማናገር :@abu_adil1  እና @Amtullahiiiiii  ላይ ጎራ በሉ ❗️

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group

....በቀን ቅልጥ ያሉ አላህን አምላኪ መናኞች ነበሩ።በዚህ ሁሉ መሃል ታድያ ይገዛሉ፣ይሸጣሉ፣አትክልቶችን ያለማሉ፣ያገባሉ፣ቤተሰቦቻቸውን ይንከባከባሉ፣ከዚያም አልፈው የተቸገሩትን ይረዳሉ። መልካም ስራዎቻቸው እንደ ተራሮች የተቆለሉ ቢሆንም ከእነርሱ በኋላ የመጡ ብዙ ትውልዶች እንደተቄሉ ብጤ በራሳቸው አይመፃደቁም፣ አይደነቁምም። ከእነርሱ በላይ የፅድቅን መንገድ የተመላለሰበት እንደሌለ በማሰብ ለራሳቸው ከፍ ያለ ግምት በመስጠት ከመኩራራት ይልቅ ሌሎችን የሚያልቁና ራሳቸውን ሁልጊዜም ዝቅ አድርገው የሚመለከቱ ነበሩ።

:

የአላህ መልዕክተኛ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ውድ ባልደረቦች የሆኑት ሶሐቦች (አላህ የሁሉንም ሥራ ይውደድላቸው።)

ካነበብኩት🤗🤗

https://t.me/darularkemfamily

Telegram: Contact @darularkemfamily

Telegram: Contact @darularkemfamily

ይህ የዳሩል አርቀም ኢስላማዊ ጀመአ ቤተሰቦችን ምናፈራበት group ነው ።በዚህ group ላይ የዳሩል አርቀም ስራ እንዲሁም ከቻሪቲ ጋ የተያያዙ ምርጥ እና አስተማሪ ጽሁፎች በደንብ ያገኛሉ ። ወደ groupu በመቀላቀል የኸይር ስራው ተካፋይ ይሁኑ ወደ ጀመአችን መግባት የምትፈልጉ ወንዶች? @Bilugolden ሴቶች ? @Amtullahiiiiii g ላይ ማናገር ትችላላችሁ
Send as a message
Share on my page
Share in the group

እሁድ 14/04/2016

:

በትናንትናው እለት በበጥበብ ኢንስቲትዩት አማካኝነት በተዘጋጀ የስልጠና ፕሮግራም ዳሩል አርቀም የበጎ አድራጎት ማህበር እና ሌሎችም ከመገናኛ መስመር ወደዛ ያሉ ስብስቦች ተሳታፊ የሆኑበት በአይነቱ የተለየ የስልጠና ፕሮግራም ሲከወን ውሏል።

___

➡️ዳሩል አርቀም የበጎ አድራጎት ማህበር እና ሌሎች ኮተቤ እና ለሚ ኩራ አካባቢ ጀመዐ መስርተው ለመንቀሳቀስ የሚሞክሩ ስብስቦች በአንድነት የኢስላም ልዩ መገለጫዎች በሚል ርዕስ እና ግማሹን የቀን ክፍል ደግሞ ለኢስላም መስራት በሚሉ ርዕሶች ላይ ስልጠናውን ተቋድሷል።

👉🏻በጠዋቱ ክፍለጊዜ ዑስታዙ "በአለም ላይ ካሉ ብዙ ሺ...ሺ እምነቶች ኢስላም በምን ተለይቶባችሁ ሙስሊም ሆናችሁ? " በማለት ፕሮግራሙን ሀ ብሎ የጀመረ ሲሆን አለም የሚታይበትን የተለያዩ መንገዶች በማንሳት እንዲሁም ኢስላም ከሀይማኖትም ከፍ ያለ ዲን እንደሆነ "ኢስላም አጠቃላይ የህይወት አቅጣጫ ነው" በማለት ውብ የሆኑ ሀሳቦችን የኢስላም ልዩ መገለጫዎች በሚል ርዕስ ሲያነሳሳልን ቆይቷል። እኛም ጥሩ ነገር እንደወሰድንበት ተስፋ አለን አልሀምዱሊላህ።

👉🏻በከሰዐቱ ክፍለ ጊዜ ደግሞ ለኢስላም መስራት ምን ማለት ነው? ሰዎችን ወደ አላህ የመጥራት አላማ እንቅፋቶች ምንዳዎች ብዙ ብዙ ጉዳዮች ላይ ከዑስታዝ አብዱልመጂድ ጋር በማንሳት ጥሩ ቆይታ ተደርጓል ።በዚህ ፕሮግራም ለኢስላም መስራት ግዴታ መሆኑን የሚቃወም አለ ወይ? ተብሎ እንደሌለ ሲያይ ሁሉም በያለበት ግዴታውን ይወጣ በማለት ሀላፊነታችንን እንድንወጣ አሳስበውን እኛም ኢንሻአልላህ ብለን መጥተናል።

👉🏻 ሶስተኛው ፕሮግራም ግን ያው ከተለያየ ጀመዐ ግን የዳዕዋ ድርቅ የመታው ከሚባሉ አካባቢዎች እንደመምጣታችን በየአካባቢያችን ያሉ ኢስላሚክ እንቅስቃሴዎችን እና ጀመዐችንን አስተዋውቀናል በፕሮግራሙ የተሳተፉት ጀመዐዎች ዳሩል አርቀም የበጎ አድራጎት ማህበር ፣ዳሩሰዐዳ፣ኢብን ሙኽታር ሲሆኑ ይህም አካባቢን ለመቀየር ግድ የሚሰጣቸው ብዙ ወጣቶች እየተፈጠሩ እንደሆነ ማሳያ እንደሚሆን ተስፋ እናደርጋለን።

🩶🩶🩶በመጨረሻም እንደሁሌው ይህን ፕሮግራም አዘጋጅተው ለጋበዙን በጥበቦች እንዲሁም ከእኛ ጋር የተሳተፉትን ሌሎች ጀመዐዎች እናመሰግናለን።🤍🤍🤍

Send as a message
Share on my page
Share in the group

ቅዳሜ 5 ሰዐት ኡስታዝ ሷዲቅ ሙሀመድ ( አቡ ሀይደር ) በኮተቤ ይከትማል!!!

ኮተቤ በትልልቅ ኡስታዞች ማበብ ከጀመረች የሰነበተች ሲሆን የዚህኛዉ ፕሮግራም ለየት የሚያደርገዉ የአቡ ሀይደር ጣፋጭ አንደበቶች እንደ ማር የሚፈሱበት መሆኑ ነዉ ❗️❗️❗️

ይህን ፕሮግራም በማዘጋጀት እንዲሁም ለኡማዉ እንዲደርስ በማድረጋቸዉ የሁነይን መስጂድ ወጣት ጀመዐዎች አላህ ስራችሁን ይቀበላችሁ🙏🙏🙏

ቅዳሜ 5:00 በሁነይን (አቡሽ ሱቅ እንገናኝ)

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group

አንድም ቀን መዎጮዋን አቋርጣ ማታውቀው እህታችን ፋጡማ አረቦ በህዳር ወርም መዎጮዋን ሳትረሳ ልካልናለችና አር ራህማኑ ምንዳዋን ያለገደብ ይለግሳት

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group