bilal kedir Profile Picture
UMMA TOKEN INVESTOR

bilal kedir berbagi sebuah
7 Bulan Terjemahkan
Tidak bisa diterjemahkan.

It hurts, it hurts a lot. But I know you are testing me. I know you see me struggle day in and day out. No love is greater than Your love. I shall be patient for Your sake. Fix my heart, comfort my soul Ya Allah

image
image
Kirim sebagai pesan
Bagikan di halaman saya
Bagikan di grup
bilal kedir berbagi sebuah
Tidak bisa diterjemahkan.

#ሸይኽ ኢብን ባዝ ተጠየቁ ፡ ሙቅ ውሃን በምናፈስበት ጊዜ

ቢስሚላህ እንላለንን፣ ይህም ጂን ቦታው ላይ ይኖራል ብሎ

በመፍራት ነው

መልስ፡

"አዎን! ቢስሚላህ ይበል ምን አልባት ቦታው ላይ ጂን ካለ

እንዲነቃ ለማድረግ ነው" ከዛም ሽይኹ እንዲህ አሉ" በርግጥም

በአንድ ወቅት አንድን ሰው ጂን ይዞት በሚቀራበት ቦታ ተገኝቼ

ነበር

#ሩቃ የሚያደርገው ሰው በሰውየው ላይ ለተደበቀው ጂኒ "ለምን

ያዝከው "አለው

#ጂንውም "የሞቀ ውሃ በአንዱ ልጄ ላይ ደፋና ገደለው "አለ

#የሚቀራዉ ሰውዬ ደግሞ "እሱ ልጅህ በቦታው መኖሩን

ስላላወቀ ነው" አለው

#ጂኒው ደግሞ "ለምን ቢስሚላህ አይልም ነበር እንዲያሳውቀው

(እንዲያነቃው)"

#ሽይኽ ዘይድ አል መድኸሊ ረሂምሁሏህ እንዲህ አሉ ፡

"ለማንኛውም የሞቀ ውሃ በፍሳሽ ትቦዎችም ይሁን በመሬት ላይ

አይደፋም ምክኛቱም መሬት በነዋሪዎች የተሞላች ነች

ምናልባትም በጂኖች አለም ወይም በትንንሽ ፍጡሮች ላይ ያርፋል

በዚህም ለበቀል ይነሳሱና ይይዙታል።ስለዚህ አንድ ሰው የሞቀን

ውሃ መድፋት ከፈለገ በቀዝቃዛ ውሃ ቅዝቃዘው የማያስቸግር

እስኪሆን ያብርደውከዛም ከፈለገ የፍሳሽ ትቦዎች ውስጥ ከፈለገ

መሬት ላይ ያፍሠው" ንግግራቸው እዚህ ጋር አለቀ ረሂመሁሏህ.

፟፟=========================

#ጉዳዩ አደገኛ ነው ሙስሊሞች ሆይ ነቃ በሉ ለወንድሞቻችሁ

ለእህቶቻችሁ ለእናቶቻችሁ አድርሱላቸው ስንትና ስንት እህቶች

በዚህ ሰበብ ችግር ውስት ይገባሉ ፓስታ የቀቀሉበትን ውሃ

አውጥተው በመድፋት ስንቱ ተለክፎዋል ስለዚህ አድርሱላቸው!

image
Kirim sebagai pesan
Bagikan di halaman saya
Bagikan di grup
bilal kedir berbagi sebuah
7 Bulan Terjemahkan
Tidak bisa diterjemahkan.

በፍልስጤሟ ምድር ጋዛ ወራሪዋ እስራኤል ከሰማይ የወረወረችው የድሮን ቦንብ ቤታቸው ዶግ አመድ አድርጎ ላያቸው ላይ ተናደ። አስራ አንድ ሙሉ ቤተሰብ ከፍርስራሹ መሐል ተጋደመ። ቦታው ላይ የደረሱት የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች ቆፍረውና ቧጠው ሲያወጧቸው ሁሉም ሞተው እናት ነፍሷ ከጀሰዷ ሊላቀቅ የመጨረሻ እስትንፋሷ ላይ ነበረች።

በዝግታ አይኗን እያስለመለመች ታቃስታለች። በሆዷ የታቀፈችው ፅንስ በህይወት ይቆይ ዘንድ እግሯን ከፈት ልጇን ደገፍ አድርጋ ተንጋላለች። ሆስፒታል እንደደረሰች እስትንፋሷ ተቋርጦ ጌታዋን ስትገናኝ ፅንሱ ግን በህይወት ነበር። ዶክተሮች በአላህ ፈቃድ የልጁን ህይወት ማትረፍ ቻሉ። አስራ አንድ ሙሉ ቤተሰቦቹን ባጣበት ቅፅበት እርሱ ይህቺን አለም ተቀላቀለ። መገን የአላህ ስራ ጉድ ነው የእሱስ አቻቻል።

mahi mahisho

Kirim sebagai pesan
Bagikan di halaman saya
Bagikan di grup
bilal kedir berbagi sebuah
Tidak bisa diterjemahkan.
7 Dilihat
Kirim sebagai pesan
Bagikan di halaman saya
Bagikan di grup
bilal kedir berbagi sebuah
Tidak bisa diterjemahkan.

የአህባሽ እምነትና ስህተቶቹ

መግቢያ

ምስጋና ሁሉ ለአለማቱ ጌታ ለአሏህ ይገባው የአሏህ ሰላምና ውዳሴ በነብያችን ላይ ይሁን፦

ከእስላምና ውጭ አሏህ ዘንድ ተቀባይነት ያለው ሀይማኖት የለም።

አላህ ዘንድ (የተወደደ) ሃይማኖት ኢስላም ብቻ ነው። አል ኢምራን፡19

እስልምና ማለት በየትኛውም ዘመን ለየትኛው የሰው ዘር ምንም አይነት እንከን የሌለበት ለፍጥረታት ፍትህና ለምድር የሚበጅ ለተከተለውና አጥብቆ ለያዘ ክብርና አሸናፊነትና ለሁለቱም ሀገር ስኬትና መዳን ያረጋገጠ ሀይማኖት ነው።

(አላህ እነዚያን ከእናንተ ያመኑትንና መልካም ሥራዎችን የሠሩትን እነዚያን ከእነሱ በፊት የነበሩትን እንደተካ በምድር ለይ በእርግጥ ሊተካቸው፣ ለእነሱም ያንን የወደደላቸውን ሃይማኖታቸውን ሊያደላድልላቸው፣ ከፍርሃታቸውም በኋላ ጸጥታን ሊለውጥላቸው ተስፋን ቃል ሰጥቷቸዋል፡፡ .......) አን-ኑር ፡55

(ከወንድ ወይም ከሴት እርሱ አማኝ ኾኖ በጎን የሰራ መልካም ኑሮን በእርግጥ እናኖራቸዋለን፡፡ ይሠሩትም ከነበሩት ነገር በመልካሙ ምንዳቸውን እንመነዳቸዋለን)።

አነህል፡97

እንደዚሁም ደግሞ እሱን ከመቀበልና ከመተግበር አሏህ ትዛዝ በመራቅ ውድቅና አፀያፊ ተግባራት የፈጣሪና የፍጡር መብቶች በመዳፈር ምድርን በተለያዩ አምባገነንነት ክፋት እና ሌሎች ሰይጣናዊ አመለካከቶች በመንሰራፋታቸዉ ምክንያት የማህበረሰብ ውርደት ሽንፈትና የበታችነት የኑሮ ውድነት የበረካ ማጣት የእርስ በእርስ ጦርነት ክፍፍል ዘረኝነት አደጋዎች መብዛትና ድንገተኛ መሆን ወረርሽኝ ድርቅ የጎርፍ አደጋ የመሬት መንቀጥቀጥ የመሳሰሉ ቀውሶች እንጀሚያስከትል አሏህም በማያሻማ ቃሉ የተናገረ ነብዩም በበርካታ ሀዲሳቸው አብራርተዋል።

ለዚህም ማረጋገጫ መለኮታዊ መልዕክት በሚመጣበት ዘመን የነበሩ ማህበረሰቦች ነብዩና የእርሳቸው ባልደረቦች በአሏህ በማመናቸው መልዕክተኛውና ይዞት የመጣው መልዕክት በመቀበላቸው የታዘዙት በመታዘዝ ራቁ የተባሉትን በመራቃቸው ምክንያት የክፍለ ዘመኖች ሁሉ ምርጥ የተባለለትን የማህበረሰብ ስኬትና ስዕብና ማሳለፉ ኢብኑ መስዑድ በአስተላለፉት ዘገባ በሁለቱ ሶሂሆች እንደመጣው ነብዩ "የሰዎች ምርጥ እኔ ያለውበት ክፍለ ዘመን ነው ከዚያም ቀጥሎ ከዚያም ቀጥሎ" እንደተናገሩት እና አሏህም በቃሉ

(ከስደተኞቹና ከረዳቶቹም ሲኾኑ የመጀመሪያዎቹ ቀዳሚዎች እነዚያም በበጎ ሥራ የተከተሏቸው አላህ ከእነሱ ወዷል ከእርሱም ወደዋል፡፡ በሥሮቻቸውም ወንዞች የሚፈሱባቸውን ገነቶች በውስጣቸው ዘለዓለም ነዋሪዎች ሲኾኑ ለእነርሱ አዘጋጅቶላቸዋል፡፡ ይህ ታላቅ ዕድል ነው፡፡) አተውባ፡ 100 በማለት አረጋግጦላቸዋል።

በመቀጠልም ከእዚህ ከብቻኛው እስልምና አሏህ ከሰማይ ከወረደው ህግጋት የክፈለ ዘመኖች ሁሉ ምርጥ የተባለትን ክፍለ ዘመን አልፎ ሌላ ሲመጣ የሰዎች አስተሳሳብ እና ዝንባሌ በተንስራፋ ሙስሊሙ ማህበረሰብ በራሱ ከትክክለኛ እምነትና አስተምሮ እንደሚርቅ ነብያችን በንግግራቸው " ከእናንተ እድሜው የቆየ ሰው ብዙ ልዩነቶችን ያያል፤ የእኔን ሱና አጥብቃቹ በመያዝ አደራቹ" እንዳሉትም በእርካታ ልዩነቶችና አለመግባባቶች እንደዚሁም መናጋቶች በርካታ አንጃዎች በቡድንም ይሁን በግለሰቦች ደረጃ ከእዚህ ትክክለኛው አስተምሮ የወጡ ሆነው ይስተዋላሉ።

ከእነዚህ ከጥመት ቡድኖች መካካል በቅርቡ 2004 ከሊባኖስ የመጣው አገራችን በከፍተኛ ሁኔታ ከገጠር እስከ ከተማ ከተራው ማህበረሰብ እስከ ትልልቅ መሻይሆች ያተራመሰው በወቅቱ ተቃውሞ የገጠመው ከመሰረቱ ጀምሮ ከፍተኛ የሆኖ በጥመቶች በስህተቶችና በሽርክያት የተጨማለቀ ለውይይትና ለመማር በሩ ዝግ ያደረገና አሁን ላይ በተለያዩ የአገራችን ክፍሎች መርከዝና መስጅዶች እንደዚሁ ትልልቅ ባለሀብቶችና በተለያዩ መስሪያ ቤትች በሀላፊትና የሚሰሩ ግለሰቦችና ባለስልጣናት እንደዚሁም ደግሞ ምንም የማያውቀው ማህበረሰብ ከጎኑ በማድረግ ቁራዓንና ሀዲስ እናስተምራለን በሚል ሙስሊሙን ማህበረሰብ ሊያስቀረው እየሞከረ የነበረው በዓድ አምልኮ በአዲስ መልክ እንዲሰራፋና ተጠናክሮ እንዲቀጥል በመጤ እና መሰረተ ቢስ ድርጊቶች የተሞላና ከነብዩ አስተምሮ ውጪ የሆነው የአህባሽ ቡዱን አንዱ ነው። እንደ አካባቢያችን ደግሞ በተለይ በስልጤ አብዛኛ አካባቢ እንደ ጉራጌ እነደዚሁ በስፋት ጉብሬ ጌቶ እነምር እንደ ጉመር ቦሌ ቀቡል ባድ አበኬና የተለያዩ ቦተዎች መጠነ ሰፊ እንቅስቃሴ እያደረገ ይገኛል። አሏህ ካለ ለወደፊት የዚህን እምኑቱ የተበላሸ ቡዱን ስህተቶች በተከታታይነት የምናቀርብ ሲሆን ለትችት ለፉከራ እኔ ብቻ ልክ እንደዚሁም ለእልክ ሳይሆን በመጀመሪያ ካለብን የዲን ሀላፊነት ሌላው እነሱን ከስህተታቸው አውቀው ወደ ቁራዓንና ሱና እንዲመለሱ በመቀጠል ባለማውቅ በስህተታቸው የተሸወደው ሙስሊሙ ማህበረሰብ አውቆ አንዲጠነቀቃቸው ብቻ ነው።

በአሏህ ፈቃድ ለሚቀርቡ ለማንኛውም አስተያየት ሀሳብና ማስተካከያዎች በመማማር መልኩ፦

📞0943113278

image
Kirim sebagai pesan
Bagikan di halaman saya
Bagikan di grup