Sena Gelalcha Profile Picture
UMMA TOKEN INVESTOR

Translation is not possible.
00:00 / 00:00
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.
image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.
00:00 / 00:00
4 views
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.
00:00 / 00:00
6 views
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.
#አንብቤው_ከተመቸኝ_ላካፍላችሁ!
🔙 ሀዘን እና ትካዜ ወደ ኋላ ጣላቸው!
🌱ኢብኑል ቀይም አላህ ይዘንለት እንዲህ ይላል፦
✍"ሀዘን ቁርኣን ውስጥ በክልከላ መልኩ ወይም በማራቅ መልኩ ቢኾን እንጂ አልተጠቀሰም
ልክ አላህ እንዳለው
{ وَلَا تَهِنُوا وَلَا تَحْزَنُوا }
{አትስነፉ አትዘኑም}
{ فَلَا خَوْفٌ عَلَيْهِمْ وَلَا هُمْ يَحْزَنُونَ }
{ፍርሃት የለባቸውም፤ እነርሱም አያዝኑም}"
🔵የዚህ ሁሉ ሚስጥሩ
👉🏽 ሸይጣን ከሚያስደስተው ነገር ሁሉ ትልቁ ሙዕሚን የኾነ ሰው አዝኖ ማየቱ ነው። ከዚያም ከመንገዱና ከጉዞው ሊገታው።
🔵በእርግጥም ነብዩ ሙሐመድ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ከሐዘን ተጠብቀዋል
"اللهم إني أعوذ بك من الهم والحزن"
[አላህ ሆይ እኔ ከሀዘንና ከጭንቀት በአንተ እጠበቃለሁ] በማለት
🌱ኢብኑል ቀይም በድጋሚ እንዲህ ይላል፦
✍"ሀዘን ብሎ ማለት
ቀልብን ያደክማል፣ ቆራጥነትን ያከሽፋል፣ ፍላጎትን ይጎዳል፣ ወደ ሸይጣንም ምንም ተወዳጅ ነገር የለም ሙዕሚን አዝኖ እንደ ማየት"
💡ስለኾነም፦
🍎ሀዘንን ራቁ!
   መልካምን ከጅሉ!
      በአላህ ላይ መልካም ግምት ይኑራችሁ!
       አላህ ዘንድ ባለው ተማመኑ
          በአላህም ላይ ተመኩ
              በአላህ ፍቃድ በሁሉም ሁኔታ ደስተኞች ትኾናላችሁ
💡ብትመለከት፦
✍አላህ ብዙ ነገራቶች ሳትጠይቀው ሰጥቶሃል። ስለዚህ አላህ የምትፈልገውን ነገር እንደ ማይከለክልህ እርግጠኛ ሁን። ምን አልባት ግን አለ መሰጠትህ የተሻለልህ ካልኾነ በስተቀር።
🌱ምን አልባት፦
✍አንተ ተኝተህ ሳለህ የሰማይ በሮች ላንተ ዱዐ በሚያደርጉልህ ሰዎች እየተንኳኩልህ ይኾናል።
👉🏽ድሃ ኾኖ የረዳኸው፣
  👉🏽አዝኖ ያስደሰትከው፣
    👉🏽የተጣበበ ኾኖ ያቃለልክለት፣
       👉🏽እያለፈ ብቻ ፈገግ ያልክለት
🤲እጁን ዘርግቶ እየለመነልህ ሊኾን ይችላል።
👇🏾
👉🏽መልካምን ከመስራት መቼም አትቆጠብ
🌱ከቀደምቶች አንዱ እንዲህ ይላል፦
✍"አላህ የኾነ ነገር እጠይቀዋለሁ, ያንን ነገር ከሰጠኝ አንዴ እደሰታለሁ፤  ያንን ነገር ካልሰጠኝ ግን አስር ጊዜ እደሰታለሁ፤ ምክንያቱም መሰጠቴ የእኔ ፍላጎት ነበር አለመሰጠቴ ደግሞ የአላህ ፍላጎት ነው።"
🌱ሌላኛው ደግሞ እንዲህ ይላል፦
✍"ህይወት አጭር ናት።
      👉🏽በሀዘን፣
         👉🏽በጭንቀትና
            👉🏽በጥበት
                👉🏽አታሳጥራት"
🤝በያላችሁበት የአላህ እዝነትና ጥበቃ አይለያችሁ🤲
Send as a message
Share on my page
Share in the group