UMMA TOKEN INVESTOR

1, ረሱል ﷺ ከሶሃቦቻቸው ጋር ቁጭ ብለው በዱኒያ ላይ በጣም ስለሚዎዷቸው ነገሮች እየተጨዋወቱ እያሉ ነብዩ ﷺ አቡበክርንረ.ዐ "ያ አቡበከር አንተ በዱኒያ ላይ በጣም የምትወደው ነገር ምንድነው?" ብለው ጠየቁት።

አቡበክርም ረ.ዐ "3 ነገሮችን እወዳለሁ:-

1.ከአንቱን ጋር መቀመጥ፣

2.አንቱን ማየት፣

3.አንቱ ባዘዙዋቸው ነገሮች ላይ በሙሉ ገንዘቤን መለገስ" ብሎ መለሰ።

°

ዑመርን ረ.ዐ በተራው ጠየቁት "አንተስ ያዑመር ?"

"በዱኒያ ላይ 3 ነገሮችን እወዳለሁ

1.በድብቅ እንኳን ቢሆን በመልካም ነገር ማዘዝ፣

2.በግልጽ እንኳን ቢሆን ከመጥፎ ነገር መከልከል፣

3 መራራ እንኳን ቢሆን እውነትን መናገር።" ብሎ መለሰ።

°

ዑስማንን ረ.ዐ ጠየቁት "አንተስ ያዑስማን?

በዱኒያ ላይ 3 ነገሮችን እወዳለሁ:-

1.ሰዎችን ማብላት፣

2.ሰላምታን ማብዛት፣

3.ሰዎች በተኙ ጊዜ ሶላትን ማብዛት፣

°

አልይን ረ.ዐ በተራው ጠየቁት "አንተስ ያአልይ ?"

"በዱኒያ ላይ 3ነገሮችን እወዳለሁ:-

1.እንግዳን ማክበር፣

2.በሙቀት ወቅት ፆምን መፆም፣

3.ጠላቴን በሰይፍ መቅላት፣

°

አባ ዘርን ረ.ዐ በተራው ጠየቁት "አንተስ ያአባ ዘር?"

"በዱኒያ ላይ 3 ነገሮችን እወዳለሁ :-

1.እርሃብን እወዳለሁ፣

2.በሽታን እወዳለሁ፣

3.ሞትን እወዳለሁ፣

ነብዩም ﷺ "ያ አባ ዘር ለምን እነዚህን ወደድክ?"

አቡዘር መለሰ "ረሃብን ወደድኩት ቀልቤን ፈሪ ሊያደርግልኝ ዘንድ፣

በሽታን ወደድኩት ወንጀሌን ሊያቀልልኝ ዘንድ፣

ሞትን ወደድኩት ከጌታየ ጋር ሊያገናኜኝ ዘንድ።" ብሎ መለሰ።

°

ነብዩ ﷺ " እኔም በዱኒያ ላይ

3 ነገሮችን እወዳለሁ:-

1.ሽቶን እወዳለሁ፣

2.ሚስቶቼን እወዳለሁ፣

3.የአይኔ ማረፊያ ሶላቴን እወዳለሁ፣

በዚህ መካከል ድንገት ጅብሪል አ.ሰ.ወ ዱብ አለ ሰላምታ ካወረደ በኋላ እንዲህ አለ

"አንቱ የአላህ መልዕክተኛ ﷺ በዱኒያ ላይ እኔም 3 ነገሮችን እወዳለሁ

ነብዩም ﷺ "ምንድናቸው ያ ጀብሪል?" ብለው ጠየቁት።

1.መልዕክትን ማድረስ፣

2. አማናን አደራን መጠበቅ፣

3.ሚስኪኖችን መውደድ፣

ጅብሪል አ.ሰ.ወ ተመልሶ ወደ ከሄደ በኋላ ረሱልና ﷺ ሱሃቦቻቸው ረዲየሏሁ አጅመኢን ከመቀመጫቸው ሳይነሱ

ተመልሶ መጣና አሁንም ሰላምታውን አቅርቦ:-

"አላህም ሱ.ወ. ሰላም ብሏችኋል ካለ በኋላ አላህም ሱ.ወ እንዲህ ብሏል:-

በዱኒያ ላይ 3 ነገሮችን እወዳለሁ:-

1.አላህን አውሺ የሆነችን ምላስ፣

2.አላህን ፈሪ የሆነችን ቀልብ፣

3.መከራ የበዛበት ታጋሽ የሆነችን ጀሰድ።

አላህ ሱ.ወ ታጋሾች አድርጎ ነብዩና ﷺ ሱሃቦች ረ.ዐ.አ የወደዱትን ያስወድደን!

°

ይህን ጣፋጭ ሐዲስ በማንበባችሁ ከፍ ያለ አጅር ታገኛላችሁ -ኢንሻ አሏህ።

ሼር በማድረግ ለሌሎች ብታካፍሉ ግን እነሱ ባነበቡት ልክ ለናንተም ሀሰናት ይፃፍላችኋል!

ኢንሻ አሏህ!!

አላህ አንብበው ከመጠቀሙት ያድርገን!!!

Send as a message
Share on my page
Share in the group
nesri  
8 month Translate
Translation is not possible.

#share#share please

የእስራኤል ጦር በጋዛ የመሬት ኦፕሬሽን ላይ የጦር ወንጀል እየፈፀመ ነው። ሂትለር ያደረጋቸውን በትክክል እየፈጸሙ ነው። እባካችሁ በዚህ ኡማ ፔጅ ላይ በፊት ሼር በማድረግ ለማህበረሰቡ በማዳረስ ምድራዊ ግፋቸዉን እናጋልጥ። ፈስ ቡክ ላይ ግን አትሞክሩት ሸር አድርገ በደቂቃዎች ዉስቸጥ አዉርዶ አካዉንተንም ዘግተዉብኛልና አሁን።

5 views
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

እጅግ ልብ የሚነካ ታሪክ

▰▰▰✿▰▰▰

አንድ ሰአለባህ ኢብን፣አቢ- አብድረህማን የሚባል የ16 ዓመት

ልጅ ነበር። ይህ ታዳጊ ወደ አኪራ በሄደ ጊዜ የእሱን ጀናዛ

ለማጀብ መላኢካዎች ወርደዋል፣ክስተቱ እጅግ ልብ

ይነካል፣በትእግስት ያንብቡት ታሪኩ እንዲህ ነው....

አንድ ቀን ረሱል ( ሰ.0.ወ) ይህ ሰአለባህ ኢብን፣አቢ-

አብድረህማን የተባለውን የ 16 አመት ልጅ፣ወደ አንድ ቦታ

ይልኩታል።በጉዞ ላይ ሳለ መንገድ ላይ በድንገት አንዲት ሴት በሯን

ከፍታ ገላዋን ስትታጠብ ይመለከታታል።አይኑ ባሳየው ነገር

ተፀፀተ

:

ይህ ልጅ አስቦበት ሳይሆን ንፋሱ መጋረጃውን ሲከፍተው በድንገት

ነበር ያያት።እናም ይህ ልጅ በጣም ደነገጠ። እንዲህም አለ ረሱል

(ሰ.0.ወ) ልከውኝ እንዴት እንደዚህ አይነት ነገር እመለከታለው?

በማለት እራሱን ወቀሰ።

ታድያ ይህን ሀራም ነገር አይቼ እንዴት ብዬ ነው ረሱልን

(ሰ.0.ወ ) የማየው ? አይሄንም ሀራም ባየሁበት አይኔማ ረሱልን

አላይም ብሎ የተላከውን ሳይመልስ በዛወ ይጠፋል።ሳይመለስ

ቀረ፣ ረሱል ( ሰ.0.ወ ) የዚህ ልጅ መጥፋት አሳሰባቸውና ሁለት

ሰሀቦችን እንዲፈልጉት ይልካሉ።

ሰሀቦቹም መዲና ድረስ ሄደው ፈልገው ሊያገኙት አልቻሉም

ለረሱል

( ሰ.0.ወ ) ልጁን እንዳጡት ይነግሯቸዋል።

ረሱል ( ሰ.0.ወ ) ጉዳዩ እጅጉን ስላሳበቸው ለሁለተኛ ጊዜ

ሌሎች ሰሀቦችን አክለው አሁንም፣ ደግመው ልጁን እንዲፈልጉት

ይልኳቸዋል። ሰሀቦችም እሱን ፍለጋ ዞረው፣ ዞረው መጨረሻ ላይ

አንድ ገበሬ ዘንድ ይደርሳሉ። ገበሬው ገና ሲያያቸው እርዳታ ፈላጊ

መሆናቸውን ሲያውቅ ምን ልርዳቹ በማለት ጠይቆ

ያስተናግዳቸዋል።

እነሱም እንዲህ አይነት ልጅ አይተሀል? ብለው በዙ

የሚያውቁበትን ምልክት ይነግሩታል። ምልክቱን ሲነግሩት፣

ሰወየው ልጁን ወዲያው አወቀው፣

:

ከዚያም ይህ ልጅ እኮ እዛጋ የምታዩት ተራራ ላይ ነው የሚኖረው፣

ምን እንደነካው እንጃ ሁል ጊዜ ያለቅሳል ፣እያለቀሰ

( አስተግፊሩሏህ ) እያለ ጌታውን ምህረት ይጠይቃል፣

( አስተግፊሩሏህ) ሲል ነው የሚውለው፣ ልጁ ከማንም

አይገናኝም መሸት ሲል ማታ አካባቢ እኛ ጋር እየመጣ፣ ወተት

ይጠይቀናል

:

ከዚያም ወተቷን ፊት፣ለፊቱ ያስቀምጣትና እንባውን ወተቷ ላይ

እያፈሰሰ ያቺን ፣ወተት ጠጥቶ ይሄዳል ። በተረፈ ከማንምጋ

አይገናኝም በማለት የልጁን ሁኔታ በሀዘን ነገራቸው።

:

ሰሀቦች ተገረሙ የተባሉትንም በመስማት የሚመጣበትን ሰዓት

እንጠብቅና ሲመጣ ረሱል ( ሰ.0.ወ ) ዘንድ ይዘነው እንሄዳለን

ተባባሉ ፣እናም ቀኑ መሸ እና ልጁ በተባለበት ሰዓት ላይ ወተት

ሊጠይቅ ሲመጣ ሰሀቦቹ ያገኙታል ፣ልጁ ሲበዛ ከስቷል፣ በሀዘን

ምክንያት ተጎሳቁሏል በጣም አዘኑ

:

ልጁንም ያዙትና ወደ ረሱል (ሰ.0.ወ ) ዘንድ ሊወስዱት

እንደሚፈልጉ ሲነግሩት ፍቃደኛ አልሆነም፣ መሄድ እንደማይችል

በጣም አጥብቆ ነገራቸው፣ በደከመ ጉልበቱ ከእጃቸው

ሊያመልጥም ፈለገ ። ነገር ግን ጉልበት እንደሌለው ስላወቁ

በግድ፣ ተሸክመው ወደ ረሱል ( ሰ.0.ወ ) ዘንድ ወሰዱት።

እርሳቸው ዘንድም ደረሱ ፣ረሱልም ( ሰ.0.ወ ) ና- እስቲ ብለው

ጭንቅላቱን ታፋቸው ላይ ሊያስተኙት ሲሉ፣ ጭንቅላቱን ከታፋቸው

ላይ በማንሳት ( ያረሱለላህ ) ይህ የኔ ጭንቅላት በጣም ብዙ

ወንጀል ተሸክሟል ስለዚህ የርስዎ የተከበረ አካል ላይ አታስተኙኝ

በሎ ገሰጻቸው

:

ልጁ ረሱል (ሰ.0.ወ)-ጋ በደረሰ ጊዜ ከመክሳቱ የተነሳ በጣም

ጎስቁሎ የሞት ጥላ በእሱ ላይ አጥልቶ ጣረ ሞት ላይ ነበር።እናም

አይኑ ድንገት ባየው ነገር ተፀፅቶ በተራራ ጫፍ ላይ ቁጭ ብሎ

እያለቀሰ (አስተገፊሩላህ) እያለ የጌታውን ምህረት እየጠቀ ቆይቶ

በመጨረሻም

ሸሀዳ ይዞ በረሱል ( ሰ.0.ወ ) እጅ ላይ ሞተ (ወደ አኪራ ሄደ) ።

ከዚያም ጀናዛው ታጥቦ ወደ ቀብር መሄድ ጀመረ፣ ጀናዛውን

ተሸክመው በሚሄዱበት ሰዓት የረሱል ( ሰ.0.ወ ) አረማመድ

ይለይ ነበር። ረሱል (ሰ.0.ወ) በእግር ጣቶቻቸው ይራመዳሉ።

ሰሀቦችም ረሱል (ሰ.ዓ.ወ) መንገድ የተጣበበባቸው መስሏቸው

ሰዎችን እየገፈታተሩ፣ መንገድ ይከፍቱላቸዋል።ነገር ግን አሁንም

ረሱል (ሰ.0.ወ) እንደመጀመሪያው ነበር በጣታቸው የሚጓዙት

ሰሀቦች በርሳቸው አረማመድ ግራ፣ተጋቡ ፣ተገረሙ እንዲህም ሲሉ

ጠየቋቸው ?

ያ-ረሱለላህ ( አንቱ የአላህ መልእክተኛ ሆይ )ምነው መንገዱ

ክፍት ሆኖ ሳለ ለምን በእግር ጣቶቾዎ ይራመዳሉ አሏቸው

ረሱልም እንዲህ በማለት መለሱላቸዋል።

የ(ሰዕለባህ ኢብን፣ አቢ-አብድረህማን)-ን ጀናዛ ለማጀብ የመጡ

መላኢካዎች ፣ብታዩዋቸው ኖሮ፣ከብዛታቸው የተነሳ አንድ እግር

እንኳን ለማስቀመጥ የሚመች ቦታ አታገኙም ነበር ብለው

ነገሯቸው።

የዚህን ታዳጊ ምርጥ የአላህ ባርያ ታሪክ ወደውታል ?

ታሪኩ ለአሁኑ ትውልድ፣ ይሆናል ያስተምራል ብለው ካመኑ፣

እርሶዎጋ ብቻ እንዳይቀር ሼር በማድረግ ለወዳጅ ዘመዶዎ ያካፍሉ

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

10 views
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

ያ ኡመተል ኢስላም ኢላ አርዲል ሀበሽ! እስከመቼ ነው በ እንደዚህ አይነት መዋረድን ምትዋረዱት? እስከመቼ ነው በኩፍ ጣጉት መከተል ምተከተሉት? እስከመቼ ነው ተዋርዳችሁ ዲናችሁን ምታዋርዱት? ምንድነው ምንጠብቀው በሀቅ መንገድ ላይ መሆናችንን ትጠራጠራላችሁ? ወይስ ከሰማይ የሚወርድ ዋህይ ትጠብቃላችሁ? ዋህዩም ተቋርጡዋል ቁርአኑም ተሟልቱዋል ሀዲሱም ተከትቡዋል መንገዱም ቀን በብርሃን ከሚበራው ብርሃን በላይ በድቅድቅ ጨለማ ያበራል ይህ መንገድ የነብያት መንገድ ነው የሞቱለት የገደሉበት የበላይነትን ያስከበሩበት መንገድ ታድያ ወደየት እንሸሻለን? ጣጉትን ማንገስ ኩፋርን መከተል አይበቃንም? የአላህን ትዕዛዝ አማና ጥሰን እፊቱ ስንቆም ምንድነው ምላሻችን? አሊሙም ዳኢውም ጃሂሉም ዝምታው ምንድነው በዚሁ ቢያጠፋን አይችልም ከነ ግሳንግሳችን? ዋ ሙስሊሞች የማመንን ገመድ እንያዝ ጂሀድን እንውጣ እሱን የተውን ቀን ነው ውርደታችን የጀመረው ሙስሊም ዱኛ ላይ ሁለት ምርጫ ድል ወይም ሹሀዳእነትን ጂሀድን እየሞትን እናስወበዋለን እንጂ እየፈራን አንሸሸውም ይህ ነው የአቂዳ ጎዞ። ቁርአኑን ያህዲ ወሰይፉን የንሱር ነው ዲነል ኢስላም። ነብሱይ ለአላህ ሱብሀነሁ ወተአላ እሚያበድር ማን ነው ክፍያው የብድሩ ምላሽ ጀነት ቃል ተግብተዋል እዛ ነው ክፍያው።

Send as a message
Share on my page
Share in the group