UMMA TOKEN INVESTOR

About me

🌿عش ما شئت فإنك ميت ،وأحبب من شئت فإنك مفارقه

7 month Translate
Translation is not possible.

አሰላሙ አለይኩም ወረህሠቱሏሂ ወበረኪቱሁ

ረሱላችን (ሷለሏሁ አለይሂ ወሰለም )እንዳሉት

ከሰው ሁሉ በላጩ ቁርኣንን የቀራ ነው አሉ

ስለዝህ በየቤታቹ በዬተኛውም አለም ሆናቹ

በ ኦንላይን(Online) ቁርኣን መቅራት ለምትፈልጉ እህቶች

👉ለአዲስ ጀማሪ

👉 ቃእደቱ ኑራንያ

👉 ቁርኣን ተጅዊድ

👉ለተጅዊድ

👉ቁርኣን ነዝር

ምትፈልጉ ደውሉልኝ ብውስጥ አውሩኝ

@bintmohammeddd

👉ዱንያ ጠፊ ናት በግዜያቹ ተጠቀሙ

ባረከሏሁ ፊኩም

ለመደወል

0982107490

0944287414

Send as a message
Share on my page
Share in the group
7 month Translate
Translation is not possible.

#እህቴ ኑሮሽን ከሰው ኑሮ ጋር አታወዳድሪ!!መረጋጋትን ታጫለሽና..

አታይኝም እኔን እህትሽን ኢሰላሚክ ወይን ብለው 30ሺ አውጥተው ሲገዙ አየሁ ለፕሮግራማቸው እኔም ለምን ይቅርብኝ ብዬ 30ብሬን አውጥቼ የራት ፕሮግራሜን በወይኑ ፈታ በኮካ አስውቤዋለሁ!! ኸላስ

ምን ልልሽ ነው እህቴ የጓደኛዬ ባል ለሚስቱ ይሄን አደረገ ጎረቤት ቤታቼው ከኔ እጥፍ ያማረ ነው,, እያልሽ ኑሮሽን ከሰው ጋር እያወዳደርሽ ሰላምሸን አትጪ.. በአለሽ ነገር ተብቃቅተሽ ኑሪ ለቤቱ ለልጆቹ ደፋ ቀና የሚለውን ባልሽን ድካም ተረጂ ..ሁሌ ስታማሪ መስማቱ ለሱም ሰላም አይሰጠውም ትዳርሽም እድሜው ሊያጥር ይችላል .... እናም ብልህ ነው መሆን ያለብን

በመጅሊሳቼው ቤታቸውን ፏ አድርገው አየተን ከሆነ

እኛ በፍራሻችን ቤታችን ፏ አድርገን ማሰዋብ

45ሺ ብር የተገዛ ምጣፋቸውን አይተን ከሆነ ...የላስቲኩም ምጣፍ ይሁን ውልውል አድርገን አፅድተን ፍርሸርሸ ማድረግ ....እኛም ሌሎቹ የሚያገኙትን ደስታ እናገኛለን ብቻ ባለን ነገር በተሰጠን ስጦታ እንብቃቃ ብቻ!!

አላህዬ በሰው ሀያት ቀንተው የሞቀ ቤታቸውን ከሚያፈርሱት አያድርገን !!

Send as a message
Share on my page
Share in the group
7 month Translate
Translation is not possible.

የአል-ቀሳም ብርጌድ ቃል አቀባይ ከመሸ እንደገለፀው

"ባህር ሰርጓጅ ወታደሮቻችን ከአስቀላን በስተደቡብ ወደምትገኘው ወደ ዚኪም የባህር ዳርቻ ሰርጎ መግባት ችሏል።

እንቁራሪት የሚል ስያሜ የተሰጣቸው የባህር ኃይላችን አሁን ከአስቀላን በስተደቡብ በምትገኘው ዚኪም ከተማ ከወራሪዋ ጦር ጋር ፊት ለፊት እየተፋለመ ይገኛል"

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
7 month Translate
Translation is not possible.

መዋጋት በእጅ ሀይል እንደሚከናወን ሁሉ በዱዓ ሀይልም እንዲሁ ይከናወናል።

ሚንሃጁ አስ ሱናህ ( 4/482)

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
7 month Translate
Translation is not possible.

☞ከሚስት ተለይቶ መኖር ያለዉ ተጽዕኖ..

=>አንድ ምሽት ዑመር (ረ.ዐ)እንደልማዳቸዉ በመዲና ጎዳናዎች እየተዘዋወሩ የህዝቡን ደህንነት  በሚከታተሉበት ጊዜ ከአንድ ቤት ዉስጥ የሴት ድምጽ ሰሙ።ሁኔታዉን ረጋ ብለዉ ሲከታተሉ ቀጣዮቹ ስንኞች ከጆሮአቸዉ ገቡ:

"

   አቤት መርዘሙ ሌሊቱ፣

   የጥቁር ጃኖ ጽልመቱ፣

    ፍቅረኛ የሌለኝ ብቸኛ፣

    የሚያጫዉተኝ ጓደኛ፣

     እንቅልፌ ጠፋ በነነ፣

   በናፍቆት መገላበጥ ሆነ፣

    አላህን ባላፍር ባልፈራ፣

     ፍራሼ ጦሙን ባለደር፣

      ስንት ተአምር በሰራ፣

📌እነዚህን ስንኞች በጠፍ ጨረቃ የደረደረችዉ ወይዘሮ ባሏ ለጅሃድ በመዉጣቱ ምክንያት ረዥም ጊዜ ስለተለያት የብቸኝነት ስሜት ክፋኛ ተጫጭኗት ቆየ።የወሲብ ስሜቷ ክፋኛ  ይፈታተናት ገባ በሌላ በኩል ደግሞ አላህን ፈሪ በመሆኗ በህገ-ወጥ መንገድ ይህን ፍላጎት ማስተናገድ እንደማትችል ታዉቃለች።እናም ቢያንስ ስሜቷን በስንኞቿ ገለጸች ኡመሩል ፋሩቅም (ረ.ዐ)ሰሙ ከዚያም ወደ ልጃቸዉ ሃፍሳ (ረ.ዐ)ሄደዉ አንድ ሴት ከባሏ ተለይታ ለምን ያህል ጊዜ መቆየት እንደምትችል ጠየቋት ለአምስት ወይም ለስድስት ወራት  የሚል መልስ  አገኙ ስለሆነም በየግዛቱ  ለሚገኙ ጦር አዛዦች ሁሉ  ተዋጊዎቻቸዉ ከ"6 ወራት በላይ በአዉድ  ውጊያ እንዳይቆዩ ትዕዛዝ አስተላለፉ።የሴትየዋም ባል እንዲመጣ ተላከበት።

"

🖋ባል በሚስቱ ላይ ያሉት መብቶች..

💠ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ)እንዲህ ይላሉ አንድ ሰዉ ለሌላዉ ሰዉ እንዲሰግዱ ቢፈቀድ ኖሮ ሚስቶች ለባሎቻቸዉ እንዲሰግዱ አዝ ነበር።(ቲርሚዚ) ያለረሱ ምንም ማድረግ የማትችል ሆና እያለ ባሏን ወደ ማታመሰግን ሴት አላህ አያይም (ይቆጣበታል)>{አን_ነሳኢ) ሶስት ሰዎችን አላህ ሶላታቸዉን የማይቀበላቸዉ ሲሆን መልካም ስራቸዉም ወደ ሰማይ አይወጣም እነርሱም የኮበለለ ባሪያ ወደ ጌታዉ(አሳዳሪዊ)እስኪመለስና እርሱን ማገልገል እስኪቀጥል ድረስ ባሏ የተቆጣባት ሴት ድረስ እስኪደሰትባትና ሰካራም ስካሩ እስኪበርድለት ድረስ(ኢብን ሂብባን)

"

♻️የሁሴን ኢብን ሙህሰን አክስት ባሏን በነቢዩ(ሰዐ.ወ)አጠገብ አወሳች። እርሳቸዉም ባሎቻችሁን በተመለከተ ራሳቸሁን መርምሩ እነርሱ ጀነታችሁም ጀሃነማችሁም ናችዉና አሉ (አህመድና _አል ሃኪም)

"

   ✍የሱና አጽዋማትን በተመለከተ የሴቶች መብት "በሚል ይቀጥላል...

 

     📚ምንጭ~ ዉድ ስጦታ ለሙሽሮች ከሚለው መፅሃፍ.።

Send as a message
Share on my page
Share in the group