UMMA TOKEN INVESTOR

Translation is not possible.

🔴የእስራኤል ወዳጅ አገራት (የሙስሊም ጠላት አገራት) የሆኑት አውሮፓውያንና መሰሎቹ እንኳ እስራኤልን እየተቃወሙ ነው። እስራኤል በሞራልም በፖለቲካውም ትልቅ ኪሳራ ውስጥ ትገኛለች‼

🛑የአውሮፓ ህብረት የውጭ ፖሊሲ ኮሚሽነር፡- አፋጣኝ፣ ጊዜያዊ እና ባለ ብዙ ወገን የተኩስ ማቆም እንዲደረግ እና ለጋዛ የሰብአዊ ኮሪደሮች እንዲከፈቱ እንፈልጋለን።

🛑የኖርዌይ ጠቅላይ ሚኒስትር፡- በጋዛ ሰርጥ ላይ የተደረገውን ከበባ እናወግዛለ፣ ሆስፒታሎች ከጦርነት መሸሸጊያ መሆን አለባቸው እንጂ ኢላማ መሆን የለባቸውም፡፡

🛑የስኮትላንድ ጠቅላይ ሚኒስትር፡- በጋዛ ለሚገኙ ህፃናት ጊዜያዊ መረጋጋት ብቻ ሳይሆን አፋጣኝ የተኩስ ማቆምም ያስፈልጋቸዋል።

🛑የቤልጂየም የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፡- በጋዛ ውስጥ የተካሄደውን ወንጅል ለመመርመር እና ተመሳሳይ ወንጀሎችን በቀጣይ ለመከላከል የዓለም አቀፉን የወንጀለኞች ፍርድ ቤት ሥራ እንደግፋለን።

#ተጨማሪ

🛑ሃማስ፡ የአውሮፓ ህብረት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ባለስልጣን ጆሴፕ ቦሬል ሃማስ ሆስፒታሎችንና ሲቪሎችን እንደ ጦር ምሽግ እየተጠቀመ ነው በሚል መናገራቸው  ወራሪዋን የውሸት ትርክት በማቅረብ እውነታውን ለማዛባት  ያደረጉትን ሙከራ አጥብቀን እንቃወማለን እናወግዛለን።

🛑ይህ አስተያየት በህጻናትና መከላከያ በሌላቸው ሰላማዊ ዜጎች ላይ ተጨማሪ እልቂትን እንድትፈፅም ለወራሪዋ ሽፋን እንድመስጠት እንቆጥረዋለን፣ እናም ቦሬል እነዚያን አሳፋሪ እና ኢሰብአዊ መግለጫዎች በአስቸኳይ እንዲያስተካል እንጠይቃለን።

🛑የእስራኤሉ ሃሬትዝ ጋዜጣ እንደዘገበው:–

"ኔታንያሁ ከአሜሪካን ሚዲያ ጋር ያደረገው ቃለ ምልልስ እንደሚያሳየው የኔታንያሁ አመራርና ጠንካራ የስራ ባህሪው ተበታትንኖ/ተኖ አሁን በብድር የሚንቀሳቀስ አንካሳ ዳክዬ ሆኗል" ሲል ዘግቧል። 🔥🔥🔥

መረጃው ለሌሎችም እንድደርስ ሸር ያድርጉት🙏

© Nejashi Media – ነጃሺ ሚዲያ

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

የተባረከው የፍልስጤም ምድር

ክፍል 5

✳️✳️✳️✳️✳️✳️✳️✳️✳️✳️✳️✳️✳️✳️✳️✳️✳️✳️✳️✳️✳️✳️

ፍልስጤሞች ከ20ኛው ክፍለ-ዘመን ጀምሮ ህልውናቸውን ሊያስክድ የመጣባቸውን ባዕድ ኃይል በከፍተኛ አልበገር ባይነት የህይወት መስዋዕትነት እየከፈሉ በሳዑዲና በግብፅ የሚገኙ አንቱ የተሰኙ ሙፍቲ ዑለማኦች ሳይቀሩ ለምን ምድሩን ጥላችሁላቸው አትሰደዱም የሚል ወኔ ሰላቢ ምክር እየለገሷቸውም እንኳ እጅ አልሰጡም፡፡

የመከላከሉ ጦርነት አጀማመርና ሂደት እንደ አንድ ተጨቋኝ ህዝብ ትግል የተለያዩ መርሐላዎችን አልፏል

በ1918 አንድ የአርበኞች ኮሚቴ የፍልስጤም ሹርጣ አባላትን በማካተት በሕቡዕ ተቋቋመ፡፡ ይህ ኮሚቴ ለዐረብ አብዮት መሠረት በመጣልና በምሥራቅ ኦርዶን በሚኖሩ ዐረቦች ዘንድ የጽዮናዊያንን ሤራ በማጋለጥና ንቃተ-ህሊና በመፍጠር የላቀ ሚና ተጫውቷል፡፡ ኮሚቴው በመሪዎቹና በአስተባባሪዎቹ ላይ በደረሰው እስራትና ማሳደድ የተነሣ ሊዳከም ቢችልም ብሶት እያባባሰው የመጣው የፍልስጤም መነሳሳት ግን እየቀጠለ የጃፋና የቡራቅ አብዮት ን ወለደ፡፡ ምንም እንኳ ባደረጃጀት ያልተሟሉና ግብታዊ የነበሩ ቢሆንም ትግሉን በማቀጣጠልና የጽዮናዊያን መሠሪ እቅድ ባንዴ ፍጻሜ እንዳያገኝ በማጓተት የጎላ ድርሻ ነበራቸው፡፡

የፍልስጤም ታጋዮች ተጨማሪ ኃይል ማደራጀት ቀጠሉ፡፡ ከነዚህ መሀል በኢዘዲን አልቀሳም የተደራጀው በዋናነት ይጠቀሳል፡፡ ኢዘዲን አልቀሳም ማነው? እሱ ከሶሪያ ወደ ፍልስጤም በመምጣት የዲን ኡስታዝ ሆኖ የራሱን የትግል እንቅስቃሴ የጀመረ ሰው ነው፡፡ በ1926 አንድ የንቅናቄ ኮሚቴ ውስጥ በአባልነት ይመዘገባል፡፡ በ1928 የንቅናቄውን የሐይፋ ቅርንጫፍ ይመሰርታል፡፡ ቀጥሎም የዚሁ ቅርንጫፍ መሪ ይሆናል፡፡ በ1930 የንቅናቄው የአስተዳደር ኮሚቴ አባል በመሆን የመሪነቱን ቦታ ይጨብጣል፡፡

ከዚህ በኋላ አልቀሳም የመንግሥት ሠራተኛ በመምሰል በብዙ የፍልስጥኤም ክልሎች እየተዘዋወረ በአምስት አምስት አባላት የተደራጁ ህዋሳትን በስፋት አዋቀረ፡፡ ኢስላማዊ ህግጋት የትግሉ መመሪያ መሆን እንዳለባቸው አስተማረ፡፡ ብቸኛው የነፃነት መንገድም ጂሃድ ፊ ሠቢሊላህ መሆኑን አሠመረበት፡፡ አፅንዖት አደረገበት፡፡

ይህ በኢዘዲን አልቀሳም የተደረጃ የህቡዕ ንቅናቄ በዐይነቱ ለየት ያለና በዐረብ ፍልስጤሞች የትግል ታሪክ ውስጥ ትልቁ የመስዋዕትነት ንቅናቄ እንደሆነም ይታመናል፡፡ ማዘዣ ቢሮዎቹ ደሃው ህዝብ በሚበዛበት የኢያሪኮ ከተማ ነበር፡፡ በአካባቢው ላይ ሰፊ ተቀባይነት እያገኘ ሲመጣ አደረጃጀቱን አሰፋው፡፡ የደዕዋና የአህዝቦት፣ የወታደራዊ ሥልጠና፣ የአቅርቦት፣ የኤሌክትሮኒክስና የውጭ ግንኙነት አካላትን በመፍጠር አቋሙን ይበልጥ አጠናከረ፡፡

በ1935 ኢዘዲን አልቀሳም የአብዮቱን መጀመር ይፋ አደረገ፡፡ ይህም የሆነው ሠላማዊ መፍትሄ የማፈላለጉ ጥረት ለተደጋጋሚ ጊዜ ተሞክሮ ያለውጤት መቅረቱ እውን ከሆነ በኋላ ነው፡፡ የአብዮቱን መጀመር ተከትሎ በቀሳም ታጣቂዎችና በእንግሊዝ ጦር መካከል ተከታታይ ግጭቶች ተካሄዱ፡፡ ብዙ ፍልሚያዎች ተደረጉ፡፡ ኋላ አልቀሳም ማፈግፈግ ግድ ሆነበት፡፡ ከተወሰኑ የጦር ጓዶቹ ጋር አንድ ቦታ ላይ ከበባ ተደረገበት፡፡ እጁን በሰላም እንዲሰጥ ተጠየቀ፡፡ አልፈቀደም፡፡ በተከተለው የተኩስ ልውውጥ ዐቅጣጫዋ በውል ያልተለየ ጥይት አገኘችው፡፡ ተገደለ፡፡ በተቀሩት ጓዶቹና በእንግሊዝ ጦር መካከል የከረረ ውጊያ ተካሂዶ የሞቱት ሞተው የተቀሩት ጠላት እጅ ወደቁ፡፡

ይቀጥላል……

መረጃው ሌሎች ጋር እንድደርስ ሸር ማድረጋችሁን አትርሱ።

💯ተጨማሪ መረጃ እንድደርስዎ ቻናላችንን Join በማድረግ ይቀላቀሉ

👇👇👇

ቴሌግራም:–

https://t.me/Brathersmedia

👇👇👇

ኡማ ላይፍ:–

https://ummalife.com/Brathersmedia

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

ሙጃሂዶቻችን ዕንቅልፍ አጥተው ፈጠው ሲያነጉ እያንቀላፋችሁ ማደር ግን እንዴት አስቻላችሁ?! አንደበቶቻችሁ አላህን ከመለመን ስለምን ይለጎማል?! እንዴትስ ይሰለቻል?! እንዴት ያ አላህ ማለት አቃታችሁን?

ያ አላህ ባሮችህ ናቸውና ረዳትና ደጋፊ ሁናቸው በሉ።

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

አላህ ዘንድ የምትመሰክር ጣት። አላህ አላህ እያለች ጌታዋን የተገናኘች። እርሱን በመናፈቅ የተቀሰረች። አዎ  በሸሐዳ እየመሰከረች ሩሑ ከጀሰዱ ተለየች።

"በርሱ መንገድ እስከሆነ አካልላችን ይቆረጥ። ደማችንም ይፍሰስ እንደ ጅረት። ልጆቻችን ይሰው። ኃብታችን ፊዳ ይሁን። ብቻ ግን ጌታችን ከእኛ ይውደድ። እንቅልፍ ከዓይናችን ቢጠፋም፣ ጠመንጃውን እንደታቀፍን ብንተኛም፣ አንጀታችን ታጥፎ ቢራብም አላህ ከወደደን ከቶ እኛን አይከፋንም"

ስለነርሱ ለመፃፍ ቃላት እንኳ ይሸሻል። መዳፌ ላይ እየተንተባተበ እዚህም እዚያም ይወድቃል። ብቻ ግን ባላችሁበት ሰላምታዬ ይድረሳችሁ።

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

የተባረከው የፍልስጤም ምድር 

               ክፍል   4

✳️✳️✳️✳️✳️✳️✳️✳️✳️✳️✳️✳️✳️✳️✳️✳️✳️✳️✳️✳️✳️✳️

    እንግዲህ!

  የእንግሊዝና የአይሁድ ጽዮናዊያን ሤራ ከ20ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ጀምሮ ሲውጠነጠን እንደነበረ ግልጽ ነው፡፡ በመሠረቱ የፍልስጤም መከራና ሥቃይ የተጠነሰሰው መላውን ሙስሊም ዓለም በሥሩ ሲያስተዳድር የነበረው የቱርክ ዑስማንያ ኢስላማዊ መንግሥት በምዕራባዊያን እጅ ሲሸነፍና ጨርሶም በ1924 እንዲያበቃለት ሲደረግ ነው፡፡ የውድቀቱ ቀጥተኛ ውጤት ሆነና ባንድ መንግሥት ጥላ ሥር ተማክሎ ይኖር የነበረው ሙስሊሙ ዓለም ዛሬ በሚታየው መልኩ በምዕራባዊያን እቅድና ፍላጎት የተከፋፈለ ጭፍራ ሆነ፡፡ እያንዳንዱ ራሱን ’ነፃ መንግሥት´ እያለ አወጀ፡፡ 

     ምዕራባዊያን ይሄን ነገር እንደምን አሳኩት? 

  ኢስላማዊውን መንግሥት ለመከፋፈል የተጠቀሙበት ዘዴ የቱርክና የዐረብ ብሔርተኛ ስሜትን በመጫር ነበር፡፡ በኢስላም መለኮታዊ ዓርማ “ላ ኢላሀ ኢልለላህ ሙሐመዱን ረሡሉልላህ” በሚለው ሥር ወንድማማች ሁኖ ባንድ ዱንያዊና ዲናዊ ዓላማና ግብ ተሳስሮ የኖረውን ህዝብ ገዢና ተገዢ አድርገው በመሳል አቃቃሩት፡፡ ቱርኮችን እንደገዢ፡፡ ዐረቦቹን እንደ ተገዢ፡፡ በዚህም ዐረቦች ከቱርክ ነፃ መውጣት አለባችሁ ተባሉ፡፡ እነሱም በየፊናቸው የተነገራቸውን ተቀብለው ዐረብ ብሔረተኝነትን በማራገብ ተጠመዱ፡፡ ያቺ የታሪካቸውና የሃይማኖታቸው ሞገስ የሆነችው ፍልስጤም ክብሯን ስትገፈፍና በባዕዳን ስትመዘበር እነሱ የእንግሊዝ መንግሥት በሰጣቸው የቤት ሥራ ተጠምደው አይሰሙም አይለሙም፡፡

  የነቢያት አገር ቤት፣ የኢስራእ ወል ሚዕራጅ ጉዞ መነሻ፣ አቅሷ የኸሊል ምድር፣ የስንት ሙጃሂዶች ደም የፈሰሰባት ቅድስት ሀገር ከሐዲያን ሲያረክሷት ዐረቦች እዚያው ግድም ሆነው አንድ ነገር ማድረግ አልቻሉም፡፡ ክብርና ሞገሳቸው ከነበረው ኢስላማዊ አንድነት ይልቅ እስከዛሬ ተዋራጅ ሆነው ያሉበት ብሔራዊ ልዩነት ይሻለናል በሚል የዘቀጠ እምነት ጎራ ለዩ፡፡ ወደ ፍልስጤም ዞረው ለማየትና ተቃውሞ ለማደራጀት ጊዜ አልነበራቸውም፡፡ ለዘላለም ከክብር ሰገነት የወረዱበት ጎሠኛ ስሜት ዛሬ ወደሚገኙበት የውርደት አዘቅት እያንደረደራቸው ምንም ቢባሉ የሚያዳምጡ አልነበሩም፡፡

ኢራቅ፣ ሶሪያ፣ ግብጽ፣ ሳዑድ ዐረቢያ … ተብለው እንደተለያየ አገር መታወጅን ቀዳሚ አጀንዳ አድርገው መሽቀዳደም ይዘዋል፡፡ ምዕራባዊያን ውጥናቸው በዐረቦች እጅ ሲፈፀም እያዩ ባደባባይ ይስቃሉ፡፡ ዛሂድ ዑለሞች ተደብቀው ያለቅሳሉ፡፡ 

    ፍልስጤም የዐረብ ወገኖቻቸውን እገዛ በመሻትም ጭምር አገራቸው የታላቁ ሶሪያ (ቢላዱ ሻም) አንድ አካል መሆኗን አበክረው ለማስረዳት ቢሞክሩም ለነሱ የተደገሠላቸው ሌላ ነገር ስለነበረ ሰሚ አላገኙም፡፡ እንደሌሎቹ ሁሉ ለነሱም አገራዊ ነፃነት እንዲከበርላቸው ቢጠይቁም አልተደመጡም፡፡ እነሱ እስከመኖራቸውም እውቅና ሊሰጣቸው አልተፈለገም፡፡ በነሱ ላይ የአይሁድ አገር ቤት ተመሥርቶ እንደ መንግሥት እንዲታወቅ ነበር የተፈለገው፡፡ “የምን ፍልስጤም ብሎ ሀገር” ሌሎቹ ዐረብ አገራት በመሬታቸው ላይ የአይሁድ ሠፋሪ ሳይኖርባቸው ብሔራዊ ተብዬውን ነፃነት ሲሰጡ ፍልስጤም ግን ባዕድ ሠፋሪም ሠፍሮባት ብሔራዊ ተብዬውን የይስሙላ ነፃነትም ተነፍጋ ህልውናዋን ለማስቀጠል ትታገል ጀመር...

               ይቀጥላል……

መረጃው ሌሎች ጋር እንድደርስ ሸር ማድረጋችሁን አትርሱ።

💯ተጨማሪ መረጃ እንድደርስዎ ቻናላችንን Join በማድረግ ይቀላቀሉ

👇👇👇

ቴሌግራም:–

https://t.me/Brathersmedia

👇👇👇

ኡማ ላይፍ:–

https://ummalife.com/Brathersmedia

Send as a message
Share on my page
Share in the group