UMMA TOKEN INVESTOR

Translation is not possible.
🔴ከአረብ ሃገር የምትመጡ በተለይ አዲስ አበባ ላይ ተጠንቀቁ ኤርፖርት ላይ ተጠንቀቁ!!
ለራሳችሁ ስትሉ ልብ ግዙ…🙏🙏🙏
⚠️የዛሬውን የሿሿ መረጃ ተመልከቱ🙊🙊
           
⭕️ከአረብ ሀገር የመጣችን ኢትዮጵያዊ ዘርፈዋት ያመለጡ ወንጀለኞች በቁጥጥር ስር ውለዋል !
⭕️ተሽከርካሪ ተጠቅመው የሿሿ የተባለ የታክሲ ላይ የዘረፋ ወንጀል የፈፀሙ አራት ተጠርጣሪዎችን ከነ-ኤግዚብቱ በቁጥጥር ሥር ማዋሉን የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ገለፀ
⭕️ተሽከርካሪ ተጠቅመው የሿሿ የተባለ የታክሲ ላይ የዘረፋ ወንጀል የፈፀሙ አራት ተጠርጣሪዎችን ከነ-ኤግዚብቱ በቁጥጥር ሥር ማዋሉን የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ገለጿል።
⭕️ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ሥር ሊውሉ የቻሉት በቤይሩት ሀገር ስትሠራ ቆይታ ወደ ሀገራችን በመመለስ ላይ ያለች የግል ተበዳይ ወ/ሪት በላይነሽ በዶሬ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ስትደርስ የራይድ ታክሲ አገልግሎት ሰጭ በመምሰል ኮድ 2- አ.አ ታርጋ ቁጥር B 96905 በሆነ ኮሮላ መኪና አሳፍረው ከቦሌ ወጡ።
⭕️ከዚያም ትንሽ አንደሄዱ ትራፊክ መጣብን እንዳንያዝ እዚህ ጋ ውረጂና ማዶ ተሻግረሽ ትሳፈሪያለሽ እንጠብቅሻለን በማለት ተበዳይ ስትወርድ ሻንጣዎቿን ጭነው ''ሿሿ"" የታክሲ ላይ የዘረፋ ወንጀል ፈፅመው  ሲያመልጡ አንድ ጉዳዩን በአይነ ቁራኛ ሲከታተል የነበር እግረኛ የመኪናውን ሰሌዳ ፎቶግራፍ አንስቶ ለኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ትራፊክ ቁጥጥርና አደጋ ምርመራ አመራርና አባላት ፖሊስ ይሰጣል።
⭕️የትራፊክ ፖሊሶችም የደረሳቸውን መረጃ መሠረት በማድረግ ተጠርጣሪዎቹን በጂፒኤስ በመከታተል አራቱንም ተጠርጣሪዎች ልደታ አካበቢ በቁጥጥር ሥር አውለዋል።
⭕️በተጨማሪም ተጠርጣሪዎቹና በተሽከርካሪ ላይ በተደረገው ፍተሻ ከተለያዩ ግለሰቦች የሰረቋቸው ሰባት ተች እስክሪን የሞባይል ስልኮችን፣ ሁለት በተን ስልክ እና ከተለያዩ ግለሰቦች የተሰረቁ  84,485 ብር፣ አምስት ባለ አምስት መቶ ሪያል  ፣አንድ የባለ ሁለት መቶ ሪያል፣ ሦስት ባለ አስር ሪያል ኖት፣ ሁለት ባለ አምስት ሪያል መያዙን ኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አስታውቋል።
⭕️የግል ተበዳይ ወ/ሪት በላይነሽ በዶሬ ንብረታቸውን ተረክበው በሰላም ወደ ቤተሰቦቿ እንዲሄዱ አድርጓል ፖሊስ።
⭕️ፖሊስና ኅብረተሰቡ በዚህ መልኩ ተባብረው ከሠሩ በየትኛውም የሀገራችን አካባቢ ሊፈጠር የሚችል የወንጀል ተግባር አስቀድሞ ለመከላከል እና ለመቆጣጠር እንደሚቻል ይህ ጥሩ ማሳያ ነው ብሏል ፖሊስ።
⭕️የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ትራፊክ ፖሊሶችም  በኤግዚብትነት የተያዙ ንብረቶች እና ተጠርጣሪዎችን ለቦሌ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ለሀርቡ ፖሊስ ጣቢያ አስረክበዋል።
📣መረጃውን ለሌሎች ሸር አድርጉላቸው!!
የቴሌግራም ቻናላችንን ተቀላቀሉ: https://t.me/IbnuibrahimOfficial
image
image
image
image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.
አንድ የመኪና አምራች ካምፓኒ የተለያዩ የመኪና ሞዴሎቹ ላይ እንደየምርት አመታቸው የተለያዩ ፊቸሮችን ይገጥማል ።የተለያዩ ማንዋሎችንም ያዘጋጃል።ማንም ሰው ተነስቶ ለምን ተለያዩ? ሁሉም ሞዴል እኩል ናቸው!  ወይም ሁሉንም በአንድ መመሪያ አሽከረክራለሁ ወዘተ ብሎ  የሚቃወም ሰው የለም።
ለምን? ከተባለ መብት ስለሌለው። በመኪናዎቹ ላይ ብቸኛ መብት ያለው አምራቻቸው ነው።የራሱ ምክንያትና ጥበብ አለው። ለአእምሮ ቀረብ ለማድረግ እንጅ ለአላህ የላቀ ምሳሌ አለው! 
አላህ የፍጡራኑ ሁሉ ፈጣሪና መራጭ ነው። ከየፍጡራኑ ሁለት አይነት ፆታ ሲፈጥር የሚገባውን መብትና ግዴታም አስቀምጧል። ስለ አፈጣጠራችን ጥበብ ብቸኛ እውቀት ያለው እርሱ ስለሆነ ወንድ ምን መብት ምን ግዴታ ሴት ምን መብት ምን ግዴታ እንዳላቸው ደንግጓል። ከዚያ በኋላ  ማንም ተነስቶ የፆታ እኩልነት ብሎ መስበክ አይችልም።አላህ ፆታዎችን እኩል አላደረገምና። በኢስላም ወደ ፆታ እኩልነት መጣራትም ክህ  ደት ነው።
ለምሳሌ ሴትን ልጅ የቤት አስተዳዳሪነትን ግዴታ አልጫነባትም። ወንዱ ላይ ደግሞ ሰርቶ ለፍቶ ቤቱን እንዲያስተዳድር ዋጂብ አድርጎበታል።ሴቷን ደግሞ ቤቷ ቁጭ ብላ እንድትኻደም ወሰነላት። ቀበሮዎቹ ታዲያ ቤቷ ቁጭ ብላ በባሏ መኻደሟን ተመቀኙና ነይ ውጪ ከወንድ ጋር እኩል ነሽ ብለው ጠሯት። ስለ ፌሚኒዝም እያወጋን ነው ...
የቴሌግራም ቻናል 👉https://t.me/IbnuibrahimOfficial
image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.
⭕️'ሁለተኛ ሚስትህ ለመሆን ዝግጁ ነኝ .. ነገር ግን አንድ መስፈርት አለኝ' አለችዉ።
⭕️እሷን ለማግባት ፍላጎት ስላለዉ መስፈርቷን መስማት ፈለገ። 'መስፈርትሽ ምንድን ነዉ?' ብሎ ጠየቃት።
⭕️'ከመጀመሪያ ሚስትህ የፈለከዉን አመት ደብቀኝ ነገር ግን ቤተሰቦችህንና ጓደኞችህን እንድታስተዋዉቀኝ እፈልጋለሁ።' አለችዉ።
⭕️የሚፈራዉ ሚስቱን እንጂ ሌላዉን ማስተዋወቁ ችግሩ አልታየዉም። በሀሳቧ ተስማምቶ አገባት። ቤተሰቦቹንና ጓደኞቹን አስተዋወቃት። እሷ ግን እናቱንና አባቱን፤ ጓደኞቹንም ጭምር በጣም ቀረበቻቸዉ። ቤቷ ትጋብዛቸዋለች፤ ወደቤታቸዉ ስጦታ ይዛ ትሄዳለች። በጣም ተዛመደቻቸዉ።
⭕️ባልም በሄደበት ሁሉ 'ሚስትህስ ሁለተኛዋ' እያሉ ያሞግሷት ጀመር። አንዴ አንዱ ጓደኛዉ 'ሚስት ገና አሁን አገባህ!' አለዉ። በሌላ ጊዜ ቤተሰቦቹን ዘያራ በሄደበት አባቱ 'አንደኛ መሆን የነበረባትን ሁለተኛ አደረካት?' ብለሸ ወቀሳ ነገር ጣል አደረገበት።
⭕️ባልም በተደጋጋሚ ያስብ ጀመር። 'ደስታዬ ያለዉ ከማን ጋር ነዉ?' ብሎ ራሱን ጠየቀ። ሁለተኛዋ በለጠችበት። በልቡ ዉስጥም አንደኛ አድርጎ አነገሳት።
⭕️ምን ለማለት መሰላችሁ 😁
ሴቶች ሁለተኛ ስትጠየቁ እምቢ አትበሉ፤ ይልቅ ብልህ ሁኑ ¡ (ሁለተኛም ሆኖ አንደኛ መሆን ይቻላል 😜)
🛑ሊንኩን በመጫን ቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ጣፋጭ ትምርት ያገኙበታል👇👇👇https://t.me/IbnuibrahimOfficial
Telegram: View @IbnuibrahimOfficial

Telegram: View @IbnuibrahimOfficial

«The time must change in Islam. But We do not update Islam.»
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.
⭕️ፖለቲከኞች የምርጫ ቅስቀሳ ሲያደርጉ የማይገቡት የውሸት ቃል የለም! ምኞት በየአይነቱ ይደረድራሉ፡ ከፈለጉም ወንዝ በሌለበት ቦታ ድልድይ እንሰራለን ይላሉ።
⭕️ልክ እንደዚሁ በሀራም አንዲትን ሴት ማጥመድ የፈለገ ተልካሻና ወሮበላ ወንድ ለልጅቷ የተስፋ ቃል ይደረድርላታል፡ መላኢካ መስሎ ልነጠፍልሽ ይላታል።
⭕️ጉዳዩን ከጨረሰ በኋላ ግን ወደ ጭራቅነት ተቀይሮ፡ በሀራሙ አጥቦና ጨምቆ ያነጥፋታል።
⛔️ከዛማ ተረኛዋን የማጥመድ ስራ ይጀምራል!
⭕️ውዷ እህቴ! ከአጅነብይ ወንድ ጋር መጨባበጥ፡ ካፌ ለካፌ መዟዟር በስልክ መጀናጀን፡... የጀመርሽ ቀን ያንቺ ጉዳይ ጠልሽቷል፡ የጌታሽና የመልዕክተኛውን ትዕዛዝ ጥሰሻል።
⛔️ጅማሬው አበላሽተሽ ጥሩ ፍፃሜን አትጠብቂ!
⭕️አንተስ ሰው መሳይ በሸንጎ፡ እንደው አሏህን ካልፈራህ፡ እህት እንኳ የለህም? በሴትስ አልተወለድክም?
⭕️አንተ የምታደርገው ነገር በእህትህ፡ በሴት ልጅህ ቢሆን ትወዳለህን?
⭕️አስተውሉ! ጌታችን አሏህ ዝሙትን አትፈፅሙ አይደለም ያለው፡ ይልቁንስ አትቅረቡ ነው ያለውና ርቀታችንን እንጠብቅ!
image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.
🔴ከጎረቤታችን የኬንያ ሙስሊሞች ምን እንማራለን…?
🟰🟰🟰🟰🟰🟰🟰🟰🟰🟰🟰🟰🟰🟰
♣️ እንደ ኬንያ ማእከላዊ ስታትስቲክስ መረጃ የኬንያ ሙስሊሞች ከአጠቃላይ የሀገሪቱ ህዝብ 11 % ያክል ይሸፍናሉ። ያ ማለት 5 ሚሊዮን አካባቢ ይሆናሉ ማለት ነው። ያ ማለት የሶማሌ ሙስሊሞች ከኬንያ አጠቃላይ የሙስሊሞች ብዛት ይበልጣል ማለት ነው ። INSAMER የተሰኘ ተቋም ይፋ ባደረገው አሃዝ ደግሞ የኬንያ ሙስሊሞች ከአጠቃላይ የሀገሪቱ ህዝብ ከ 25-30% ይሸፍናሉ። ያ ማለት ከ 12 - 14ሚሊዮን ህዝብ ማለት ነው።
በከፍተኛው አሃዝ ወስደን ብናሰላው እንኳ የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ብዛት ከኬንያ ሙስሊሞች በ 5 እጥፍ ገደማ ይልቃል!
ነገር ግን
♣️ የኬንያ ሙስሊሞች ሁለት ታላላቅ አለምአቀፍ ኢስላማዊ ዩኒቨርስቲዎች አሏቸው ። RAF international universty እና Umma University የሚባሉ ሁለት ግዙፍ ዩኒቨርስቲዎች እና የምርምር ማእከሎች! ነገር ግን ከ 50 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑት የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ምንም አይነት ዩኒቨርስቲም ሆነ ዪኒቨርስቲ ኮሌጆች የላቸውም!
♣️ የኬንያ ሙስሊሞች በርካታ የመጀመሪያ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እንድሁም ኮሌጆች ሲኖሯቸው የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ግን ያሏቸው በጣት የሚቆጠሩ የኢለመንታሪ ትምህርት ቤቶች ብቻ ነው ።
♣️ የኬንያ ሙስሊሞች በፖለቲካ ተሳትፏቸውም ከኢትዮጵያዊያን በጣም የተሻለ ነው ። ከየትኛውም ማህበረሰቦች በላይ የኬንያ ሙስሊሞች በጣም ጠንካራ በጣምም ተፅእኖ ፈጣሪዎች ናቸው ። 222 መቀመጫ ካለው የኬንያ ፓርላማ 32 ቱ ሙስሊሞች ናቸው። ሚስሊሞች በኬንያ በጣም ስትራቴጂካዊ አካባቢዎችን የያዙ ሲሆን እነ ሞንባሳ ፣ ላሙ ወዘተ በመሳሰሉ የወደብ ከተሞች ላይ የሚኖሩት በአብዛኛው ሙስሊሞች እንደመሆናቸው በሀገሪቱ ፖለቲኮ-ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ያላቸው ተፅእኖ ከፍተኛ ነው።
♣️ የኬንያ ሙስሊሞች ራሳቸውን በከፍተኛ ልእልና ነው የሚያዩት ። በኬኒያዊያን ዘንድ ሙስሊምነት ማለት ስልጡንነት አዋቂነት እና በማህበራዊ አስተሳሰብ ላቅ ማለት ነው ። ራሳቸውንም የኬንያ ባለቤት አድርገው ነው የሚያዩት ። በርካታ የታሪክ አሻራዎችና ረጅም ዘመን የመሪነት ታሪክም አላቸው ። ኬንያዊያን ሙስሊሞች አለምአቀፋዊ ንቃተ ህሊናቸውም በጣም ከፍ ያለ ነው።
♣️ ኬኒያዊያን ሙስሊሞች ከራሳቸው አልፈው ስለመላው ሙስሊሞች ሁኔታ የሚያጠና የሚከታተል ታላቅ የሚዲያ ተቋም አላቸው ። የሚዲያ ግሩፑም ISLAM AND MEDIA WORKING GROUP ( #iamcr ) ይሰኛል። ይህ ድርጅት በአለም አቀፍ ደረጃ በመላው ሙስሊሞች ላይ ትኩረቱን አድርጎ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ሁኔታዎችን ይከታተላል ፣ ጥልቅ ምርምሮችን ያደርጋል የመፍትሔ አቅጣጫዎችንም ያስቀምጣል። ይህ ተቋም በተለያዩ የሙስሊሙ አለም ክፍሎች የሚገኙ ምሁራንን ስለ ኢስላማዊ አለም የሚዲያ እና ግንኙነት እንቅስቃሴ በአንድ በመሰባሰብ እንዲያጠኑና የመፍትሔ አቅጣጫ እንዲያስቀምጡ በከፍተኛ ሁኔታ ያበረታታል። በአንፃሩ የኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች አንድም ጠንካራ ሚዲያ (Mainstream media ) የላቸውም ። ይህ አሳፋሪ ነው።
♣️ ኬንያዊያን በአንድ ጥላ ስር የሚያሰባስባቸው ፤ ፊርቃና መዝሃብ ሳይለይ እንደ ጃንጥላ ከለላ የሚሆናቸው የእስልምና ተቋም አላቸው ። ለኬንያዊያኑ ስድብ አይሁንብኝና እኛ መጅሊስ እንደምንለው ማለት ነው ። ያ የሀይማኖታቸው ከፍተኛ ተቋም Supreme council pf Kenya Muslims ( #supkem ) ይሰኛል። ይህ የሃይማኖት ተቋም በኬንያ ሙስሊሞች ከፍተኛው የስልጣን ባለቤት ነው ። ከፈትዋ ጀምሮ የተለያዩ ሀይማኖታዊ እንቅስቃሴዎችን ከፖለቲካዊ እስከ ኢኮኖሚያዊ ከዚያም እስከ ማህበራዊ ዘርፎች የሙስሊሞችን እጣፈንታ ይወስናል። የራሱ ፍርድ ቤት አለው ። አንድ ሰው ሙስሊም እስከሆነ ድረስ ጉዳዩ የሚታየው በሼሪአ ፍርድ ቤት በኩል ነው ።
ዋና ቃዲና የኢስላማዊው ካውንስል ፕሬዝዳንት ስልጣናቸው ከሙስሊሞችም ይሻገራል ። የሙስሊሞች ካውንስል ፕሬዝዳንቱ የኬንያን ፕሬዝዳንት የማማከር ስልጣንም አላቸው ወይም የኬንያ ፕሬዝዳንት አማካሪ ናቸው ።
♣️ በዚህም የኬንያ መንግስት ከሙስሊሞች ጋር ሊኖረው የሚገባውን ግንኙነት ያማክራሉ ፤ የሙስሊሞችን ጥያቄ ፍላጎት ለመሪው በቀጥታ ይነግራሉ በአጠቃላይ እጅግ ከፍተኛ ስልጣን አላቸው።
image
Send as a message
Share on my page
Share in the group