Translation is not possible.

Follow & Share → Umma ሚዲያ

↓↓↓↓↓

Umma ሚዲያ

ከነቢ ሰዐወ ህልፈት በኋላ ሰሃባዎች ወደ ተለያዩ የአለማችን

ክፍሎች ተበትነው ዘመቻ ላይ ናቸው።

ሳዕድ ኢብኑ አቢ ወቃስ ረዐ በታዘዘው መሰረት ሰራዊቱን ይዞ

ከፐርሺያ ምድር ተከስቷል። ያ በዐረብያ ምድር ያለ ስልጣኔ የኖረ

ማህበረሰብ ትልቁን የስልጣኔ መገለጫ የሆነውን ፐርሺያን በጦር

ሊገጥም አኮብኩቧል።

የፐርሺያው ስረወ መንግስት እልፍ አዕላፍ የሆነ የሰራዊት ማዐት

አሰልፎ ቁጥራቸው እና ትጥቃቸው እዚህ ግባ ከማይባሉ

ሰሓባዎች ጋር ሊፋለም ድንኳናቸውን ተክለው ማዶ ለማዶ

ይተያያሉ።

በዚህ መሃል የሰሓባዎቹ የጦር አዛዥ የሆነው ሳዕድ ከሰራዊቱ 7

ወጣቶችን መልምሎ የፐርሺያ ሰራዊቶችን ሁኔታ እንዲያጣሩ እና

ከቻሉም አንድ የፐርሺያ ወታደር ጠልፈው እንዲመጡ ላካቸው።

7 ሁነው ጉዞ ጀመሩ። ትንሽ እንደተጓዙም በርከት ያለ ቁጥር

ያላቸው የፐርሺያ ወታደሮችን ከርቀት ሲመጡ ተመለከቱ'ና

መቋቋም ስለማይችሉ ለመመለስ ወሰኑ።

ግና ከመካከላቸው በሀሳባቸው ሳይስማማ ቀርቶ አንደኛው

«የታዘዝኩትን ሳልፈፅም አልመለስም» በማለት ተልዕኮውን

ለማሳካት ጎዞውን ቀጠለ። 6ቱ ትተው ተመለሱ።

ጉዞውን በእርጋታ እና በመጠንቀቅ ቀጠለ። ሰራዊቱን በውሃ

ድልድዮች ተደብቆ ከተሻገረ በኋላ ማንም በማያውቀው ሁኔታ

ከ40,000 ሰራዊት እንብርት ላይ ተከሰተ።

ከሰራዊቱ መሀል ላይ ቁሞ ሩቅ እያማተረ ሲመለከት ከርቀት ነጭ

ድንኳን እና ከደጁ የቆመ የንጉሳን ፈረሰ ከአይኑ ገባ።

«ይህ የጦር አዛዣቸው የሩስቱም ድንኳን መሆን አለበት» ብሎ ወደ

ድንኳኑ ተጠግቶ ሌሊቱ ፅልመቱን ለምድር እስኪያልብስ እዝያው

ቁጭ አለ።

ፀሀይ ጠልቃ ምድር በፅልመት ስትወረር፣ ሰራዊቱ ከብርዱ

ጭጋግ ሽሽት ከየድንኳኖቻቸው ሲወሸቁ፤ ወጣቱ ሰይፉን

ከማንገቻው መዝዞ ወደ አዛዡ ድንኳን አመራ።

ከድንኳኑ ደጅ ሲደርስም የድንኳኑን ማዋቀርያ ገመዶች በሰይፉ

ቆራርጦ ሙሉ ድንኳኑ በአዳሪያኑ ላይ ሲወድቅ እሱ ደጅ ላይ

የታሰረውን ፈረስ ፈትቶ ጎዞውን ቀጠለ።

ፈጣን ፈረሰኞች ኮቴውን ተከትለው ያሯርጡት ጀመር፤ ከፈረስ

ጀርባ ያደገው የዐረብያ ብላቴናውም አሸዋውን እያቦነነ ከፊታቸው

ይከንፋል።

በመጨረሻም ከሁሉም ርቆ ሶስት ፈረሰኞች ብቻ ሲያሯርጡ

ደረሱበት። ከሶስቱ ፈረሰኞች የግድ አንዱን ይዞ ወደ አሚሩ መሄድ

ስለሚጠበቅበት ሊያጃጅላቸው ፈልጎ ሲደርሱበት እያመለጣቸው፤

በጣም ሲራራቁ እየጠበቃቸው ከክልላቸው አስወጣቸው።

ከዝያም ዞሮ ሰይፍ ተማዘዛቸው፤ ብዙም ሳይቆይ ሁለቱን ገድሎ

አንዱን አስሮ ይዞት ከፊት ከፊት እየነዳው ጉዞ ወደ አሚሩ ጀመረ።

ልክ የሙስሊሞችን ሰራዊት ደርሶ ምርኮኛውን ከአሚሩ ፊት

ሲያቆመው ምርኮኛው ለአሚሩ፦ «ከለላህን ስጠኝ እኔም

ዕውነታውን ላውራ» አለው።

«እኛ የዕውነት ህዝቦች ነን፤ ከላላችንን የምንሰጥህ እማትዋሸን

እንደሆን ነው» አለው አሚሩ።

ንግግሩን ቀጠለ፦ «እስቲ ስለ ፐርሺያ ሰራዊቶች ንገረኝ»

ምርኮኛው፦ «ስለ ፐርሺያ ሰራዊት ስብጥር ከመናገሬ በፊት ስለ

ጀግናው ጓድህ ላውጋህ።

ከልጅነቴ አንስቶ የጦርነት ሜዳ ላይ ነው ያደግኩት እንዲህ አይነት

ሰው አይቼም አላውቅም። ሁለት ጠንካራ የሰራዊት ቡድኖችን

አልፎ በመግባት የአዛዣችንን ድንኳን ቆራርጦ ጣለ'ና ፈረሱን ይዞ

ጋለበ።

ለ3 ሁነን እስከ መጨረሻ ተከታተልነው። ከፈረሱ ወርዶ

ተፋለመን'ና የ1000 ፈረሰኛ ግምት የምንሰጠውን ጀግናችንን

ገደለው።

ሁለተኛውንም የጦር መኳንንት በ1000 የምንገምተው ሲሆን

እሱንም እያየሁ ገደለው። ሁለቱም ያጎቶቼ ልጆች ነበሩ።

ይህ ድርጊቱ እልህ በልቤ ቋጥሬ ልገድለው ባለ በሌለ ጉልበቴ

እንዳሯሩጠው አስገደደኝ። የኔ አይነት ጉልበታም ከወታደሩ ይኖራል

ብዬ ባልገምትም ባላሰብኩት መልኩ የዚህ ልጅ ምርኮኛ ሆኜ

መጣሁ።

የዚህ አይነት ጀግና አንድ ካላችሁ መቼም አትሸነፉም» አላቸው።

በመጨረሻም እስልምናን ተቀበለ።

የሙስሊሞቹ ወታደሮችም ምድር አንቀጥቃጭ የሆነ ጦርነት

አድርገው ፐርሺያን ሙሉ በሙሉ ደምስሰው ድልን ተቀዳጁ።

ያ ጀግናው ሰሓቢይም ስሙ ጡለይሃ ቢን ኩወይሊድ ዱንያ

እስካለች ድረስ ሲወሳ ይኖራል።

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group