UMMA TOKEN INVESTOR

About me

#الحمدلله

ummadawud shared a
Translation is not possible.

እደለኛ ሰው ማለት.....!👌

በሌሊቱ ወቅት የሱረቱል በቀራን የመጨረሻ ሁለት አንቀጾች ያነበበ ሰው በአላህ ፍቃድ ሌሊቱን ከመጥፎ ነገር ሁሉ እንደሚጠበቅ ተረድቶ ሲያበቃ አንቀፆቹን አዘወትሮ ያነበባቸው ሰው ነው።

እደለኛ ሰው ማለት.....!👌

ፈርድ የሆኑ ስላቶችን ከሰገደ በኋላ አያተል ኩርሲይን ካነበበ ጀነትን መግባት ሞት እንጂ ምንም እንደ ማይከለክለው ተረድቶ አዘወትሮ አያተል ኩርሲይን ያነበበ ሰው ነው።

እደለኛ ሰው ማለት.....!👌

ከመተኛቱ በፊት አያተል ኩርሲይን ያነበበ ሰው ለሊቱን ሙሉ እስኪያነጋ ከአላህ የተመደበ ጠባቂ እንደሚጠብቀውና ሸይጣንም እንደማይቀርበው አውቆ ከመተኛቱ በፊት አያተል ኩርሲይን አዘወትሮ ያነበበ ሰው ነው።

እደለኛ ሰው ማለት.....!👌

ሱረቱል ኢኽላስን ሶስት ጊዜ ማንበብ ሙሉ ቁርዓንን ከማኽተም ጋር እንደሚስተካከል ተረድቶ ይህችን ሱራ አብዝቶ ያነበበ ሰው ነው።

እደለኛ ሰው ማለት.....!👌

ለሴትና ለወንድ አማኞች ሁሉ ዱዓዕ ያደረገ ሰው በአያንዳንዱ አማኝ አላህ ዘንድ አጅር እንደሚመዘገብለት ተረድቶ ለሙዕሚኖች ሁሉ አብዝቶ ዱዓዕ ያደረገ ሰው ነው።

እደለኛ ሰው ማለት.....!👌

ሱብሃነሏህ

ወል ሀምዱ ሊላህ

ወላ ኢላሃ ኢለሏህ

ወሏሁ አክበር

ማለት ፀሀይ ከወጣችበት ሁሉ የተሻለና የበለጠ መሆኑን ተረድቶ እነዚህን ውድ ቃላት አብዝቶና ደጋግሞ ያላቸው ሰው ነው።

እደለኛ ሰው ማለት.....!👌

ይህንን ካወቀ በኋላ የሰራበትና ሌሌሎችም እንዲያውቁና እንዲተገብሩ በማሰታወስና በማካፈል የአጅሩ ተካፋይ የሆነ ሰው ነው።

Send as a message
Share on my page
Share in the group
ummadawud shared a
Translation is not possible.

ወላሂ አንብቡና ሼር አርጉ 👌

ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ተናገሩ"አንድ ሰው በሞተ ጊዜ ዘመዶቹ በቀብር ሥነስርአቱ ላይ ሲጨናነቁ አንድ እጅግ ያማረ ቆንጆ ሰው በጭንቅላቱ በኩል ይቆማል።ጀናዛውም እንደተከፈነ ያ ሰው በከፈኑ እና በሞተው ሰው ደረት መሀል ይሆናል።ከቀብር ሥነስርአቱም በህዋላ ቀባሪ ቤተሰቦቹ ወደ ቤት ሲመለሱ ሁለት ሙንከር እና ነኪር የተባሉ ምላኢኮች ወደ ቀብሩ በመምጣት ጀናዛውንና ያንን ቆንጆ ሰው በመለያየት ያንን የሞተውን ሰው በእምነቱ ጉዳይ ብቻውን በጥያቄ ሊያፋጡት ይሞክራሉ ። ሆኖም ያ ቆንጆ ሰው ይናገራል "ይህ ሰው አጋሬም ጋደኛዬም ነው ብቻውንም ልተወው አልችልም። እናንተ እንድትጠይቁት ከተመደባቹ ስራችሁን መሥራት ትችላላቹ እኔ ግን ወደ ጀነት መግባቱን ሳላረጋግጥ ትቼው እልሄድም"። ከዝያም ወደ ሞተው አጋሩ በመዞር እንዲህ ይለዋል "እኔ አንዳንዴ ድምፅህን ከፍ አርገህ ሌላ ጊዜ ደግሞ ቀስ ብለህ ስታነበኝ የነበርኩት ቁርአን ነኝ ምንም አትጨነቅ፤ ከሙንከርና ነኪር ጥያቄና መልስ በኃላ ምንም ጭንቀት አይኖርብህም"፤ጥያቄና መልሱም ካለቀ በኃላ ያ ቆንጆ ሰው አል ማሉል አላ በተባሉ የጀነት መላኢኮች የተዘጋጀ በመልካም ሽታ የሚያውድ እና ከ ሀር በተሰራ ልብስ የተዘጋጀ አልጋ ያዘጋጅለታል።

2. ረሰል(ሶ.ዐ.ወ) እንደተናገሩት በቂያማ ቀን በአላህ ሱ.ወ ፊት ስንቆም ከቁርአን የበለጠ ለኛ ሚከራከርልን አይኖርም ከነብይያትም ከ መላኢኮችም በበለጠ።

3. እባክዎን ይህን መልእክት የቻሉትን ያህል ያስተላልፉ። ረሱል (ሶ.ዐ.ወ) እውቀትን ከኔ ለሌላው አስተላልፉ አንድም አረፍተ ነገር ብትሆን እንኩዋን ብለዋል።

4. ይህ መልእክት በ አላህ ፍቃድ በቀጣይ 7 ቀናት ቢያንስ 5 ሚልዬን ሰዎች እንዲዳረስ ዱአ እያደረግን ነው።

እባክዎን ይህን መልእክት ለ ቤተሰብዎ፣ ለዘመድዎትና ላሚያውቅዋቸው ሁሉ በማስተላለፍ ከተትረፈረፈው የአላህ ምንዳ ተጠቃሚ ይሁኑ።

*እርስዎ ቁርአንን ሲይዙ ሰይጣን ራሱን ያመዋል።

*ሲከፍቱት ይወድቃል።

*እያነበቡት ሲያይ ራሱን ይስታል።

*ይህንን መልእክት ሊያስተላልፉ ሲያስቡ ላማዳከምና ለማስነፍ ይሞክራል።

እኔ አሸነፍኩት ምክንያቱም ለእርስዎ መላክ ችያለሁ።

5. እባክዎን ሸይጣንን ያሸንፉና ይህንን መልዕክት ጠቃሚ ነው ብለው ካመኑበት ሼር!!

ለ አላህ ብላችሁ share አርጉ 🙏🙏

Send as a message
Share on my page
Share in the group
ummadawud shared a
Translation is not possible.

ጥበበኛው ሉቅማን ልጃቸውን ሲመክሩ እንዲህ ይላሉ ፦

" ከኢማን ቀጥሎ ልትደክምለት የሚገባው ትልቁ ነገር መልካም ጓደኛ ይሁን። መልካም ጓደኛ ምኗም እንደማይጣል መልካም ዛፍ ነው። በጥላው ትጠለላለህ። ከግንዱ ቤት ትሠራለህ። ከፍሬው ትመገባለህ።"

Send as a message
Share on my page
Share in the group
ummadawud shared a
Translation is not possible.

ሰውየው በአላህ ቅጣት እና በክስረት ውስጥ እየኖረ የደረሰበትን አደጋ ላያውቅ ይችላል።

ቅጣቱ ነፍሱን መርሳቱ ነው። ለነፍሱ የሚበጃትን አያውቅም። ነውሯን አያውቅም። እንዴት ከቆሻሻዋ ልትፀዳ እንደምትችል አይረዳም። በሚጎዱት ነገሮች ይጠመዳል። ለህይወቱ ከሚጠቅሙት ነገሮች ይርቃል።

:

አስተውል!

[وَلَا تَكُونُوا كَالَّذِينَ نَسُوا اللَّهَ فَأَنسَاهُمْ أَنفُسَهُمْ ۚ أُولَٰئِكَ هُمُ الْفَاسِقُونَ]

«እንደነዚያም አላህን እንደረሱትና ነፍሶቻቸውን እንዳስረሳቸው (ሰዎች) አትኹኑ፡፡ እነዚያ እነርሱ አመጸኞቹ ናቸው፡፡»

የጀመሩት እነርሱ ናቸው። አላህን ረሱ።

በውጤቱ አላህም ነፍሳቸውን እንዲረሱ አደረገ። የመድኅን መንገዳቸውን፣ የደስታውን ጎዳና ሸፈነባቸው።

(Tofik Bahiru)

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

🤲ya Allah برحمتك يا جبر

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group