UMMA TOKEN INVESTOR

anwar bilgu shared a
Translation is not possible.

🔹የአቡ ዑበይዳ መግለጫ ክፍል 1 ፡-

የአል አቅሳ ማዕበል ጦርነት ከተጀመረ 133 ቀናት አልፈዋል፣ የቀጠናውን ገፅታ የሚቀይር እና ከጥቅምት 7 ቀን 2023 ማለዳ ጀምሮ በዘመናዊው የሰው ልጅ ታሪክ ውስጥ ለረጂም ጊዜ የቆየውን የመጨረሻውን ቅኝ ግዛት መዳከም እና መጠናቀቅ መስክሯል።

ለአል-ቁድስ እና የአላህን መልእክተኛ መንገድን ለመደገፍ ስንል የጀመርነው የአል-አቅሳ ማዕበል በአላህ ፍቃድ አይቆምም እየጨመረ ቅርፅ እየያዘ ይሄዳል ኢ-ፍትሃዊነትን እና ጥቃትን ከአል-አቅሷ እና ከኢስራእ እና ሚዕራጅ ምድር በማስወገድ ለሀገራችን ህዝብ እና ለሙስሊሙ ታሪክ ትልቅ ለውጥ ይሆናል።

ልጆቹ አቅመ ደካሞችን በወንድነት ትምህርት የሚያስተምሩ ፣ሴቶቹ ወንዶችን የሚፈጥሩ ትውልድን የሚያፈሩ ፣ ተቃውሞው የዘመኑ የትግል ፣የጀግንነት እና የመስጠት ተምሳሌት የሆነውን ህዝብ እንዴት ያሸንፋሉ?

ተቃውሞው በልቡ ውስጥ የሚኖር ህዝብን፣ ተቃውሞው መከራውን፣ ስቃዩን እና ተስፋውን የሚካፈለው ህዝብን፣ የሚወዱትን በመስዋእትነት የከፈሉለትን፣ በአላህ መንገድ ላይ መሪዎችንና ወታደርን የሚያቀርቡለትን፣ የተቀደሱትን እና የተከበሩ ቦታዎቹን የሚከላከሉለትን እና ለጥያቄው የሚታገሉለትን ህዝብ እንዴት ያሸንፋሉ?

በአልቃሳም ብርጌድ ውስጥ ያሉ ተዋጊዎች እና የፍልስጤም ተቃውሞ አሁንም በዘመናችን ታሪክ በአሳዛኝነቱ፣ በአረመኔነቱ እና በአስጸያፊው የዘረኝነት አስተሳሰቡ ምንም ተወዳዳሪ የሌለውን ወንጀለኛውን የናዚ ጦር በመጋፈጣቸው በህዝባችን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅ ኪሳራ በጠላት ጦር ላይ እያደረሱ ነው።

የእኛ ተዋጊዎች የጠላት ተሸከርካሪዎችን እና የታጠቁ ተሽከርካሪዎችን እያወደሙ፣ በታንክ፣ በአውሮፕላኖች እና በጦር መርከቦች የታገዙ ጠላት ወታደሮችን አድፍጠው እያጠቁ፣ በፕሮፌሽናል ኦፕሬሺን መኮንኖቻቸውን በጥይት አልመው እየመቱ ወታደሮቻቸውን በባዶ ርቀት እየገደሉ ይገኛሉ፡፡

ጠላት እሳት በሆነችው ምድር ላይ ሰላም ነኝ ብሎ በሚያስብበት ጊዜ ሁሉ ታጋዮቻችን ጠላት ከማይጠብቀው ቦታ ተነስተው አላህ በሰጣቸው እርዳታ፣ ድጋፍ እና ስኬት እያጠቁ ነው፡፡

በአሁን ሰአት የሀገራችን ታጋዮች እና ተቃዋሚ ሃይሎች ከጠላት ጋር የሚያደርጉት ውጊያ በሁሉም ግንባሮች ቀጥሏል እና የጠላትን እብሪት፣ ትዕቢት እና አረመኔያዊ የናዚ ጥቃት በመጋፈጥ ዘመቻውን እየተጠናከረ ነው።

የአልቃሳም ብርጌድ ኦፕሬሺኖችን በየሰዓቱ ስናበስራችሁ በዝርዝር ልንገልጽ አንፈልግም ፣ እና ለአንዳንድ ተዋጊዎቻችን በውጊያ ተሳትፎ ውስጥ ያለው የውጊያ ሁኔታ የአንዳንድ ተልእኮዎችን ሪፖርት ያዘገያል፡፡ ነገር ግን ሪፖርቶችን እና ትዕይንቶችን የምናሰራጨው ታጋዮቻችን በግንባር ላይ የፈጸሙት እና እየፈጸሙ ያሉት አካል ነው። ለደህንነት ሲባል እና በውስብስብ የውጊያ ግንባር ሁኔታዎች አንዳንድ ኢፕሬሺኖችን ላለማሳወቅ እና አንዳንድ ትዕይንቶችን ላለማሰራጨት ወስነናል።

በሰሚን፣ በደቡብ እና ማዕከላዊ ጋዛ ሰርጥ የጽዮናውያን ሰርጎ ገቦች እና ወራሪዎችን በሁሉም አካባቢዎች ያሉ ተዋጊዎቻችን የጽዮናውያን ወረራ መጠንን መሰረት በማድረግ የተለያዩ ስልቶችን እና ዘመናዊ መሳሪያዎችን በመያዝ የጀግንነት ጦርነት እያካሄዱ መሆኑን እኛ የአልቃሳም ብርጌድ አባላት እናረጋግጣለን፡፡ በእያንዳንዱ ጥራት ያለው ዘመቻ ውስጥ ተገቢውን መሳሪያ እና የውጊያ ባህሪ ለመወሰን የመስክ ግምገማዎች በማድረግ በጠላት ሃይሎች መካከል የተረጋገጠ ኪሳራን ለማድረስ እየሰራን ነው፡፡

በሙስሊሙ ዓለም የተፈጠሩ ሁሉንም አዳዲስ መረጃዎች በተለይም በወቅታዊ የፍልስጤም ጉዳይ እውነተኛ እና ሚዛናዊ መረጃ ለማግኘት የሙሐመድ ትውልድ ገፅን ፎሎው ያድርጉ

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
anwar bilgu shared a
Translation is not possible.

🇵🇸🇪🇹 ጠቅላይ ሚኒስትር መሐመድ ሽታይህ ከአፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ ባደረጉት ንግግር:-

“እስራኤል” ጠቅላይ ሚኒስትሯ በስልጣን ላይ እንዲቆዩ እስከዚህ አመት መጨረሻ ድረስ ጦርነቱን መቀጠል ትፈልጋለች።

አጠቃላይ የሰፈራ ፕሮጀክቱ በአለም አቀፍ ማዕቀብ ስር መቀመጥ አለበት።

የአሜሪካ እና የአውሮፓ ሀገራት ሰፋሪዎችን በአሸባሪዎች ዝርዝር ውስጥ አስቀምጠዋል, ነገር ግን በጣም አስፈላጊው ነገር የሰፋሪዎቹን ምርቶች አለመጠቀም ነው።

- ወደ ጋዛ ውስጥ የሚገባው ዕርዳታ በጋዛ ካሉት ወገኖቻችን ከሚያስፈልገው 8% አይበልጥም።

- የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ከአሁን በኋላ አሜሪካን ወይም አውሮፓን አይሰሙም, "እስራኤልን" በፖለቲካ መግለጫዎች ቋንቋ ብቻ ሳይሆን በተግባር ቋንቋ ማነጋገር አለብን።

ለተጨማሪ 33 ዓመታት የሚቆይ ድርድር ውስጥ መመለስ አንችልም እና አለም በ 1967 ድንበር ላይ ለፍልስጤም ሀገረ መንግስትን እውቅና መስጠት ይጠበቅበታል።

ዛሬ እስራኤል ወንጀለኛ ሀገር መሆኗ በአለም እና በፍትህ ፍርድ ቤት ተረጋግጧል።

በሙስሊሙ ዓለም የተፈጠሩ ሁሉንም አዳዲስ መረጃዎች በተለይም በወቅታዊ የፍልስጤም ጉዳይ እውነተኛ እና ሚዛናዊ መረጃ ለማግኘት የሙሐመድ ትውልድ ገፅን ፎሎው ያድርጉ

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
anwar bilgu shared a
Translation is not possible.

የእስራኤል ብሄራዊ ደህንነት ሚኒስትር ኢታማር ቤን ጊቪር አለም አቀፉ የፍትህ ፍርድ ቤት በእስራኤል ላይ ተከታታይ አስቸኳይ እርምጃዎችን በመወሰን ብይን መስጠቱን ተከትሎ ፍርድ ቤቱን "ፀረ-ሴማዊ ነው" በማለት ፈርጇል።

ሚኒስትሩ የፍርድ ቤቱን ውሳኔዎች ችላ በማለት "የእስራኤልን ሀገር መንግስት ቀጣይ ህልውና አደጋ ላይ የሚጥሉ ውሳኔዎች መደመጥ የለባቸውም" ሲሉ አሳስቧል ።

በሙስሊሙ ዓለም የተፈጠሩ ሁሉንም አዳዲስ መረጃዎች በተለይም በወቅታዊ የፍልስጤም ጉዳይ እውነተኛ እና ሚዛናዊ መረጃ ለማግኘት የሙሐመድ ትውልድ ገፅን ፎሎው ያድርጉ

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
anwar bilgu shared a
Translation is not possible.

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ኔታንያሁ ዓለም አቀፉ የፍትህ ፍርድ ቤት እስራኤል ጦርነቱን እንድታቆም መወሰኑን ተከትሎ በሰጠው ምላሽ “በጋዛ ጦርነቱ ይቀጥላል” ብሏል።

በሙስሊሙ ዓለም የተፈጠሩ ሁሉንም አዳዲስ መረጃዎች በተለይም በወቅታዊ የፍልስጤም ጉዳይ እውነተኛ እና ሚዛናዊ መረጃ ለማግኘት የሙሐመድ ትውልድ ገፅን ፎሎው ያድርጉ

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
anwar bilgu shared a
Translation is not possible.

"የመን እና ፍልስጤም በጦር መሳሪያ ሳይሆን በፅናት በሀብት ሳይሆን በመስዋእትነት የትልቅነት ምሳሌዎች": ዛሬ በየመን ዋና ከተማ ሰነዓ ታላቅ ሰልፍ ተካሂዷል።

በሙስሊሙ ዓለም የተፈጠሩ ሁሉንም አዳዲስ መረጃዎች በተለይም በወቅታዊ የፍልስጤም ጉዳይ እውነተኛ እና ሚዛናዊ መረጃ ለማግኘት የሙሐመድ ትውልድ ገፅን ፎሎው ያድርጉ

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group