UMMA TOKEN INVESTOR

Tarjima qilib boʻlmadi.

وَلَا تَمْشِ فِى ٱلْأَرْضِ مَرَحًا ۖ إِنَّكَ لَن تَخْرِقَ ٱلْأَرْضَ وَلَن تَبْلُغَ ٱلْجِبَالَ طُولًۭا

Xabar sifatida yuborish
Sahifamda baham ko'rish
Guruhda ulashish
Tarjima qilib boʻlmadi.

ቁርኣን ለምንድን ነው ጠንካራ ማህበረሰብን ለመገንባት አይነተኛ መንገድ የሆነው?

ምክንያቱም ቁርኣን ለሚከተሉት ነገሮቻችን ገደብና ልክ አስቀምጦላቸዋልና

- ለድምፃችን : "و اغضُضْ مِن صوتِك".

- ለእርምጃችን : "و لا تَمشِ في الأرض مرحًا".

- ለእይታችን: "و لا تمدَّنَّّ عينَيك"

- ለመስሚያችን: "و لا تَجَسَّسُوا".

- ለምግባችን: "وكلوا و اشربوا ولا تُسْرفوا"

- ለንግግራችን : "و قُولُوا للناسِ حُسْناً".

- ለአቀማማጫችን: "ولا يغتب بعضكم بعضاً".

- ለነፍሳችን: "لا يسخر قومٌ من قومٍ".

- ለአስተሳሰባችን:  "إنَّ بعضَ الظنِّ إثمٌ"

- ይቅርታን አስተምሮናል: " فمن عفا و أصْلحَ فأجرُهُ على الله ".

ቁርኣን ህይወታችንን ስርአት የሚያስይዝና ስኬታማ ኑሮን የሚያረጋግጥልን መመሪያችን ነው።

" الذين آمنوا وتطمئن قلوبهم بذِكْرِ اللهِ ألا بذِكْرِ اللهِ تطمئنُّ القلوب".

💚 #ከቁርኣን_ጋር_እንተዋወቅ

Xabar sifatida yuborish
Sahifamda baham ko'rish
Guruhda ulashish
Tarjima qilib boʻlmadi.

☞☞ሀሰን  አል  በስሪ አላህ ይዘንላቸውና እንዲህ ይላሉ፦☜

ከሙእሚን ስነምግባር በላጩ  ለሰዎች ይቅር ማለት  ነው።

በርግጥ አላህ (سبحانه وتعالى) የሙእሚንን ባህሪ  እንዲ በማለት አውስቶታል፦

وَٱلْعَافِينَ عَنِ ٱلنَّاسِ ۗ

(ጀነት) ከሰዎችም ይቅርታ አድራጊዎች ለኾኑት (ተደግሳለች)፡፡

          [الزهد لأحمد (1680)]

ይቅር ባዮች ምንዳቸው አላህ ዘንድ ነው።  ይሄን ያክል ነው ተብሎ  በገደብ አልተገለፀም፦

فَمَنْ عَفَا وَأَصْلَحَ فَأَجْرُهُۥ عَلَى ٱللَّهِ ۚ

ይቅርም ያለና ያሳመረ ሰው ምንዳው በአላህ ላይ ነው፡፡ (ሹራ 40)

Xabar sifatida yuborish
Sahifamda baham ko'rish
Guruhda ulashish
Tarjima qilib boʻlmadi.

➧በቁርኣን ተጠቃሚ ለመሆን !

ቁርኣን ለሰው ልጆች መድህን ይሆን ዘንድ አላህ ከሰባት ሰማይ ከዐር በላይ በጅብሪል አማካኝነት በነብዩ - ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም - ላይ ያወረደው የሁለት ሀገር ስኬት የያዘ የልብ መድሃኒት ተግፃፅና ብስራት እንዲሁም ዛቻና የተስፋ ቃል የያዘ መለኮታዊ የሕይወት መመሪያ ነው

ይህ ቁርኣን ማን እንደሚጠቀምበት አላህ በተከበረ ቃሉ እንዲህ ሲል ይገልፅልናል

" በዚህ ( በቁርኣን ) ውስጥ ለእርሱ ልብ ላለው ወይም እርሱ በልቡ የተጣደ ሆኖ ( ወደሚነበብለት ) ጆሮውን ለጣለ ( ለሰጠ ) ሰው ግሳፄ አለበት " ::

ሱረቱል ቃፍ : 37

በዚህ አንቀፅ በቁርኣን ተጠቃሚ ለመሆን አራት ነገሮች መሟላት እንደሚያስፈልግ አላህ ይነግረናል እነሱም :-

ተፅኖ የሚፈጥር ነገር

ተቀባይ ( የተፅኖ ማረፊያ )

መስፈርት

ከልካይ ነገር መወገድ

ተፅኖ ፈጣሪ ------ ቁርኣን ( ግሳፄ )

ተቀባይ ------ ልብ ( ሕያው የሆነ )

መስፈርት -------- ጆሮ መስጠት

ከልካይ ነገር መወገድ ---- ልብ ሌላ ቦታ አለመሄድ

ቁርኣን ተፅኖ የሚፈጥረው ሕያው በሆነ ልብ በተጣደ ጆሮ ሁለመናውን ወደ ቁርኣን አድርጎ ልቡ ከሸፈተበት መመለስና በቁርኣን ላይ እንዲሆን ማድረግ በቻለ ሰው ላይ ነው

በሱረቱ ያሲን : ከ69 - 70 ላይ አላህ እንዲህ ይላል " ይህ ቁርኣን ግልፅ ግሳፄ እንጂ ሌላ አይደለም :: ሕያው ለኾነ ሊያስጠነቅቅ " ::

ሰለዚህ በቁርኣን ተጠቃሚ ለመሆን እነዚህ አራት ነገሮች አሟልቶ መገኘት ያስፈልጋል

አላህ ከተጠቃሚዎች ያድርገን።

Xabar sifatida yuborish
Sahifamda baham ko'rish
Guruhda ulashish
Tarjima qilib boʻlmadi.

وَٱتَّقُوا۟ فِتْنَةًۭ لَّا تُصِيبَنَّ ٱلَّذِينَ ظَلَمُوا۟ مِنكُمْ خَآصَّةًۭ ۖ وَٱعْلَمُوٓا۟ أَنَّ ٱللَّهَ شَدِيدُ ٱلْعِقَابِ

ከናንተም ውስጥ እነዚያን የበደሉትን ብቻ ለይታ የማትነካን ፈተና ተጠንቀቁ፡፡ አላህም ቅጣቱ ብርቱ መኾኑን እወቁ፡፡

Xabar sifatida yuborish
Sahifamda baham ko'rish
Guruhda ulashish