UMMA TOKEN INVESTOR

abu mdamin shared a
Наган дахаан йохтахам.

O! Israel TURKEY does not owe you anything!!!!

14 views
Send as a message
Share on my page
Share in the group
abu mdamin shared a
Наган дахаан йохтахам.

🍁ነብዩ ﷺ እንዲህ አሉ፦

የሱብሂ ሰላትን የሰገደ ሰው እሱ በአላህ ጥበቃ ሰር ነው…

🍁ጢቢይ ረሂመሁላህ እንዲህ አለ፦ የሱብሂ ሰላት ከሌሎቹ ሰላቶች ተለይታ የመጣችበት ምክንያት ከሌሎች ሰላቶች   ከበድ ስለምትል መሸቃ ስላላት ነው። ይህን መፈፀም ደግሞ የሰውየውን ኢኽላስ የሚያመላክት ነው። በእውነት (በኢኽላስ) በአላህ የሚያምን ደግሞ እሱ በፈጣሪው ጥበቃ ስር ነው።

👉በዚህ ሀዲስ ዙሪያ ሁለት ንግግሮች አሉ፦ ከሁለቱ አንዱን እንይ!

አንደኛው፦ ለማንኛውም ሙስሊም የሱብሂ ሰላትን የሰገደ አካል  ላይ ችግርን አዛን ከማድረስ መቆጠብ! ለምን ከተባለ የሱብሂ ሰላት የሰገደ በአላህ ጥበቃ ስር ስለሆነ። በአላህ ጥበቃ ስር ያለን አካል ላይ የተጋረጠ ሰው ደግሞ የፈጣሪውን ቃል አፍርሷል አስወግዷል ስለዚህ ይህ ሰው ቅጣት ይገባዋል ማለት ነው።

📚ፈይዱል ቀዲር ሊልመናዊ

👉ኢብን ዑሰይሚን ሪያዱ አሷሊሂን ላይ እንዲህ አሉ፦

💫በዚህ ሀዲስ ላይ  ምናየው የሱብሂ ሰላታቸውን የሚሰግዱ ሙስሊሞችን የማክበር ግዴታ እንዳለብን ሚገልፅ ማስረጃ ነው።  ለምን ከተባለ የሱብሂ ሰላትን ሙእሚን እንጂ አይሰግዳትም።

ስለዚህ ማንኛውም ሰው በነሱ ላይ ድንበር ማለፍ አይችልም።

  ይህን አመላካች እንዲሁም አጠናካሪ የሆነ ታሪክ  እንይ

               👇

ዓዕመሽ እንዲህ አለ፦ ሳሊም ኢብን ዓብደላ ሃጃጅ ኢብን ዩሱፍ 👉(መሪ ነበር) እሱ ዘንድ ተቀምጦ ሳለ:  ሃጃጅ እንዲህ አለው፦ ተነስና የዚህን ሰውዬ አንገት ቁረጠው:

🩸ሳሊምም ሰይፉን ያዘ ከዛም ወደ መቅጫው ቦታ ካወጣው በኋ የሱብሂ ሰላትን ሰግደሃል አለው?

🩸ልጁም አዎን አለ

🩸ሳሊምም የፈለከውን መንገድ ይዘክ ሂድ አለው።

🗡ከዛም ሳሊም ሰይፉን ወረወረው

ሀጃጅም አንገቱን መታከው? ብሎ ጠየቀው

ሳሊምም አይ አልመታሁትም አለው

ሃጃጅም ለምን? አለው

💫ሳሊምም እንዲህ አለ፦ እኔ ይህ አባቴ እንዲህ ሲል ሰምቼዋለው ነብዩ  ﷺ እንዲህ አሉ "የሱብሂ ሰላትን የሰገደ ሰው በአላህ ጥበቃ ስር ነው"።

رواه الطبراني في معجم الوسيط 📚

Send as a message
Share on my page
Share in the group
abu mdamin Сhanged his profile picture
7 month
Наган дахаан йохтахам.

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group