UMMA TOKEN INVESTOR

Translation is not possible.

ቀልብ የፅድቅም የጥፋትም የእዝ ማዕከል

~~ ~ ~ ~ ~ ~ ~ ~ ~

ጀነት ነፍስ በምትጠላቸው ነገሮች ተከባለች፤ ጀሀነም ደግሞ ነፍስ በምትወዳቸው ሸይጧን በሚያስውባቸው አማላይ ነገሮች፡፡ በብዙ ሁኔታዎቻችን ከአረሕማን ይልቅ ለሸይጧን የቀረብን ነን፡፡ ዐይኖቻችን፣ ጆሮዎቻችን፣ እጆቻችን፣ እግሮቻችን፣ እንዲሁም ምላሳችን ለሸይጧናዊ ተልእኮ የሰሉ ናቸው፡፡ ቀላሉን አምላካዊ ክልከላ መታገስ አቅቶን ከባባድ ሸይጧናዊ ልፋት ላይ እንተጋለን፡፡ ሁሉም የሰውነታችን ክፍሎች ለጥፋት ሲተባበሩ፣ አንዳቸው ብቻ ለሚበቁት ኸይር ግን ተባብረውም ይዝላሉ፡፡ ይሄ ሁሉ የሚሆነው እንግዲህ ማዕከሉን “ዋግ” ሲመታው ነው፡፡ ቀልብ በሺርክ፣ በቢድዐ፣ በስሜት፣ ለሙስሊሞች በምታረግዘው ክፋት፣ … ከተበከለች ታማ፣ ታውካ፣ አመርቅዛ ትሞታለች። ታዲያ ቀልብ ስትሞት ሞቷ ለኸይሩ እንጂ ለሸሩማ ኢንኩቤተር ትሆናለች - ክፉ የሸር መፈልፈያ። ብቻ ሂወቷ በኢማን ካልኩሌተር ሲሰላ ያለ ኢማን ሂወት የለምና ሞታለች - የምር ሞት! ከዚያስ? ከዚያማ ቀልብ ተበላሽታ ሌላው ሰውነት ምን ጤና ሊኖረው? የአካል እንቅስቃሴ በሙሉ ደመ-ነፍሳዊ ይሆናል። ተንቀሳቃሽ ሙት!!! ግድግዳ የተጠጋ እንጨት ሆኖ ሂወት እንዳለው ያስባል፡፡

ከዚህ በኋላ ዐይንም ዐይን ጆሮም ጆሮ አልሆነም፡፡ የሰማያትና የምድር አፈጣጠር፤ የሌሊትና የቀን መተካካት ለሱ ከታክሲዎች መተላፍ፣ ሽንት ቤት ደርሶ ከመመለስ ብዙም ልዩነት የለውም፡፡ ችግሩ ከማዕከሉ ነዋ!

(أَفَلَمۡ یَسِیرُوا۟ فِی ٱلۡأَرۡضِ فَتَكُونَ لَهُمۡ قُلُوبࣱ یَعۡقِلُونَ بِهَاۤ أَوۡ ءَاذَانࣱ یَسۡمَعُونَ بِهَاۖ فَإِنَّهَا لَا تَعۡمَى ٱلۡأَبۡصَـٰرُ وَلَـٰكِن تَعۡمَى ٱلۡقُلُوبُ ٱلَّتِی فِی ٱلصُّدُورِ)

((ለነርሱም በነርሱ የሚያውቁባቸው ልቦች ወይም በነርሱ የሚሰሙባቸው ጆሮዎች ይኖሩዋቸው ዘንድ በምድር ላይ አይሄዱምን እነሆ ዐይኖች አይታወሩም። ግን እነዚያ በደረቶች ውስጥ ያሉት ልቦች ይታወራሉ፡፡)) (አልሐጅ፡ 46)

በሌላ በኩል ልብ ከተስተካከለች፣ በኢማን ከተዋበች፣ በተቅዋ ካሸበረቀች መላ ሰውነት ጤና ይኖረዋል፡፡ ፊትም ኑር ይላበሳል፡፡ ዐይኖች በሐራም አይገግሙም፡፡ ጆሮዎች ለሙዚቃ አይቆሙም፡፡ ምላስም የሀሜት ማሽን አትሆንም፡፡ ከውጭ ሙስሊም ያልሆነ ገፅታ እየተስተዋለ ምላስ “ዋናው ልብ ነው” እያለች አታሽቃብጥም፡፡ ማዕከሉ ነቅቶባታላ!

ልብ ስትስተካከል እውነተኛ ማንነት ይገኛል፡፡ ከውስጥም ሙስሊም፣ ከውጭም ሙስሊም! በሐያእ የለሰለሰ፣ በውጭ ገፅታው ያልተኮፈሰ፣ በልቡ የመጠቀ፣ ከእንቶ ፈንቶ የራቀ ልዩ ስብእና!!! አቡበክር አሲዲቅ ረዲየላሁ ዐንሁ ከሌሎች የመጠቁት በሶላትና በፆማቸው ብዛት አልነበረም፡፡ ይልቁንም ልባቸው ውስጥ በፀደቀ ነገር ነበር። ኢማን! የቀልብ ልዩ ክብር!!!

ባጭሩ ጥፋታችንም ልማታችንም ከልብ ጋር የተሳሰረ ነው ማለት ነው፡፡ ታዲያ እኔና እርሶ የቱጋ ነን? ሰገነት ወይስ ጫማ ተራ? ነው ወይስ መሀል ሰፋሪ? በሌላ አነጋገር ልባችን ጤነኛ ነው? በሽተኛ ነው? ወይስ ሙት ነው?

ለካ ይህንንም ለማወቅ ልብ ያስፈልጋል፡፡ ((ባለ ልቦናዎቹ እንጂ አይገነዘቡም)) አይደል ያለው ኻሊቁ?

አንተ ልቦችን ገለባባጭ የሆንከው ጌታችን ሆይ! ልቦቻችንን ወደ ትእዛዝህ አዙርልን። በዲንህም ላይ አፅናን፡፡ አላሁመ ኣሚን፡፡

(ኢብኑ ሙነወር፣ 2001)

#islam #gaza #ислам #хадисы #Коран #quran #islamedia #Палестина #إسلاميواليت #коран #إسلاميديا #Ислам #إسلاميكوين #сунна #дуа #акыда #хадис #рамадан #Рамадан #намаз

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

ዑመሩል ፋሩቅ ሸይጧን የሚሸሸው ሶሐቢይ!

~

ሶሐቢዩ ሰዕድ ብኑ አቢ ወቃስ (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንዲህ ይላሉ፡-

በአንድ ወቅት ዑመር ብኑል ኸጧብ ከነቢዩ (ﷺ) ቤት ሊገቡ ፍቃድ ጠየቁ፡፡ ከነቢዩ (ﷺ) ዘንድ ድምፃቸውን ከፍ አድርገው የሚያወሩ ሴቶች ነበሩ፡፡ የዑመርን ድምፅ ሲሰሙ ሒጃባቸውን አስተካክለው ሊለብሱ ተሯሯጡ፡፡ ረሱል (ﷺ) እየሳቁ ለዑመር እንዲገቡ ፈቀዱላቸው፡፡

ዑመር፡ “አላህ ጥርስህን ያስቀው የአላህ መልእክተኛ ሆይ!” አሏቸው፡፡

ነብዩ (ﷺ)፡ “እነዚህ እኔ ጋር የነበሩ ሴቶች ገረሙኝ፡፡ ድምፅህን ሲሰሙ ወደ ሒጃባቸው ተሯሯጡኮ” አሉ፡፡

ዑመር፡ “አንተ ነህ ልትከበርና ልትፈራ የሚገባህ የአላህ መልእክተኛ ሆይ!!” ካሉ በኋላ “እናንተ የነፍሶቻችሁ ጠላቶች! እኔን ትፈራላችሁ የአላህ መልእክተኛን አትፈሩምና?!” አሉ ለሴቶቹ።

ሴቶቹ፡ “አዎ ከረሱል (ﷺ) ይልቅ አንተ ደረቅና ሃይለኛ ነህ” አሉ፡፡

ከዚያም ረሱል (ﷺ) ለዑመር እንዲህ አሏቸው:– “ነፍሴ በእጁ በሆነችው ጌታ ይሁንብኝ! ሸይጧን በአንድ መንገድ ላይ በጭራሽ አያገኝህም፣ መንገድ ቀይሮ በሌላ መንገድ ቢሄድ እንጂ!” [ቡኻሪ፡ 3294] [ሙስሊም፡ 2396]

ይሄ ሐዲሥ ለዑመር ጠላቶች ምቾት የሚነሳ ነው፡፡ ሺዐዎች የዑመር ስም ሲነሳ በጥላቻ እብደታቸው እንደሚነሳ ይታወቃል፡፡ ዛሬ ድረስ ይሄ ነገር በግልፅ የሚታይ ነው፡፡ እ.ኢ.አ በ2005 ኢራቅ ውስጥ 15 ሰዎች ስማቸው ዑመር ስለሆነ ብቻ በሺዐዎች ተገድለዋል፡፡ በቅርቡም ኢራን ውስጥ በርካታ ዑመሮች በሌላ ሳይሆን በስማቸው ብቻ ከስራ እንደተባረሩ ተነግሯል፡፡ ይሄ ለዑመር ያላቸው ጥላቻ እጅግ የመረረ እንደሆነ የሚያመላክት ነው።

ሌላ ነገር፡፡ መዲና ውስጥ የሚገኘው የነብዩ (ﷺ) መስጂድ ካሉት በርካታ በሮች ውስጥ አንዱ “ባቡ ዑመር" ነው፣ "የዑመር በር”፡፡ ታዲያ ሺዐዎች ምን አሉ? “ለዑመር ካለን ጥላቻ የተነሳ ወደ መስጂዱ ስንገባ በዑመር በር በኩል አንገባም” አሉ። ይህንን የሰማ አንድ ሸይኽ ምን አለ ታዲያ? “ረዲየላሁ ዐንከ ያ ዑመር! ሸይጧን በህይወትህ ሳለህ ብቻ አይለም ሞተህም ይሸሽሃል!”

አላሁ አክበር!!!

(ኢብኑ ሙነወር፣ 03/02/2005)

#islam #gaza #ислам #хадисы #Коран #quran #islamedia #Палестина #إسلاميواليت #коран #إسلاميديا #Ислам #إسلاميكوين #сунна #дуа #акыда #хадис #рамадан #Рамадан #намаз

Send as a message
Share on my page
Share in the group
nurdene abederhimn Сhanged his profile picture
7 month
Translation is not possible.

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group