UMMA TOKEN INVESTOR

Translation is not possible.

አሰላሙአለይኩም ወራመቱላሂ ወበረካቱ

ነገ ጁምዐ ሰለዋት እናብዛ ኢንሻአላህ

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

#ተውሒድ_የመዳኛ_መንገድ_ነው

========================

↪️ከኢብኑ ዐባስ ተይዞ (ረዲየላሁ ዐንሁማ) የአላህ መልእክተኛ ﷺ በጭንቅ ጊዜ እንዲህ ይሉ ነበር:–

( لَا إِلَهَ إِلَّا اللَّهُ الْعَظِيمُ الْحَلِيمُ، لَا إِلَهَ إِلَّا اللَّهُ رَبُّ الْعَرْشِ الْعَظِيمِ، لَا إِلَهَ إِلَّا اللَّهُ رَبُّ السَّمَاوَاتِ وَرَبُّ الْأَرْضِ وَرَبُّ الْعَرْشِ الْكَرِيمِ ) متفق عليه

“ከአንድ አላህ በስተቀር በእውነት የሚመለክ የለም! እርሱም ሀያልና ቻይ ነው። ከአንድ አላህ በስተቀር በእውነት የሚመለክ የለም! እርሱም የሰማያትና የምድር እንዲሁም የዐርሽ ጌታ ነው።” ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።

↪️ከአቢ በክር (ረዲየላሁ ዐንሁ) ተይዞ የአላህ መልእክተኛ ﷺ የጭንቀተኛ ሰው ዱዓ የሚከተለው ነው ብለዋል:–

( اللَّهُمَّ رَحْمَتَكَ أَرْجُو ، فَلَا تَكِلْنِي إِلَى نَفْسِي طَرْفَةَ عَيْنٍ ، وَأَصْلِحْ لِي شَأْنِي كُلَّهُ، لَا إِلَهَ إِلَّا أَنْتَ ) حسنه الألباني في صحيح أبي داود

“አላህ ሆይ! እዝነትህን እከጅላለሁ፣ ራሴን ለራሴ የአይን እርግብግብታ ያህል እንኳን አትተወኝ፣ ጉዳዬን ሁሉ አስተካክልልኝ፣ ከአንተ በስተቀር በእውነት የሚመለክ የለም!።” አልባኒ አቢዳውድ ላይ ሀሰን ነው ብለውታል።

↪️ከሰዕድ ኢብን አቢ ወቃስ ተይዞ (ረዲየላሁ ዐንሁ) የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ አሉ:–

دَعْوَةُ ذِي النُّونِ إِذْ دَعَا، وَهُوَ فِي بَطْنِ الْحُوتِ : ( لَا إِلَهَ إِلَّا أَنْتَ سُبْحَانَكَ إِنِّي كُنْتُ مِنَ الظَّالِمِينَ ؛ فَإِنَّهُ لَمْ يَدْعُ بِهَا رَجُلٌ مُسْلِمٌ فِي شَيْءٍ قَطُّ إِلَّا اسْتَجَابَ اللَّهُ لَهُ ) صححه الألباني في صحيح الترمذي

“የአሳው ባለቤት "ነቢዩላህ ዩኑስ" ጥሪ (ዱዓ) በአሳው ሆድ ውስጥ ሆኑ የሚከተለው ነበር «ከአንተ በስተቀር በእውነት የሚመለክ የለም! ጥራት ይገባህ እኔ ከበደለኞች ሆኜ ነበር» በዚህች ቃል ሙስሊም የሆነ ሰው አላህን አንዳች ነገር አይለምንባትም አላህ ልመናውን ቢቀበለው እንጂ።” አልባኒ ትርሚዚይ ላይ ሶሂህ ነው ብለዋል።

↪️ዓኢሻ (ረዲየላሁ ዐንሃ) እንዲህ ትላለች: ነቢዩ ﷺ ቤተሰባቸውን ሰበሰቡና የሚከተለውን አሉ:–

أَنَّ النَّبِيَّ

صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ جَمَعَ أَهْلَ بَيْتِـهِ ، فَقَالَ : ( إِذَا أَصَابَ أَحَدَكُمْ غَمٌّ أَوْ كَرْبٌ ، فَلْيَقُلِ : اللَّهُ اللَّهُ رَبِّي ، لَا أُشْرِكُ بِهِ شَيْئًا )صححه الألباني في السلسلة الصحيحة

“አንዳችሁን ጭንቀት ከገጠማችሁ: አላህ ጌታዬ ነው በርሱም ምንም አላጋራበትም ይበል።” አልባኒ በሲልሲለቱ ሶሂሃ ሰሂህ ነው ብለውታል።

✔️ኢብኑል ቀይም አላህ ይዘንላቸውና እንዲህ አሉ:– (ይህቺ በባሮቹ ላይ የአላህ ሱና ናት፣ የዱንያ አስቸጋሪ ጭንቀት ሁሉ አልተመለሰችም በተውሒድ ቢሆን እንጂ፣ ለዚያም ነው የጭንቀት ጊዜ ዱዓ በተውሒድ ቃል የሆነችው፣ የአሳው ባለቤት "ነቢዩላህ ዩኑስ" የተጨነቀ ሆኖ አላህን አለመነባትም አላህ ጭንቀቱን በተውዷ ቃል ቢገላግለው እንጂ፣ ከባድ በሆነ ጭንቀት ውስጥ ሽርክ እንጂ አይጥልም፣ ከርሷም የሚያድን የለም ተውሒድ እንጂ፣ እሱ የፍጡራን አስደንጋጭና መውጫው መጠበቂያውና መርጃው ነው።) አልፈዋኢድ ሊብኒል ቀይም 67

ተውሒድ የዱኒያም የአኼራም የጭንቀት ጊዜ መውጫ ነው።

✍🏻ኢብን ሽፋ ሙሀረም 17/1440

========================

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

ልጁ በትካዜ ተውጧል። ቅስሙ ተሰብሯል። በሃሳብ ሩቅ ተጉዟል። ቀጭን

እንጨት በእጁ ጨብጧል። መሬቱን እየጫረ ስዕል የሚስልበት እንጨት

ነው። አንዲት ሴት በአጠገቡ እያለፈለች ሳለ ተመለከተችው። ሀዘን

እንዳጠላበት አስተዋለች። ሁኔታው ልቧን አራራው። " እዚህ ምን እየሰራህ

ነው የኔ ልጅ? ብላ ጠየቀችው። ልጁም " የጀነትን ስዕል ከሳልኩ በኋላ

ለብዙ ቦታ እከፋፍለዋለሁ" አላት። በልጁ ምላሽ ፈገግ ተሰኘች። በመቀጠል

" ከክፍልፋዮቹ መካከል አንዷን ግንጣይ መውሰድ እችል ከሆነ ዋጋው ስንት

እንደሆነ ትነግረኛለህ?" አለችው። ካቀረቀረበት አንገቱን ቀና አደረገና " አዎ

ይቻላል፤ የምፈልገው 20 ሪያል ብቻ ነው" አላት።

.

.

.

.

.

ሴትዮዋም 20 ሪያል ከጣፋጭ ብስኮቶች ጋር ሰጠችው። ወደ ቤቷ

አመራች። ሌሊት ላይ አስደናቂ ህልም አየች። ራሷን ጀነት ውስጥ

ተመለከተች። ሲነጋ ህልሟን ለባሏ አጫወተችው። በሀዘን ቅስሙ ከተሰበረው

ልጅ ጋር ስለነበራት ውሎ ነገረችው።

.

.

.

.

ይህን አስገራሚ ታሪክ የሰማው ባል ልጁ ወዳለበት አካባቢ ገሰገሰ።

ከሳለው የጀነት ክፍልፋይ አንዷን ክፋይ ለመግዛት ቋመጠ። ልጁ አጠገብ

ደረሰ። ሰላምታ ተለዋወጡ። ከዚያም እንዲህ አወጉ: -

.

.

.

.

ሰውየው " ከጀነት ክፍልፋዮች መካከል አንዷን ቁራጭ መግዛት

ስለምፈልግ ዋጋው ስንት ነው?"

.

.

.

ልጁ " በፍፁም አልሸጥም"

.

.

.

ሰውየው "ትላንት ለባለቤቴ አንዷን ክፋይ በ20 ሪያል አልሸጥክላትምን?

.

.

.

ልጁ "ሚስትህ እኮ 20 ሪያል ያወጣችው የነፍሴን ስብራት ለመጠገን

እንጂ ጀነትን በ20 ሪያል ፈልጋ አይደለም። አንተ ግን ጀነትን በ20 ሪያል ብቻ

ነው የፈለከው። ጀነት እኮ የተተመነ ዋጋ የላትም። ወደጀነት ለመግባት

የብዙዎችን የነፍስ ስብራቶች በመጠገን ወጌሻ መሆን ይጠይቃል።

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

*★ መውደድ ሚወዱትን በመከተል ነው !*

* አዎ የምትወደውን ሰው ከኋላኋላው ትከተለዋለህ ፣ በአስተሳሰቡም ፣ በንግግሩም፣ በተግባሩም እሱን ለመምሰል ትጥራለህ እንጂ ከሱ ለመቅደምም ሆነ ለመቃረን በፉፁም አታስብም ። በነብዩ ሷለላሁ አለይሂ ዘመን የነበሩ ሙሽሪኮች እኛኮ አላህን እንወዳለን ሲሉ አላህ የውዴታ መፈተኛ የሆነውን ይህን የቁርኣን አንቀጽ አወረደ :—

{قُلْ إِن كُنتُمْ تُحِبُّونَ اللَّهَ فَاتَّبِعُونِي يُحْبِبْكُمُ اللَّهُ وَيَغْفِرْ لَكُمْ ذُنُوبَكُمْ ۗ وَاللَّهُ غَفُورٌ رَّحِيمٌ }(ሱረቱ አሊ-ዒምራን - 31)

* ((በላቸው፡- «አላህን የምትወዱ እንደኾናችሁ ተከተሉኝ፤ አላህ ይወዳችኋልና፡፡ ኀጢኣቶቻችሁንም ለናንተ ይምራልና፡፡ አላህም መሓሪ አዛኝ ነው፡፡»))

★አዎ አላህን መውደድ በቃል ብቻ ሳይሆን በተግባርም መሆን አለበት ለዚህም ማረጋገጫው ነብዩ ሙሀመድን ሷለላሁ አለይሂ ወሰለም መከተል ነው ። በዚሁ ልክ የነብዩ ሙሀመድንም ሷለላሁ አለይሂ ወሰለም ውዴታ ማረጋገጫው ሱናቸውን በመከተል ነው የሰሩትን በመስራት የተውትን በመተው ፣ ያዘዙትን በመታዘዝ የከለከሉትን በመከልከል ።

★ ያ አላህ እንወድሃለን ውዴታህን በተግባር ከሚያሳዩህ ባርያዎችህ አድርገን

★ ያ አላህ ውዱን ነብይህን ሷለላሁ አለይሂ ወሰለም እንወዳለን ውዴታችንን በተግባር ከሚያውሉ ባርያዎችህ አድርገን 🤲🏻🤲🏻🤲🏻አሚን

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group