UMMA TOKEN INVESTOR

abu yunus shared a
Translation is not possible.

ከቂያማ ምልክቶችመካከል የተወሰኑት የሚከተሉት ናቸዉ

1 ዝሙት ይስፋፋል 2 ወንዶች ሀር ይለብሳሉ

3 ሙዚቃ እንደሚፈቀድ ይነገራል 4 ሴቶች ዘፋኞች በአጫዋችነት ይያዛሉ

5 መጥፎ ቃላቶችንመለዋወጥ ይበዛል

6 ዝምድናን መቁረጥ ይበረክታል

7 ታማኝ ሰዉን እንደ ከዳተኛ መቁጠር እና መወንጀል

8 ከዳተኛን ማገዝ እና ማቅረብ

9 ድንገተኛ ሞት መከሰት

10 መስጅድን እንደ መተላለፊያ መንገድ መጠቀም

11 ጥሪያቸዉ ወይም ተልእኮአቸዉ ተመሳሳይ የሆነ ሁለት ቡድኖች ይፋ ጦር ይማዘዛሉ(የአልይ ና የሙአዉያዉጊያን ያመለክታሉ

12 የዘመን መቀራረብ ወይም የጊዜ መፍጠን (በረካ ማጣት)

13 ፈተናዎች ይደራርሳሉ ፣ተንኮል ይስፋፋል

14 ኢልም ከህፃናት ይፈለጋል

15 የመሬት መንቀጥቀጥ

16 ሰዉነታቸዉን አግባብ ባለዉ ልብስ ያልሸፈኑ ሴቶች ይበዛሉ

17 እዉቀት የሌላቸዉ ሰዎች ህዝባዊ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ይወስናሉ

18 ሰላምታ በትዉዉቅ ላይ ብቻ ይመሰረታል

19 ዉሸት መናገር ይስፋፋል::

20 የንግድ ቤቶች ተቀራርበዉ ይገነባሉ።

21 ለሰይጣን አገልግሎት የሚዉሉ ግመሎች ና ለሰይጣን አገልግሎት የሚዉሉ ቤቶች ይገነባሉ። ማለትም 1 አንድ ሰዉ ከሚጠቀምባቸዉ ዉጭ ያሉ ግመሎች በስድ ሲለቀቁ ሰይጣን ይጋልባቸዋል። 2 ከመኖሪያ ቤት ዉጭ ያሉ ትርፍ ቤቶች ለረጅም ጊዜ ሰዉ ሳይገባባቸዉ ከቆዩ የሰይጣን መኖሪያ ይሆናል።

22 ሰዎች በመስጊድ ዉበት ይፎካከራሉ_በዉስጡ ይመፃደቃሉ።

23 ሺበታቸዉን በጥቁር ቀለም የሚያጠቁሩ ሰዎች ይመጣሉ። እነዚህ ሰዎች የጀነትን ሽታ እንኮአን አያገኙም።

24 ሰዎች አላህን የመታዘዝ ባህሪያቸዉ ይመነምናል።ለአኬራ መስራትም ይቀንሳል።

25 ስስት ይስፋፋል፣ሁሉም ሰዉ ግለኛ ይሆናል፣አዋቂ እዉቀቱን ለማካፈል ይሳሳል።

26 ሰዎች አላማዉን በማያዉቁት ዉጊያ ዉስጥ ይሳተፋሉ (ይጋደላሉ።)"ነፍሴ በእጁ በሆነዉ ጌታ እምላለሁ በሰዎች ላይ ይህ ዘመን ይመጣል።ገዳይ በምን ምክንያት እንደገደለ አያዉቅም-ተገዳይ በምን ምክንያት እንደተገደለ አያዉቅም።

" 27 የህዝብ ገንዘብ ያለ አግባብ ይመዘበራል።

28 አማና (ታማኝነት) ይጎአደላል።

29 ባል ሚስቱን እየታዘዘ እናቱን ይበድላል።

30 በአባቶች ላይ እየተፌዘ (አባት ሳይከበር) ጎአደኛ ይከበራል።

31 በመስጅድ ዉስጥ ጩሀት ይበራከታል።

32 ተንኮሉ ተፈርቶ ሰዉ ይከበራል-ችሎታና ስነ-ምግር ግን የለዉም።

33 ፖሊስ ይበዛል፤ይህም ማለት ወንጀል መበራከቱን ያመለክታል።

34 አንድ ሰዉ በእዉቀቱ አናሳ ሆኖ እና በባህሪዉም ገና ያልተገራ ሆኖ ሳለ ድምፁ የሚያምር ሆኖ በመገኘቱ ብቻ ሶላት እንዲመራ (እንዲያሰግድ) ይደረጋል።

35 ሚስት ባሏን በንግድ እና በስራ ላይ ትጋራለች።

36 ብእር ይበራከታል፤ድርሰት እና ህትመት ይስፋፋል።

37 ልጅ መመኪያ መሆኑ ቀርቶ መተከዣ እና መቆጫ ይሆናል።

38 የዝናብ እጥረት ይስተዋላል።

39 መኪና ይፈለሰፋል። "ከኡመቶቼ መካከል ወደመጨረሻዉ የሚመጡት 'ሱሩጅ ወይም (መኪና) ላይ ይሳፈራሉ። የመጎጎዣ አይነት ነዉ በመስጅድ በሮች ያቆሙታል (ይወርዳሉ) ሴቶቻቸዉ ግን የለባሽ እርቃን ናቸዉ።

40 ፊትና በመብዛቱ ሳቢያ ሞትን መመኘት።

41 ኢራቅ ማእቀብ ይጣልባታል-ምግብናእርዳታ ትከለከላለች።

42 በመቀጠልም ሻም (ሶሪያ፣ሊባኖስ፣ዩርዳኖስ እና ፍልስጤም) ምግብና እርዳታ ይከለከላሉ ማእቀብ ይጣልባቸዋል።

43 የነብዩ ሙሀመድ (ሶ.አ.ወ) ከዚህ አለም በሞት መለየት እንደ አንድ የቂያማ ቀንመድረስ ምልክት ተወስዷል።

44 በይተል መቅደስ (እየሩሳሌም) በሙስሊሞች ቁጥጥር ስር መግባት።

45 በጅምላ ጨራሽ በሽታም ሆነ ጦርነት የሰዉ ህይወት መጥፋት።

46 ሙስና፣ማጭበርበር እናየ ዋጋ ንረት እያየለ መምጣት።

47 በአረቦችም ሆነ በሌሎች ወገኖች ቤት ዉስጥ ጣልቃ ገብነት እና ፊትና(መከራ) ይስተዋላል።

48 በሙስሊሞች እና በሮማዉያን(አዉሮፓ እና አሜሪካ) የጋራ ስምምነት ይፈረማል። አዉፍ ኢብን ማሊክ (ረ.አ) እንዳስተላለፉት የአላህ መልእክተኛ (ሶ.አ.ወ) እንዲህ ብለዋል፦ የቂያማ ቀን ከመድረሱ በፊት ስድስት ነገሮች

ይከሰታሉ፥ 1 የኔሞት። 2 ከዚያም በይተልመቅዲስ ይከፈታል። 3 ከዚያም ሁለት ሞት እዉን ይሆናል። 4 አንድ ሰዉ መቶ ዲናር ቢሰጠዉ እንኳን ምንም አይመስለዉም። 5 ከዚያ በሁላ ደግሞ ፊትና ይከሰታል። 6 ከዚያም በናንተና በነጮች መካከል ስምምነት ይኖራል። ይከዷችሁል ። 80 አላማ ይዘዉ ይመጣሉ እያንዳንዱ አላማ ደግሞ 12 ሺህ (ንኡስ አላማ) አለዉ።

ያአላህ እዘንልን ከምናውቀውም ከማናውቀውም ፊትና ጠብቀን በዲናች አትፈትነን በዲናችን ላይ የመጣውን ፊትና አንሳልን ያረብ

➤➤ይህንንፔጅ Like Share

በማድረግ የበኩሎን ይወጡ ።

★★★Like The Page★★

Send as a message
Share on my page
Share in the group
abu yunus shared a
Translation is not possible.

# እውን ፈጣሪ አለን. ???

አንድ የእምነት ሰው ጸጉሩን ሊስተካከል ወደ አንድ ጸጉር

አስተካካይ ቤት ይሄዳል። እናም በመሀል ጫወታ ይጀምራል።

ጸጉር አስተካካይ፦ታውቃለህ ፈጣሪ የለም ?

ተስተካካይ፦በመገረም እንዴት?

አስተካካይ፦አይታይህም?

ተስተካካይ፦ምኑ?

አስተካካይ፦እንዴ ፈጣሪ ቢኖር እኮ ይሄ ሁሉ

ጦርነት፣ረሀብ፣ችግር፣ስርአት አልበኝነት አይኖርም ነበር ስለዚህ

ፈጣሪ አንዴ ፈጥሮን ትቶን ሄዷል ወይ ሞቷል።

ተስተካካይ፦ታውቃለህ ጸጉር አስተካካይም የሚባል የለም

አስተካካይ፦ግራ በመጋባት እንዲህም በመገርም እንዴት?

ተስተካካይ፦ጸጉር አስተካካይ ቢኖርማ ጸጉሩ የጎፈረ ጺሙ

የተንዠረገገ ሰው አይኖርም ነበር።

አስተካካይ፦እነዚህ ሰዎች እኮ ወደ ጸጉር አስተካካይ

አለመምጣታቸው ነው እንጂ ቢመጡማ ኖሮ አንድም ጸጉሩ

የተንዠረገገ እና የተንጨባረረ ጸጉር አታይም ነበር።

ተስተካካይ፦ትክክል ብለሀል በአለማችን ያለው ችግርም ይኸው

ነው ሰው ከፈጣሪው ስለራቀ ነው እንጂ ፈጣሪ ስለሌለ

አይደለም።

ከተመቸወ. ሼር

profileን ፣፣፣ላይክ በማድርግ ቤተሰብ ይሁኑ follow me

ይህንንፔጅ Like Share Invite

በማድረግ የበኩሎን ይወጡ ።

Send as a message
Share on my page
Share in the group
abu yunus Сhanged his profile picture
6 month
Translation is not possible.

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group